Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ሕወሓትን ተከትለው “በረሀ የወረዱና በሕይወት የሌሉ” ሰዎች ከመንግስት ደሞዝ እየተከፈላቸው ነው
News

ሕወሓትን ተከትለው “በረሀ የወረዱና በሕይወት የሌሉ” ሰዎች ከመንግስት ደሞዝ እየተከፈላቸው ነው

Ethioreview newsEthioreview news—May 20, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

[ዋዜማ ራዲዮ]- ቀድሞ በትግራይ ክልል ስር የነበሩና ጦርነቱን ተከትሎ በአማራ ክልል መተዳደር በጀመሩ አካባቢዎች፣ የመንግሥት ሠራተኞች የደሞዝ አከፋፈል በየደረጃው ያሉ ሃላፊዎችን አላስማማም። ከመንግሥት ደሞዝ እየተከፈላቸው ካሉት ሠራተኞች መካከል በሕይወት የሌሉ፣ ወደ ሥራ ገበታቸው ያልተመለሱ እና ከአማፂው ሕወሓት ጋር ወደ በረሀ ወርደው መንግሥትን እየተዋጉ ነው የተባሉ ይገኙበታል።

በትግራይ ክልል ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ መደበኛው የመንግሥት ሥራ ከሁለት ወራት በላይ ተቋርጦ ነበር። ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር መሰየሙን ተከትሎ የመንግሥት ሠራተኞች ወደ ሥራ ገበታቸው እንዲመለሱ ጥሪ ቀረቧል። አንዳንዶች ወደ ሥራ ሲመለሱ ሌሎች ሕወሓትን ተከትለው “ወደ በረሀ ወርደዋል”። በጦርነቱ ሒደት ቀድሞ በትግራይ ክልል ይተዳደሩ የነበሩ አንዳንድ አካባቢዎችን በኃይል የተቆጣጠረው የአማራ ክልል መንግሥት በያዛቸው አካባቢዎች ላሉ የበላይ አመራሮች (የፖለቲካ ተሿሚዎች) ደሞዝ መክፈል የጀመረው ብዙም ሳይቆይ ነው። ለበታች ሠራተኞች ደግሞ በትግራይ ክልል መንግሥት በኩል ከፌደራሉ መንግሥት በጀት ደሞዛቸው እንዲከፈላቸው ተደርጓል።

ዋዜማ በደቡብ ትግራይ (አሁን በአማራ ክልል እየተዳደረ ያለው) የፋይናንስና አስተዳደር ሠራተኞችን ጠይቃ እንደተረዳችው ማን በሥራ ገበታው ላይ እንዳለና እንደሌለ ተገቢ ቁጥጥር ለማድረግ አስቸጋሪ ሆኗል። በጸጥታ ችግር ምክንያት የተረጋጋ የመንግሥት ሥራ ማካሄድ አለመቻሉ የሠራተኞች ቁጥጥርን አዳጋች አድርጎታል። ክልሉ አሁንም ቀድሞ በነበረው የደሞዝ መክፈያ ሰነድ እየተጠቀመ ነው።

የአላማጣ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ካሳ ረዳ ለዋዜማ ራዲዮ እንደገለጹት ጦርነት ከመቀስቀሱ በፊት የመንግሥት ሠራተኞች ሲከፈላቸው በነበረው የገንዘብ መክፈያ (ፔሮል) ዛሬም (የሚያዚያ ወር መጀመሪያ) በተመሳሳይ መንገድ የፌዴራል መንግሥት እየከፈለ መሆኑን ተናግረዋል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

በራያ ግንባር ጦርነት ሲከፈት አካባቢውን ለቀው የወጡ እና በአሁኑ ወቅት የት እንዳሉ የማይታውቁ የአካባቢ አመራሮች ዛሬም በስማቸው ገንዘቡ ወጥቶ በባንክ ደብተር ቁጥራቸው ገቢ እየተደረገላቸው መሆኑን አቶ ካሳ ለዋዜማ አረጋግጠዋል። ከእነዚህ አመራሮች አንዳንዶቹ ገና በቁጥጥር ስር ያልዋሉ እና ትጥቅ ይዘው የጠፉ አመራሮች መሆናቸውን ከንቲባው ጠቁመዋል።

ከንቲባው እንዳሉት ይህንኑ በተመለከተ ለፌዴራል የገንዘብ ሚኒስቴር ማስተካከያ እንዲያደርግ በተደጋጋሚ መጠየቃቸውን ገልጸው ይሁን እንጂ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እስካሁን ማስተካከል እንዳልቻለ ተናግረዋል።

የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወልደ ትንሳኤ መኮነን በበኩላቸው አላማጣ ከተማን ጨምሮ በባላ፣ ዋጃ እና በሌሎች በዙሪያው በሚገኙ ከተሞች እና ወረዳዎች የሚሰሩ የመንግሥት ሠራተኞችን አስመልክተው በሥራ ገበታቸው የተገኙ እና ያልተገኙ በሚል ለመንግሥት በየወሩ ሪፖርት ቢልኩም የቀድሞው የተከፋዮች ዝርዝር አሁንም አልተስተካከለም።

የአማራ ክልል መንግሥት ደመወዝ የሚከፍለው ለፖለቲካ ተሿሚ የበላይ አመራሮች እንጂ ሁሉም የመንግሥት ሠራተኞች አለመሆኑን የገለጹት አቶ ወልደ ትንሳኤ በአላማጣ እና በዙሪያዋ ባሉ ከተሞች የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ከፌደራል መንግሥት በቀጥታ በትግራይ ክልል በኩል እንደሚከፈላቸው ተናግረዋል።

