Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የተከዜ የኃይል ማመንጫ ዩኒቶች ምንም ዓይነት ጥገና ሳይፈልጉ ወደሥራ መግባታቸው ተገለጸ
News

የተከዜ የኃይል ማመንጫ ዩኒቶች ምንም ዓይነት ጥገና ሳይፈልጉ ወደሥራ መግባታቸው ተገለጸ

Ethioreview newsEthioreview news—April 10, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የተከዜ ኃይል ማመንጫ ሁለቱ ዩኒቶች ምንም ዓይነት ጥገና ሳይፈልጉ ወደ ሥራ መግባታቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን አስታወቁ። ከዚህ በፊትም ግድቡ ተመቷል ፣ ከዚህ በኋላ አገልግሎት አይሰጥም ሲባል የነበረው ሐሰት መሆኑንም አመለከቱ።

አቶ ሞገስ በተለይም ለአዲስ ዘመን እንዳስ ታወቁት፣ የተከዜ ኃይል ማመንጫ ከዚህ ቀደም ኃይል ማመንጨት ቢችል ማስተላለፍ የሚያስችል መስመር ስላልተዘረጋለት ኃይልን ማመንጨት አቁሞና ለወራትም ያለ ሥራ ተቀምጦ ነበር ፤ አሁን ላይ ግን ካሉት አራት ዩኒቶች ሁለቱ በሙሉ አቅማቸው አገልግሎትን እየሰጡ ነው።ሁለት ዩኒቶች በሳምንቱ መጀመሪያ ተንቀሳቅሰዋል፤ በእነሱም እስከ 108 ሜጋዋት የሚደርስ ኃይል ይዞ ሠርቷል። ሁለቱ ዩኒቶችም ወደ ሥራ ያልገቡት የኃይል ፍላጎቱን ታሳቢ በማድረግ እንጂ ሌላ ችግር ኖሮባቸው አይደለም።

ዩኒቶቹ ስለሚሠሩ ብቻ ወደ ተግባር አይገቡም። ከትላንት በስቲያ ሁለቱን ዩኒቶች ሥራ ስናስጀምር የተጠቀምነው 7 ሰዓት ከ 18 ደቂቃ ሲሆን፤ እስከ 12 ሰዓትም አንዱ ዩኒት ብቻ እንዲሠራ የሆነው፤ ከ 12 ሰዓት ጀምሮ ደግሞ ሁለተኛው ዩኒት እንዲሠራ ሆኗል፤ በመሆኑም የኃይል ፍላጎቱ እየታየ ሁሉም ወደሥራ የሚገቡበት ሁኔታ ይፈጠራል ብለዋል።የኃይል ማመንጫዎቻችን ልክ እንደ ማሰራጫ መስመር አካባቢን ሳይሆን ሁሉንም የአገሪቱን ክፍል ነው የሚያገለግሉት፤ አሁን ለጊዜው የተከዜ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያልፍበት መስመር ጉዳት ደርሶበት ስለነበርና መጠገን ያለባቸውም መስመሮች ተጠግነው እስከሚጠናቀቁ ትግራይ ላይ ብቻ አገልግሎቱን እየሰጠ መሆኑን አስታውቀዋል።

የተከዜ የኃይል ማመንጫ ምንም ዓይነት የተለየ ሥራ አልተሠራበትም ከዚህ በፊትም ግድቡ ተመቷል፣ ከዚህ በኋላ አገልግሎት አይሰጥም ሲባል የነበረው ሐሰት መሆኑን መለከቱት አቶ ሞገስ ፤ እንደውም በወቅቱ የክረምቱ ዝናብ ጥሩ ስለነበር ኃይል ማመንጫው በውሃ ተሞልቶ ነበረ ፤በዚያ ላይ ደግሞ ካሉት አራት ዩኒቶች መካከል አንዱ የጥገና ሥራ ላይ ስለነበር ሙሉ ኃይሉን እንኳን ቢጠቀም አቅሙ የሚቀንስበት ደረጃ ላይ አልነበረም ብለዋል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

