Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ቴሌ ብር የሞባይል መገበያያ ዘርፍ ከዓመት በሁዋላ ለውጭ ኩባንያዎች ክፍት ይሆናል
News

ቴሌ ብር የሞባይል መገበያያ ዘርፍ ከዓመት በሁዋላ ለውጭ ኩባንያዎች ክፍት ይሆናል

Ethioreview newsEthioreview news—May 12, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ቴሌ ብር የሞባይል ገንዘብ ማዘዋወር አገልግሎት ፈቃድ ለኢትዮ ቴሌኮም ሲሰጥ ድርጅቱ አቅሙን አጎልብቶ ከውጭ ተቋማት ጋር የመወዳደር ብቃት እንዲያጎለብት መሆኑን ያመለከቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፣ ይህ ለኢትዮ- ቴሌ ኮም ብቻ የተሰጠ እድል ለአንድ አመት ብቻ የሚቆይ መሆኑን ጠቁመዋል ። እድሉን በመጠቀም ኢትዮ ቴሌኮም በጥብቅ ዲሲፕሊን ሥራውን በውጤታማነት መፈጸም እና አቅሙን ማጎልበት እንዳለበት አሳስበዋል።

መንግሥት በቴሌኮም ዘርፍ ሁልጊዜም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም እንደሚያስቀድም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አስታወቁ። ኢትዮ ቴሌኮም ‹‹ቴሌ ብር ››የተሰኘ ለማህበረሰቡ ምቹ እና ሁሉን አካታች የገንዘብ ማስተላለፊያ እና የመገበያያ የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት አስጀመረ።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የሞባይል የክፍያ ሥርዓቱን ትናንት በወዳጅነት አደባባይ በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንዳስታወቁት ፣ኢትዮጵያ በሞባይል ገንዘብ ማዘዋወር አገልግሎት ከዓመታት በፊት መጀመር ሲገባት ባለመጀመሯ ምክንያት ከፍተኛ ኪሳራ ለመቀበል ተገዳለች ።

በሞባይል ገንዘብ ማዘዋወር አገልግሎት ካለው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አንፃር እንዲጀመር ከ10 ዓመት በፊት ለመንግሥት ቀርቦ የነበረ ቢሆንም መንግሥት እንዲጀመር ፍላጎት አለማሳየቱን ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፣ የቴሌኮም ዘርፉ ከሁለት አመት በፊት ለውጪ ባለሀብቶች ክፍት ይሆን ተብሎ ሲወሰን አንዱ እና አከራካሪው ጉዳይ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር እንደነበር አመልክተዋል ።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

እንደ አገር በሞባይል ብር የማዘዋወር አገልግሎትን ስንጀምር ከፍተኛ ዋጋ አስከፍሎናል።በአሁን ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚሰሙ የመገናኛ ብዙኃን ፕሮፖጋንዳዎች በአብዛኛው ከዚህ ጉዳይ ጋር የተያያዙ እንደሆኑ ጠቁመዋል።

የመገናኛ ብዙኃን የፕሮፖጋንዳ ዱላ እንዲያርፍብን የመረጥንበትን ዋናው ምክንያት በቀጥታ ከብሔራዊ ጥቅም ጋር የሚያያዝ ስለሆነ ነው። በአሁኑ ወቅትም በዘርፉ ለመሳተፍ ጥያቄ ላቀረቡ የሞባይል የገንዘብ ዝውውር አለመካተቱን አስታውቀዋል ። በዚህም ሀገሪቱ በትንሹ 500 ሚሊየን ዶላር እንደምታጣ አመልክተዋል ።

በዘርፉ ለመሰማራት ፍላጎት ያላቸው አካል፤ ማወቅ የሚገባቸው ሁሌም ቢሆን መንግስት በቴሌኮም ዘርፉ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም እንደሚያስቀድም ነው ብለዋል።

ቴሌ ብር የሞባይል ገንዘብ ማዘዋወር አገልግሎት ፈቃድ ለኢትዮ ቴሌኮም ሲሰጥ ድርጅቱ አቅሙን አጎልብቶ ከውጭ ተቋማት ጋር የመወዳደር ብቃት እንዲያጎለብት መሆኑን ያመለከቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፣ ይህ ለኢትዮ- ቴሌ ኮም ብቻ የተሰጠ እድል ለአንድ አመት ብቻ የሚቆይ መሆኑን ጠቁመዋል ። እድሉን በመጠቀም ኢትዮ ቴሌኮም በጥብቅ ዲሲፕሊን ሥራውን በውጤታማነት መፈጸም እና አቅሙን ማጎልበት እንዳለበት አሳስበዋል።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ በበኩላቸው፣ኩባንያው ባለፉት 127 ዓመታት ካቀረባቸው አገልግሎቶች ለየት ያለውን የቴሌ ብር አገልግሎት ለደንበኞቹ ማቅረቡን አስታውቀዋል።

የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ለማህበረሰቡ ምቹ እና ሁሉን አካታች የገንዘብ ማስተላለፊያ እና የመገበያያ ዘዴ መሆኑን ያስታወቁት ወይዘሪት ፍሬህይወት ፣ አገልግሎቱን ደንበኞች ስልካቸውን በመጠቀም ብቻ መጠቀም እንደሚችሉ ገልጸዋል። በአገልግሎቱም ገንዘብ መላክ ፣ መቀበልና ግዢ መፈጸም እንደሚችሉም ጠቁመዋል ።

ቴሌ ብር የተሰኘው የክፍያ ስርዓቱት ደንበኞች ጥሪ ብር ወይም ቼክ ሳያስፈልጋቸው ዘርፈ ብዙ ክፍያዎችን እንዲፈፅሙ የሚያደርግ ነው። አገልግሎቱ ጤናማ የገንዘብ ፍሰትን ከመፍጠሩም ባሻገር ቁጠባን በማሳደግ፣ ድህነትን ለመቀነስ ፣ ሥራ ፈጣሪነትንና ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት እንዲሁም ገንዘብ የሚታተምበትን ወጪ በመቀነስ የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እንደሚያሳድገው አስታውቀዋል ።

በፋይናንስ አገልግሎት ዘርፉ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ እና የኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምትደርገው ሽግግር ለማገዝ ሁነኛ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የጠቆሙት ወይዘሪት ፍሬህይወት ፣ አገልግሎቱ ኢትዮ ቴሌኮም ካለው ሰፊ ተደራሽነት አንፃር ትልቅ የሚባል ሚና እንደሚጫወት አመልክተዋል ። በተለይም በውጭ አገር ከሚገኙ ተጠቃሚዎች የሚደረገው የገንዘብ ማስተላለፍ አገልግሎት፣ ለኩባንያውም ሆነ ለአገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ግኝት የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ እንደሆነ ገልጸዋል።

በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ ከ 40 በመቶ እስከ 50 በመቶ ያሕል ጠቅላላ የአገሪቱ ግብይትና የገንዘብ ፍሰት በቴሌ-ብር እንዲከወን መታቀዱን ያመለከቱት ወይዘሪት ፍሬህይወት ፣ መተግበሪያም በአምስት ቋንቋዎች መዘጋጀቱን አስታውቀዋል ።

ታምራት ተስፋዬ

አዲስ ዘመን ግንቦት 4 ቀን 2013 ዓ.ም

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Two Killed In Sudan Rally Over 2019 Protest Killings
“Goitum”- Notorious Ethiopian human trafficker who operated in Libya arrested
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2