Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  “የኤርትራ ወታደሮች በጦርነቱ ተሳትፈዋል” ሲል ኢዜማ ሪፖርት አቀረበ
News

“የኤርትራ ወታደሮች በጦርነቱ ተሳትፈዋል” ሲል ኢዜማ ሪፖርት አቀረበ

Ethioreview newsEthioreview news—February 11, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ኢዜማ በርዕስ ከፋፍሎ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ኤርትራ ሰራዊቷን ማዝመቷንና የህወሃት ሃይልን መውጋቷን ይፋ አደረገ። በማይክድራ ሪፖርቱ ግርግጌ በግልጽ እንዳስቀመጠው ” የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት” ሲል የገለጸው ሃይል ከሌሎች በስም ከጠቀሳቸው አደረጃጀቶች ጋር አብረው ነው ህወሃትን የወጉት። በዚህም ጦርነቱ ሊወስድ የነበረው ጊዜ እንዳጠረም አመልክቷል። ኢዜማ እጅግ እያነታረከ ያለውንና ትህነግ ዳግም ነብስ እንዲዘራ የሚደረገው ዘመቻ አንኳር የሆነውን ጉዳይ ጦርነቱ ከተካሄደ ወራት በሁዋላ ይህንን ጉዳይ አንስቶ ምስክር ለመሆን የመወሰኑ ግብ ምን እንደሆነ እንዳልገባቸው ሪፖርቱን ተከትሎ አስተያየት እየተሰጠ ነው። ጉዳዩ ኢዜማን ዋጋ እንደሚያስከፍለው ተጠቁሟል።

“የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ የኤርትራ መከላከያ ሠራዊት፣ የአካባቢው ሚሊሺያ አባላት፣ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል እና እንደ ግለሰብ የታጠቁ ነዋሪዎች በጋራ ተቀናጅተው በመሰለፍ የሕወሓትን ኃይል በመፋለማቸው ጦርነቱ ሊወስድ ከሚችለው ጊዜ ባነሰ መቋጨቱን ነዋሪዎች አስረድተዋል” ያለው ኢዜማ በማይካድራ ጉብኘት ያደረጉት አባላቱ እንዳረጋገጡት የአካባቢው ነዋሪዎች አሁንም ሌላ ስጋት አለባቸው።

ሪፕርቱ የኤርትራ ወታደሮች ባይደርሱ አስከፊ ቀውስ ሊደርስ ይችል እንደነበር ጠቁሞ የነዋሪዎቹን ስጋት ሲገልጽ ” … የሱዳን ጦር ሊመታን ይችላል፤ ‹‹ሳምሪ›› የሚባለው አደረጃጀት ሙሉ ለሙሉ ስለመጥፋቱ እርግጠኞች ስላልሆንን በድጋሚ ሊያጠቃን ይችላል፤ በየአካባቢው ተቆርጦ የቀረው የሕወሓት ታጣቂ ቡድን ባልታሰበ ጊዜና ሁኔታ ጥቃት ሊፈፅምብን ይችላል” በማለት ነው። አያይዞም እነዚህኑ በስም ፣ በብዛት ወይም በብሄር ያልጠቀሳቸውን ነዋሪዎች ጠቅሶ ” በአማራ ክልል አስተዳደር በኩል የአድሎዊነት ስሜት እየተስተዋለ ስለሆነ ስጋት ውስጥ ወድቀናል በማለት ነዋሪዎች ያለባቸውን ስጋት ጠቁመዋል” ሲል የኢዜማ ሪፖርት ያትታል። የአማራ ክልል ለምን? እነማን ላይ? እንዴት አይነት በደል እንደሚፈጽም በሪፖርቱ አልተብራራም።

