Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ለተሳካ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር አሁንም ቁልፍ ጉዳይ ነው እንላለን (ኦፌከ)
News

ለተሳካ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር አሁንም ቁልፍ ጉዳይ ነው እንላለን (ኦፌከ)

Ethioreview newsEthioreview news—March 4, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

(ከኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌከ) የተሰጠ መግለጫ)

ከሁለት የፖለቲካ ድርጅቶች፤ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፌዲን) እና ከኦሮሞ ሕዝብ ኮንግረስ (ኦሕኮ) ውህደት ሐምሌ 22/2004 የተመሠረተው ፓርቲያችን፤ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ)፤ በአገራችን ውስጥ በተካሄዱት ምርጫዎች በአብዛኛዎቹ ስንሳተፍ ቆይተናል፡፡ ከውህደቱ በፊት በተካሄደው የ1997 ዓም 3ኛ ዙር ምርጫ ላይ ኦፌኮን የመሰረቱ ፓርቲዎች በተናጠል ተሳትፈው ብዛት ያላቸውን መቀመጫዎች ያሸነፍን ሲሆን፤ በተፈጸመው የኢህአዴግ የዘረፋ ተግባር ምክንያት ተመናምኖ ኦሕኮ 43 እና ኦፌዲን 11 መቀመጫዎችን በማግኘት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ገብተዋል፡፡ በጬፌ ኦሮሚያም፤ ኦሕኮ 105 እና ኦፌዲን 10 መቀመጫዎች ነበሯቸው፡፡ ከዚያ በኋላ በነበሩት ምርጫዎች በገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ ሕገ ወጥ ዘረፋ ምክንያት የሕዝባችንን ድምፅ ልንከላከል እንዳልቻልን ይታወቃል፡፡

እንዴዚያም ሆኖ ብዙዎች ተስፋ በቆረጡበት ጊዜ ቄሮ የሚባለውን የኦሮሞ ወጣቶችን በዋናነት ከአንቀሳቀሱት የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ውስጥ ኦፌኮ አንዱ ሆኖ በቆራጥነት በመሳተፍ አባላቱን ውድ ዋጋ አስከፍሎ ላሁኑ ለውጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳደረገም በአደባባይ ይታወቃል፡፡
ኦፌኮ በአንድ በኩል በ2012 ሊካሄድ በነበረው ምርጫም ሆነ በ2013 ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው ምርጫ ላይ ለመሳተፍ አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረገ በሌላ በኩል ደግሞ የተሳካ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ይካሄድ ዘንድ ያለመታከት ብሔራዊ መግባባት በሀገራችን እንዲፈጠር ስጠይቅ ቆይቷል፡፡ ብሔራዊ መግባባት ለሀገራችን ሠላምና መረጋጋት፣ ለነፃና ፍትሓዊ ምርጫ ከሁሉም በላይ ደግሞ ለተሳካ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን ከትንንሽ ስብሰባዎች እሰከ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በተደረጉ ስብሰባዎች ላይ ተናግረናል፡፡ ላለፉት ሦስት ዓመታት ባወጣናቸው መግለጫዎችም አጥብቀን ጠይቀናል፡፡ ነገር ግን ገዥው ፓርቲ ለሥልጣን ባለው ስስት ምክንያት ምክራችንን አልተቀበለም፡፡ ብሔራዊ መግባባቱም ባለመሳካቱም እንደፈራነው አገሪቱም ሆነ እኛ አስቸጋሪ የፖለቲካ አጣብቂኝ ውስጥ ገብተናል፡፡

ላላፉት ወራትም ምርጫ ውስጥ ለመሳተፍ እንዲያስችለን የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮና የምርጫ ቦርድን ጨምሮ ለሚመለከታቸው ሁሉ ስናሳውቅ ቆይተናል፡፡