በአላማጣ ከተማ አስተዳደር፣ በዋጃ ፣ በጥሙጋ እና በባላ ከተሞች በተለያዩ የአመራር ቦታዎች የተመደቡ የሥራ ሀላፊዎችን ደመወዝ የአማራ ክልል መንግሥት እየከፈለ እንደሚገኝም የዞኑ አስተዳደር አስታውቋል።

ቀደም ሲል በጦርነት የደመወዝ ክፍያ ተቋርጦ እንደነበር ያስታወሱት የአላማጣ ከተማ ከንቲባ አቶ ካሳ ረዳ የአማራ ክልል መንግሥት ለሁሉም የመንግሥት ሠራተኞች የሁለት ወር ደመወዝ መክፈሉን እና የሥራ ማስኬጃ በጀት መድቦ ከተማዋ መንቀሳቀስ መጀመሯን ተናግረዋል።

“ በዚያን ወቅት በሥራ ገበታቸው ያልተገኙ የህወሓት አመራሮችን ተከትለው የጠፉ ግለሰቦችን ለይተን ደመወዝ እንዳይከፈል ማድረግ ችለን ነበር ፤ ይሁን እንጂ በፌዴራል መንግሥት እንዲከፈል መመሪያ ሲመጣ ጫካ ገብተው መንግሥትን የሚወጉ የሕወሓት ታጣቂዎች ሳይቀር በባንክ ቁጥራቸው ደመወዛቸውን እንዲያገኙ ሆኗል” ሲሉ አቶ ካሳ ረዳ ተናግረዋል።

ዋዜማ ራዲዮ ይህንኑ በማስመልከት ገንዘብ ሚኒስቴር ምላሽ እንዲሰጣት ጠይቃ ነበር ። የተቋሙ ኮሚኒኬሽን ባለሙያ ገንዘቡ በየወሩ ለትግራይ ክልል ገቢ እንደሚደረግ እና በሥራ ገበታቸው የተገኙትን አጣርቶ ደመወዝ መክፈል ያለበት ክልሉ እንጂ የገንዘብ ሚኒስቴር አይደለም ብለዋል። ስለሆነም የትግራይ ክልል ይህንን ችላ ብሎ በሥራ ገበታቸው ያልተገኙ ሰዎች ደመወዝ እየከፈለ ከሆነ መጠየቅ ያለበት ክልሉ ነው ሲሉ ተናግረዋል ።

የትግራይ ክልል ፕላን እና ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ካሕሳይ ብርሃነ በበኩላቸው ለዋዜማ እንደገለጹት ከህወሓት ታጣቂዎች ጋር ተከትለው ወደ “በረሀ የገቡ እና በሕይወት የሌሉ ሰዎች ሳይቀር ደመወዝ ይከፈላቸዋል” የሚለውን እስካሁን እንደማያውቁና የተባለው እውነት ሆኖ ከተገኘ ግን በየወረዳው ተመድበው ይህንኑ መቆጣጠር የነበረባቸው አመራሮች ተጠያቂ ይሆናሉ ሲሉ አስጠንቅቀዋል። [ዋዜማ ራዲዮ]


  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ እስከታተመ ድረስ ቴዲም ሆነ የተጠቀሱት አካላት ስለሚሰሙት ቁጥር ስፍር የሌላቸው መረጃዎች በአዎንታም ሆነ በአሉታ አልተነፈሱም። ነገሮችን በጥሞና የሚከታተሉ “ቴድሮስ ራሱ ወይም አግባብነት ያላቸው ሃቁን ለህዝብ ለምን አይናገሩም? ህዝብ ሲተራመስ ዝም የሚሉት ለምንድን… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ ግለሰቦች የኋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማህበርን ዓመታዊ እራት ለመታደም ተሰብስበዋል። ከ2600 ባልይ እንግዶች ፊት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ቀዳማዊት እመቤት ሜላኒያ ትራምፕ በክብር መድረኩ ላይ ተቀምጠዋል። ሴሽታው እየተጠበቀ ባለበት ሰዓት ድንገት አዳራሹን… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም አውርደው ብዙም ሳይቆዩ አሁን ወዳሉበት ደረጃ ደረሱ። የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምንት መፈረሙን ተከትሎ ያኮረፉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ፣ ሰሞኑን አሜሪካ መልሳ ልትዋዳጃቸው ማቀዷ ተሰምቷል። ዜናው መልካም ቢሆንም ኢሳያስ ግን አይቀበሉትም የሚል አስተያየት እየተሰጠ ነው።… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድንገተኛ አደጋ ጊዜ እርስ በርስ የሚረዱበትን አዲስ የጋራ መከላከያ ስምምነት ረቂቅ ለማዘጋጀት መስማማታቸውን አስታወቁ። በቆጵሮስ አስተናጋጅነት በተካሄደው የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ላይ የተወሰነው ይህ ውሳኔ፣ አውሮፓ በራሷ የመከላከያ አቅም ላይ እንድትተማመን ለማድረግ የታለመ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የአሜሪካ ኤምባሲ የሰላማዊ የተቃውሞ ጥሪውን ጠምዝዞ የማስጠንቀቂያ መልዕክት አሰራጨ
In 24 hours, Egypt changed its position- Al-Sisi reiterates need for binding legal agreement for GERD
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2