እንደ አቶ ሞገስ ገለጻ፣ ኃይል ማመንጫው ላይ ምንም የተከሰተ ጉዳት ባለመኖሩ ከወራት ቆይታ በኋላ ወደ ስር ሲገባ ያስወጣው ወጪም የለም፤ ከዚያ ይልቅ ትግራይ ክልል ላይ የህግ ማስከበር ሥራው በሚከናወንበት ወቅት በደረሰ ከፍተኛ የሆነ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ውድመት ተቋሙ 240 ሚሊየን ብር ኪሳራ አጋጥሞታል።

ትግራይ ላይ አሁን ለሦስተኛ ጊዜ ሰሞኑን የኃይል መቋረጥ ተከስቷል ያሉት አቶ ሞገስ የዚህን የኃይል መቋረጥ ትክክልኛ ምክንያት ለማወቅ ባለሙያዎች እየሠሩ እንደሆነ አስታውቀዋል።ከተከዜ ወደመቀሌ የሚሄደውን መስመር በመጠገን ኃይል እንዲያመነጭ ማድረግ ተችሏል ፤ ይህ መስመር ባይጠገን ኖሮ የኃይል ማመንጫው መሥራት የሚችል ቢሆንም እንኳን ወደመስመር ማስገባት ወይም ኤሌክትሪክ እንዲያመነጭ ማድረግ አይቻልም ነበር።አሁን ባለው ሁኔታ የኃይል ማመንጫው ራሱን በራሱ እንዲቆጣጠር ሆኖ ለመቀሌና አካባቢው ከተሞች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን አብራርተዋል።

ይህንን ለማድረግም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች ከፍተኛ የሆነ ዋጋ ከፍለዋል ያሉት አቶ ሞገስ፣አንዳንድ ቦታዎች ላይ አሁንም ጭምር የሰላም ስጋት ከመኖሩም በላይ በአነስተኛ ቡድን እየተደራጁ ጥቃት ለመሰንዘር የሚሞክሩ አካላት አሉ፣ ባለሞያዎቻቸው ከእነሱም ጋር ጭምር እየተጋፈጡ ሥራቸውን መሥራታቸውን ጠቁመዋል።የትግራይ ክልል ኤሌክትሪክ መቋረጥን መንግሥት ሆን ብሎ እንዳደረገው አድርጎ የሚናፈሰው ነገር ፍጹም ሐሰት ነው ያሉት አቶ ሞገስ ፣ እንደዚህ ዓይነት ሃሳብ ቢኖር ኖሮ ልክ አንደኛው መስመር እንደተቋረጠ አማራጭ በሚባል ሌላ መስመር ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኝ አይሠራም ነበር ብለዋል።ክልሉ ቀደም ሲል ኃይልን ያገኝ የነበረው አላማጣ።

መሆኒ መቀሌ በሚሄድ መስመር ነበር፤ እሱን መጠገን እስከሚቻል ድረስ የኃይል መቋረጡ ይቆይ ነበር፤ ነገር ግን በሌላ መስመር ቀይሮ ለመሥራት የተደረገው ጥረት ተከዜም ወደ ሥራ እንዲገባ አደርጎታል። ህብረተሰቡም ይህንን በአግባቡ ሊረዳ እንደሚገባም አመልክተዋል።በመሰረተ ልማት ላይ የሚደርስ ጉዳት ማንንም ተጠቃሚ አያደርገም፣ እንደ አገር ሁሉንም የሚጎዳ ከመሆኑም በላይ በአካባቢው ላለ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ከፍተኛ የሆነ ተጽዕኖን የሚያሳድር ነው፤ በመሆኑም ህብረተሰቡ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚደርስን ጉዳት ለሚመለከተው የጸጥታ አካል በማሳወቅ አጥፊዎች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ማድረግ እንደሚያስፈልግም አስታውቀዋ።

እፀገነት አክሊሉ

  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“ዶላር እናወርዳለን” የውጭ አገር ዜጎችን የዝርፊያ ድራማ ፖሊስ አለሳልሶ ይፋ አደረገው
የአዳም የማምረቻ መሳሪያዎች ፋብሪካ 1.9 ቢሊዮን ብር በትኖ መሰብሰብ አልቻለም
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2