ኢዜማ በመቀለ ጉብኝቱም ሆነ በሁመራ አካባቢ አደረኩ ባለው ማጣራት የአገር መከለከያ ላይ ስለተፈጸመው ወንጀል የትግራይ ነዋሪዎችን ጠይቆ ምን እንዳሉት በዝርዝር አልተናገረም። የራሱንም እይታ በሪፖርቱ አላካተተም።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ዝግጅት ክፍላችን ያነጋገራቸው ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የዩኒዘርስቲ መምህር ” ኢዜማ በዚ ሪፖርቱ ዋጋ ይከፍላል” ብለዋል። አያይዘውም ከሶስት ወር በሁዋላ ሄዶ ዓለም መንግስትን ወጥሮ በያዘበት ጉዳይ ላይ መረጃ መስጠት ፖለቲካሊ ስህተት መሆኑን ጠቁመዋል። ከዛም በላይ ” ከማእከላዊ መንግስትም ሆነ ከአማራ ክልል ጋር ያለው ግንኙነት ሊበላሽ ይችላል የሚል ግምት አለኝ። ተጋራቸው ስህተት እንደሆን ከዛሬ ማታ በሁዋላ ሪፖርቱ ለፖለቲካ ግብዓት ሲውል ያዩታል። በትግራይ ያላቸውን ስም ለማደስ ከሆነ መንገዱ ይሄ አይደለም” ሲል ተናግረዋል።

የተለያዩ በስም የጠቀሳቸውን ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሰፈሩ ተፈናቃዮችን እንደጎበኘና የተለያዩ ወጣቶችን እንዳናገረ የጠቆመው የኢዜማ መግለጫ

  • በኤርትራ ወታደሮች ፈፀሙት ያሉትን አሰቃቂ ጥቃቶች ገልጸዋል፣
  • በትግራይ ሕዝብ ላይ ከ40 ዓመት በላይ ተጭኖ የቆየ ሥርዓት በቅርቡ ከጫንቃው ቢነሳም ሕዝቡን በፍጥነት ማሳመንና ወደ ቀድሞ ሕይወት ለመመለስ ጊዜ ስለሚፈልግ የመንግሥት ታጋሸነት እንደሚያስፈልግ፣
  • በትግራይ በየ20 ዓመቱ ጦርነት እየተቀሰቀሰ ልጆቿን የምትገብርበት ሁኔታ መቀጠሉ እንደጎዳቸው በምርጫ የሚያምን ትውልድ መፈጠር እንደሚያስፈልግ፣
  • የሕውሓት አመራሮች ተመልሰው ይመጣሉ በማለት ተስፋ የሚያደርጉ ሰዎች እንደአሉ፡፡ በተለይ ወጣቶቹ ከዚህ ስሜት እንዲወጡ ጊዜያቸውን በሥራ እንዲያሳልፉ ማድረግ እንደሚገባ፣
  • አብዛኛው አቅም ያላቸው ወጣቶች በመሸሻቸው ስልክም ስለማይሠራ የሸሹትን ቤተሰቦቻቸው ደኅንነታቸውን ለማረጋገጥ አለመቻላቸው ከፍተኛ ጭንቀት እንደፈጠረባቸው፣
  • አሁን ላይ ፖለቲካውን ለጊዜው በማቆየት ሰብዓዊ ድጋፍ ላይ ሁሉም ርብርብ ሊያደረግ እንደሚገባ ነዋሪዎቹ አጽንኦት ሰጥተው ለአመራሮቹ ገልጸዋል፡፡

ስለማይካድራ የቀረበው ሪፖርት ሙሉ ቃል ይህን ይመስላል

ወደ ማይካድራ የተጓዘው ልዑክ ቡድን መረጃ ያሰባሰበው የአካባቢው ነዋሪዎችን፣ የተጎጂ ቤተሰቦችን፣ ቀብር አስፈጻሚዎችን እና ወታደሮችን ቃለ-መጠይቅ በማድረግ ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የጅምላ ቀብር ቦታዎችን፤ ሰፋፊ ሜካናይዝድ እርሻ ቦታዎችን፤ የተለያዩ ጥቃት ለመፈፀሚያነት የተዘጋጁ ድምዕ አልባ መሣሪያዎች የተከማቹባቸውን ሕንጻዎች፤ በከፍተኛ ደረጃ ግጭት የተካሄደባቸው ሥፍራዎችን (ለምሳሌ ከአዲስ አበባ 970 ኪሜ ላይ ከባድ እልቂትና ከሕወሓት ጋር የመጨረሻ ከባድ ግጭት የተካሄደበትን ንጓራ ድልድይን የመሳሰሉ)፤ በባህላዊ ጦር መሳሪያ እልቂት የተፈጸመባቸው አካባቢዎችን፤ ቀደም ሲል የሕወሓት ወታደራዊ ካምፕ ነበሩ የተባሉ ቦታዎችን ወዘተ… በመጎበኘት መረጃዎችን ለማሰባሰብ ተሞክሯል፡፡

