Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የኦብነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ በአስቸኳይ ስብሰባ ውሣኔዎች በሙሉ ተቀባይነት እንደሌላቸው ምርጫ ቦርድ አስታወቀ
News

የኦብነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ በአስቸኳይ ስብሰባ ውሣኔዎች በሙሉ ተቀባይነት እንደሌላቸው ምርጫ ቦርድ አስታወቀ

Ethioreview newsEthioreview news—February 16, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የኦብነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ በአስቸኳይ ስብሰባ ተላልፈዋል የተባሉ ውሣኔዎች በሙሉ ተቀባይነት እንደሌላቸው ምርጫ ቦርድ አስታወቀ


የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር ኦብነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ በአስቸኳይ ስብሰባ ተላልፈዋል የተባሉት ውሣኔዎች በሙሉ ተቀባይነት እንደሌላቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ በማህበራዊ ገፁ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ)ን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ ሙሉ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

እነ አቶ ራያል ሃሙድ ጥር 24 ቀን በተፃፈ ደብዳቤ የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር/ኦብነግ ከጥር 12-15 ቀን 2013 ዓ.ም ባካሄደው አስቸኳይ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ በፓርቲው ውስጠ ደንብ እና ሌሎች የውስጥ መመሪያዎች፣ ከቀረቡት ሪፖርቶች እና ግኝቶች አንፃር በጥልቅ አጥንቶ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አብዲራህማን ማህዲ የሊቀመንበርነት ቃለ መሃላቸውን እና የድርጅቱን ውስጠ ደንቦች ጥሰዋል የሚል ድምዳሜ ላይ መድረሱንና ከሊቀመንበርነታቸው መነሳታቸውን፤ በአራት ወራት ውስጥ ብሔራዊ ጉባኤ እንዲካሄድ፤ አቶ ራያል ሃሙድ ተጠባባቂ ሊቀመንበር እንዲሆኑ መወሰኑን እንዲሁም ተጠባባቂ ሊቀመንበሩ 15 የሽግግር ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት እና 3 የውስጥ ኦዲተሮች መምረጣቸውን ገልፀው ዝርዝሩን አያይዘው አቅርበዋል፡፡

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

በተጨማሪም ጥር 26 ቀን 2013 ዓ.ም. በፃፉት ደብዳቤ የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ከጥር 12-15 ቀን 2013 ዓ.ም. ባካሄው አስቸኳይ ስብሰባ የፓርቲው ሊቀመንበር እንዲታገዱ የወሰነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በፓርቲው ሊቀመንበር በተፈረመና በ29/01/2021 በቁጥር Chair/ONLF/G/D/001/21 ለኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር የዲሲፕሊን ኮሚቴ በተፃፈ እና ለቦርዱ በግልባጭ በተላከ ደብዳቤ በፓርቲው ስነምግባር ደንብ አንቀፅ 11(b)፣ አንቀፅ 17(b)፣ አንቀፅ 22(b) በአንቀፅ 23(b) እና በአንቀፅ 29 መሠረት ክስ ቀርቦ በዲሲፕሊን ኮሚቴው ከተገመገመና ከተጣራ በኋላ የክስ ዝርዝሮች ከአቃቤ ሕግ ከተሰሙ በኋላ የዲሲፕሊን ኮሚቴው ተከሳሾቹ የተከሰሱትበትን ጥፋቶች መፈፀማቸውን አረጋግጠው 22 ሰዎች እንዲባረሩ፣ 7 ሰዎች ለ6 ወራት እንዲታገዱ፣ ጥፋተኛ የተባሉ ሰዎች በፓርቲው ሕጎች በተደነገገው መሠረት ቅጣቱ ከተጣለበት ቀን ጀምሮ በ1 ወር ጊዜ ውስጥ ይግባኝ ማለት እንደሚችሉ በግልባጭ ለቦርዱ አሳውቋል፡፡

ቦርዱ በፓርቲው አመራሮች መካከል ያለውን አለመግባባት አስመልክቶ የቀረቡትን ሰነዶች በመመርመር ከዚህ የሚከተለውን ውሣኔ ወስኗል፡፡ በእነ አቶ ራያል ሃሙድ በኩል ከጥር 12-15 ቀን 2013 ዓ.ም. ተካሂዷል የተባለው አስቸኳይ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ስለመጠራቱ የሚያሳይ ሰነድ ያልቀረበ በመሆኑ፣

በአስቸኳይ ስብሰባው ላይ ተገኙ ከተባሉት 47 ሰዎች መሃል 10 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ብቻ በመሆናቸው በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀፅ 11.2 እና በአንቀፅ 13.1 መሠረት ምልአተ ጉባኤ ሳይሟላ የተካሄደ ስብሰባ በመሆኑ፤

በእለቱ የተካሄደውን ስብሰባ የመሩትና የፓርቲው “ምክትል ሊቀመንበር” እንደሆኑ የተገለፁት አቶ ራያል ሃሙድ በቦርዱ ጽሕፈት ቤት በሚገኘው የፓርቲው ሰነድ ላይ የሚታወቁት በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ሲሆን የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ አህመድ ያሲን ሼክ ኢብራሂም በመሆናቸው፤

የፓርቲው ሊቀመንበር የፈፀሟቸው ጉዳዮች በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀፅ 33 መሠረት በዲስፕሊን ኮሚቴ ስለመታየታቸው የቀረበ ሰነድ ባለመኖሩ፣

በዕለቱ በተካሄደው ስብሰባ አስራ አምስት “የሽግግር ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ” እና ሶስት የውስጥ ኦዲት መመረጡን መግለፁ ስብሰባው ምልአተ ጉባኤ ሳይሟላ የተካሄደ ከመሆኑ በተጨማሪ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ስለ “ሽግግር ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ” የተደነገገ ባለመኖሩ፣

በአራት ወራት ውስጥ ብሔራዊ ጉባኤ እንዲካሄድ የተላለፈው ውሣኔ ምልአተ ጉባኤ ሳይሟላ የተካሄደ ከመሆኑ በተጨማሪ ከመተዳደሪያ ደንቡ አንቀፅ 10.3 እና አንቀፅ 12.7 ጋር የሚቃረን በመሆኑ፣

ቦርዱ ከላይ የተገለፁት በፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አስቸኳይ ስብሰባ ተላልፈዋል የተባሉት ውሣኔዎች በሙሉ ተቀባይነት የላቸውም ሲል ወስኗል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በፓርቲው ሊቀመንበር በኩል በፓርቲው ስነምግባር ደንብ መሠረት ክስ ቀርቦ በዲሲፕሊን ኮሚቴው ከተገመገመና ከተጣራ በኋላ 22 ሰዎች እንዲባረሩ 7 ሰዎች ለ6 ወራት እንዲታገዱ ስለመወሰኑ የተገለፀው ተጠቃሾቹ የተከሰሱበትን ጉዳይም ሆነ አጠቃላይ ሂደቱን የሚያሳይ ቃለጉባኤና ተያያዥ ሰነዶች ያልቀረቡ በመሆኑ ቦርዱ ውሣኔው ተቀባይነት የለውም ሲል የወሰነ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።

EBC

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
እናት ፓርቲ ለቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ከ50 በላይ ሴት እጩዎች ማቅረቡን አስታወቀ
የጣና በለስ ቁጥር አንድ የስኳር ፋብሪካ ከሶስት ወራት በኋላ ወደ ሙከራ ምርት ሊሸጋገር ነው፡- ስኳር ኮርፖሬሽን
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2