  1. በዞንና በወረዳ ደረጃ የሚገኙ ጽ/ቤቶቻችን አንዳንዶች ተሰብረው ስለተዘረፉ፤ አንዳንዶች ደግሞ በአመራር አባላቱ ላይ ከደረሰ ዛቻና ማስፈራራት የተነሳ ስለተዘጉ እንዲከፈቱልን፣
  2. አባሎቻችን ከላይኛው እስከ ታችኛው እርከን ድረስ ያሉትና የፓርቲያችንን ምርጫ ውድድር ሊያስተባብሩ፣ ሊወዳደሩና ሊታዘቡ የሚችሉ በተለይ በዞንና ወረዳ እርከኖች ላይ የሚገኙ መታሰራቸውን፣ ማስፈራሪያ ስለደረሰባቸው አከባቢያቸውን ለቅቀው መሰደዳቸውን፣ በዋና ጽ/ቤት ደረጃ ምርጫውን እንዲያስተባብሩ ከተመደቡት አምስት አባላት ውስጥ አራቱ አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ደጀነ ጣፋ፣ አቶ ጃዋር ሲራጅ ሞሃመድ እና አቶ ሀምዛ አዳነ መታሰራቸውን፤ ይህ እርምጃም ምርጫውን እንዳንወዳደር ሆን ተብሎ የተደረገ መሆኑን ለሚመለከታቸው አሳውቀናል፡፡
  3. ሥልጣን ላይ ያለው ፓርቲ እና መንግስታዊ መዋቅሩ የተደባለቀ ስለሆነ የፖለቲካ ምህዳሩ በመጥበቡ በነፃነት ተንቀሳቀሰን የፓርቲያችንን ፖሊሲ እና የፖለቲካ ፕሮግራም ለሕዝብ ማድረስ ያለመቻላችንን፣
  4. በገለልተኝነት ምርጫውን ያስፈፅማሉ የተባሉት የምርጫ አስፈፃሚዎችም በገዥው ፓርቲ ካድሬዎች የተሞሉና ቀሪዎች ደግሞ ሕግ የማውጣት ከፍተኛ ኃላፊነት የሚጠይቀውን የሕዝብ ተወካዮች ምርጫን የማስፈጸም ልምድና ቁመና ላይ እንዳልሆኑ እና በሁለቱም በኩል ፍትሓዊ ምርጫ ያስፈጽማሉ የሚል እምነት እንደሌለንም ለምርጫ ቦርድ ደጋግመን አሳውቀናል፡፡
  5. በኦፌኮ አባላትና ደጋፊዎች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ይቆም ዘንድ ለኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት፣ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት፣ ለኢፌዲሪ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና ለኢፌዲሪ ጠቅላይ አቃበ ሕግ አቤቱታ ብናቀርብም አባ ካና ያለን አካል የለም፡፡ እዚህ ላይ የበለጠ የሚገርመው ደግሞ የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች የኦፌኮን መሀከለኛ እና የበታች አመራሮችን በማሰርና በማሳደድ የላይኛው አመራር አካል እንድንሳፈፍ እያደረጉ፣ ጅብ እንኳን ወደ ማያውቁት አገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ የሚለውን ተረት ረስተው፤ ሲፈልጉ ድርጅታችን ምርጫውን ፈርቶ ሊወጣ ነው፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ማን ሕወሓትን አምርሮ ሲታገል እንደነበረ እንደረሳ ሰው፤ ለሕወሓት ልዩ ፍቅር ብለው ከምርጫ ውድድሩ ሊወጡ ነው ይሉናል፡፡
  6. በጣም ጥቂት ከሚባሉ በስተቀር በአገር ውስጥና ከአገር ውጪ የሚገኙ ሜዲያዎች፤ በተለይም ከሕዝብ በተሰበሰበ ግብር የሚተዳደሩት ሜዲያዎች በገለልተኝነት እንዳይሰሩ በመደረጋቸው ያጋጠሙን ችግሮች ናቸው፡፡
More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ስለሆነም፤ ድርጅታችን የተቋቋመው እንደማንኛውም ፓርቲ ተወዳድሮ የመንግስት ሥልጣን መያዝ መሆኑ ታውቆ በኃይል የተዘጉ ጽ/ቤቶቻችን ተከፍተውና የታሰሩ አባሎቻችን ተፈትተው እንዲሁም አስፈላጊ ከሆነ የምርጫ መርሐ ግብሩ ተሻሽሎና የፖለቲካ ምህዳሩ ለሁሉም ዜጎች ተመቻችቶና ከሁሉም በላይ ደግሞ በተሳካ ብሔራዊ መግባባት የታጀበ የተሳካ ብሔራዊ ምርጫ እንድናካሄድ አጥብቀን እየጠየቅን፤ ኦፌኮ ለዜጎቿ ሁሉ የምትሆን ኢትዮጵያ እንድትፈጠር በሚደረገው ሠላማዊ ትግል ጎን በፅናት የሚቆም መሆኑን ዳግም እያረጋገጠ፤ የኢትዮጵያ ሐቀኛ ዴሞክራሲያን ኃይሎች እና የተረጋጋች አገር እንዲትፈጠር የምትመኙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ተገቢውን ድጋፍ እንድትሰጡን በአክብሮት ጥሪ እናደርጋለን፡፡

መጪው ጊዜ የነፃነት ጊዜ ነው!

እናመሰግናለን!

የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ

ፊንፊኔ፤ የካቲት 23/2013

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
The National Movement of Amhara(NaMA) Denounces International Violations of the Sovereignty of Ethiopia
ሰሜን ሸዋ በ2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ወጭ የሲሚንቶ ኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ ሊገነባ ነው፡፡
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2