Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  እነ እስክንድር ነጋ ለመጪው ምርጫ በእጩነት ተመዝግበው መወዳደር እንደሚችሉ የሰበር ሰሚ ችሎት ወሰነ
News

እነ እስክንድር ነጋ ለመጪው ምርጫ በእጩነት ተመዝግበው መወዳደር እንደሚችሉ የሰበር ሰሚ ችሎት ወሰነ

Ethioreview newsEthioreview news—May 24, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሁለተኛ ሰበር ሰሚ ችሎት የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ አመራሮች እስክንድር ነጋ፣ ስንታየሁ ቸኮል፣ ቀለብ ስዩም እና አስካለ ደመሌ ለፓርቲው በእጩነት ተመዝግበው መወዳደር እንደሚችሉ ውሳኔ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያስተላለፈው ዛሬ ሰኞ ግንቦት 16 በነበረው የችሎት ውሎው ነው። 

ችሎቱ ውሳኔውን የሰጠው የባልደራስ ፓርቲ አመራሮችን በተመለከተ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተላለፈውን እና በስተኋላ ላይም በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጸደቀውን ውሳኔ ውድቅ በማድረግ ነው። የባልደራስ ፓርቲ እነ አቶ እስክንድር ነጋ በመጪው ምርጫ በእጩነት እንዲመዘገቡለት ምርጫ ቦርድን ቢጠይቅም፤ አመራሮቹ በህግ ከለላ ስር ስለሚገኙ ለምርጫ እጩነት መመዝገብ አይችሉም በማለት ቦርዱ ጥያቄውን ሳይቀበለው መቅረቱ ይታወሳል። 

የምርጫ ቦርድን ውሳኔ የተቃወመው ባልደራስ ጉዳዩን ወደ ፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወስዶት ነበር። ጉዳዩን የተመለከተው የከፍተኛው ፍርድ ቤት የምርጫ ቦርድን ውሳኔ በማጽደቁ፤ ባልደራስ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አቤት ብሏል።   

የባልደራስን አቤቱታ በሚያዝያ 29፤ 2013 የተቀበለው የሰበር ሰሚ ችሎት፤ ፓርቲው ያቀረበውን መከራከሪያ መርምሯል። የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅ ላይ ማንኛውም በህግ እና በፍርድ ውሳኔ የመምረጥ መብቱ ያልተገፈፈ ሰው በዕጩነት መቅረብ እንደሚችል መደንገጉን ባልደራስ በአቤቱታው አንስቷል። ድንጋጌው ይህን ቢልም ምርጫ ቦርድ ግን በትርጉም አሳብቦ አዲስ ድንጋጌ በአዋጁ ውስጥ ማካተቱ ተገቢ አይደለም ብሏል።  

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ከዚህ በተጨማሪም የከፍተኛው ፍርድ ቤት እና የምርጫ ቦርድ ውሳኔዎች፤ የተከሰሱ ሰዎች በፍርድ ሂደት ውስጥ ባሉበት ጊዜ ንጹህ ሆኖ የመገመት መብታቸውን (presumption of innocence) በጽኑ የሚጎዳ ነው ሲል ፓርቲው በአቤቱታው ጠቅሷል። ስለሆነም ምርጫ ቦርድ በአራቱ የባልደራስ አባላት ላይ ያስተላለፈው ውሳኔ እና የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአብላጫ ድምፅ የሰጠው ውሳኔ ተሽሮ አባላቱ በዕጩነት እንዲመዘገቡ በማለት ጠይቆ ነበር።

በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሰጠው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ የእጩዎችን ምዝገባ በሚመለከት የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመሆኑ ፓርቲው ይግባኝ የማቅረብ መብት የለውም በማለት ተሟግቷል። በእስር ቤት የሚገኙ እና የዋስትና መብታቸውን የተከለከሉ የፓርቲው አባላት በምርጫ ሂደቱ በነጻነት የመንቀሳቀስ እና ከመራጩ ህዝብ ጋር መገናኘት እንደማይችሉ አገናዝቦ የከፍተኛው ፍርድ ቤት የወሰነው ውሳኔም ተገቢ ነው ብሏል።

የፓርቲው አባላት “በእጩነት ተመዝግበው ቢመረጡ በእስር ቤት እያሉ የመረጣቸውን ህዝብ ማገልገል አይችሉም” መባሉ ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን የሚጋፋ ውሳኔ አይደለም ሲል ምርጫ ቦርድ በምላሹ ላይ ተከራክሯል። በሌላ በኩል ደግሞ የባልደራስ ፓርቲ፤ አራት አባላቱ በእጩነት እንዲመዘገቡ በጠየቀባቸው የምርጫ ክልሎች ላይ፤ ሌሎች እጩዎችን ያስመዘገበ በመሆኑ ጥያቄው አግባብ አይደለም ሲል ምላሽ ሰጥቷል።  

አምስት የሰበር ሰሚ ዳኞች የተሰየሙበት የዛሬው ችሎት፤ በምርጫ አዋጁም ሆነ በህገ መንግስቱ ላይ የዜጎች የመምረጥ ወይም የመመረጥ መብት የሚነፈገው በህግ ወይም በፍርድ ቤት ውሳኔ  ካገኘ በኋላ ነው ብሏል። ስለሆነም በተያዘው ጉዳይ የፓርቲው አመራሮች በህግ የተላለፈባቸው ውሳኔ ባለመኖሩ በእጩነት መመዝገብ ይችላሉ ሲል ፍርድ ቤቱ ወስኗል። አጠቃላይ የምርጫ አላማ የዜጎችን ተሳትፎ ማረጋገጥ ሆኖ ሳለ፤ በህግ ግልጽ ተደንግጎ ባልተቀመጠበት ሁኔታ ምርጫ ቦርድ የፓርቲው አባላት በእጩነት መወዳደር አይችሉም ማለቱ የህግ መሠረት የለውም በማለትም ፍርድ ቤቱ የቦርዱን ውሳኔ ውድቅ አድርጎታል። 

የባልደራስ ፓርቲ አመራሮች አሁን ለእጩነት ለመመዝገብ በጠየቁበት የምርጫ ክልሎች ላይ ሌሎች ተተኪ ተወዳዳሪዎችን ማስመዝገባቸውን በመጥቀስ ምርጫ ቦርድ ያቀረበው ምላሽም እንዲሁ በሰበር ሰሚ ችሎቱ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል። ችሎቱ ለዚህ በምክንያትነት የጠቀሰው፤ ምርጫ ቦርድ ተተኪ እጩዎች ያላቸውን በዝርዝርና በማስረጃ አስደግፎ አለማቅረቡን ነው።

በዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞከራሲ ፓርቲ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተወካዮች በአካል ቀርበው ችሎቱን ተከታትለዋል።

በቅድስት ሙላቱ (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) 


[jetpack_subscription_form show_subscribers_total=”false” button_on_newline=”false” custom_font_size=”16px” custom_border_radius=”0″ custom_border_weight=”1″ custom_padding=”15″ custom_spacing=”10″ submit_button_classes=”” email_field_classes=”” show_only_email_and_button=”true”]
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት እንደምትመረመር አሳሰበች
“የመርዛማ ጋዝ ጦር መሳሪያን መጠቀም እልቂቱንና ጉዳቱን ወራሪ ቅኝ ገዥዎች በጀግኖች አያት ቅደመ አያቶቻችን ላይ በፈፀሙት ጥቃት አሳምረን እናውቀዋለን”
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2