በግጭቱ ወቅት የታዩ ክስተቶች

ሕወሓት ያስተዳድራቸው በነበሩ አካባቢዎች በተለይም ማይካድራ እና ሑመራ ግጭቱን ተከትሎ ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ፣ ሞት እና የሀብት ውድመት ተከስቷል፡፡ የማይካድራው እልቂት የተጀመረው ጥቅምት 29 ቀን 2013 ዓ.ም ለጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም አጥቢያ ሲሆን፤ እስከ ኅዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ በነዋሪዎቹ ላይ እልቂት እንደተፈፀመ ልዑክ ቡድኑ ከነዋሪዎች ለመረዳት ችሏል፡፡ የሟቾቹ ቁጥር በሚመለከት ልዑክ ቡድኑ የተለያዩ መረጃዎችን የአካባቢው ነዋሪዎችን፣ ቀብር አስፈጻሚዎች እና የተጎጂ ቤተሰቦችን ቃለ መጠይቅ በማድረግ መረጃ ለማሰባሰብ ሙከራ አድርጎ የነበረ ሲሆን የሟቾቹ ብዛት ቁጥር ከፍተኛ መሆኑንና ትክክለኛ ቁጥር ለማስቀመጥ እንደሚያዳግት ለመረዳት ተችሏል፡፡ ቡድኑ ከላይ የተጠቀሱትን አካላት ቃለመጠይቅ ከማድረግ በተጨማሪ የጅምላ ቀብር ሥፍራዎችን ተመልክቷል፡፡

ሟቾቹን አንድ በአንድ ለመቅበር ሙከራ ተደርጎ የነበረ ቢሆንም የሟቾቹ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ የተነሳ ጉድጓድ መቆፈር እና አስክሬኖቹን መሸከም ስላቃተ በጅምላ ከመቅበር ውጪ ሌላ አማራጭ ስላልተገኘ አስክሬኖቹን በዶዘር መቅበር ብቸኛ አማራጭ እንደነበር ነዋሪዎች ገልፀዋል፡፡ ሟቾች ማንነታቸው እየተለየ የተጠቁ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል፡፡

ወደ ማይካድራ የተጓዘው የኢዜማ ልዑክ ቡድን ፖለቲካዊ ቀውስ ወደተባባሰባቸው ማይካድራ፣ ሑመራ እና አካባቢው በደረሰበት ወቅት የቀውሱ መጠን ካለፈው አንጻር እንደቀነሰ ተረድቷል፡፡ ይህ ሊሆን የቻለውም እልቂቱ እንዲያበቃ፤ ቂመኝነት እንዲቀር፤ ሀዘኑ እንዲለዝብ የሃይማኖት አባቶች መገዘታቸው እና በሕዝቡ ውስጥ ሆነው ችግሩ እንዲፈጠርና የተፈጠረውም እንዲባባስ ሲያደርጉ የነበሩ ግለሰቦች ከአካባቢው በመሰወራቸው መሆኑን ልዑክ ቡድኑ መረዳት ችሏል።

 የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ የኤርትራ መከላከያ ሠራዊት፣ የአካባቢው ሚሊሺያ አባላት፣ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል እና እንደ ግለሰብ የታጠቁ ነዋሪዎች በጋራ ተቀናጅተው በመሰለፍ የሕወሓትን ኃይል በመፋለማቸው ጦርነቱ ሊወስድ ከሚችለው ጊዜ ባነሰ መቋጨቱን ነዋሪዎች አስረድተዋል።

  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
How to Stop Ethnic Nationalism From Tearing Ethiopia Apart.
በትግራይ በከፊልና ሙሉ በሙሉ አቁመው የነበሩ የጤና ተቋማት ወደ አገልግሎት እየተመለሱ ነው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2