መንግሥት የፋይናንስ ተደራሽነትና አካታችነትን ለማስፋት እየሰራ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ ተናገሩ።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በበኩሉ በምስረታ ላይ የሚገኙ ባንኮች በስድስት ወራት ውስጥ 500 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል እንዲያስመዝግቡ አሳስቧል።
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነጻ አገልግሎት የሚሰጠው ዘምዘም ባንክ ስራ መጀመርን አስመልክቶ አቶ አህመድ ሺዴ ከአገራዊ ለውጡ በኋላ የፋይናንስ ተደራሽነትና አካታችነት ለማስፋት በመሰራት ላይ ነው ብለዋል።
በዚህም ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ለውጡን ተከትሎ በተካሄዱት ሪፎርሞችና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሰጡት አመራር ወደ ሥራ መግባቱን ተናግረዋል።የሙስሊም ማህበረሰብ ሲያነሳው የነበረው በባንኩ ምስረታ ምላሽ ማግኘቱን ሚኒስትሩ አመልክተዋል።
ባንኩ ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነት ከማረጋገጡም በላይ፤ በአገሪቱ ኢኮኖሚ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንከ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ በበኩላቸው የፋይናንስ ተደራሽነትን ለማስፋት በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን የባንኮች አቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ባለፉት ሶስት ዓመታት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ አስተዋጽኦ ያላቸው በርካታ ማሻሻያዎች መደረጋቸውን ጠቁመዋል።በዚህም በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ዘርፍ ለማሳደግ ባንኮች አቅም እንዲያጎለብቱ፣ ከጎረቤት አገሮች ባንኮች ጋር ጠንካራና ተፎካካሪ እንዲሆኑ ለማድረግ ፍላጎት እንዳለ ገዢው አመልክዋል።
በአገሪቱ ያሉ ባንኮች ራሳቸውን በቴክኖሎጂ፣ በሰው ኃይል፣ በመሰረተ ልማትና በካፒታል እንዲያሳድጉ አሳስበዋል።በአገሪቱ የፋይናንስ ተደራሽነበት በዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና በተለይ በገጠር ተደራሽነቱን ለማሻሻል እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የፋይናንስ ተደራሽነት ለማስፋት ባንኮች በአቅምም ሆነ በብዛት ወደ ኢኮኖሚው ለማስገባት ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከወለድ ነጻ ባንኮች እንዲፈጠሩ በሰጡት አቅጣጫ መሰረት ባንኩ በተለይ የፋይናንስ አገልግሎት ባልተዳረሰባቸው የገጠር አካባቢዎች ለማደረስ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ባንኩ በተለይ በእምነት ምክንያት የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚ ያልሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ እምነታቸውን መሆኑን ዶክተር ይናገር ገልጸዋል።በአገሪቱ በምስረታ ላይ የሚገኙ ባንኮች በስድስት ወራት ውስጥ የተፈቀደ ካፒታላቸው መጠን 500 ሚሊዮን ብር አድርገው እንዲመዘገቡ ገዢው አሳስበዋል።
ይህንን ካፒታል ካላሟሉ ግን መመስረቻ ካፒታላቸው አምስት ቢሊዮን ብር እንደሚሆን ገልጸዋል።በአሁኑ ወቅት በምስረታ ላይ የሚገኙት 16 ያህል ባንኮች መስፈርቶችን በሟሟላት ወደ ሥራ እንዲገቡ ዶክተር ይናገር አስገንዝበዋል።
የዘምዘም ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ መሊካ በድሪ እንዳሉት ባንኩ በአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ አስተዋጽኦ ለመወጣትና አማራጭ የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመ ነው።በ876 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታልና 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የአክሲዮን ሽያጭ ያካሄደ ሲሆን፤ 11 ሺህ ባለ አክሲዮኖች አሉት ብለዋል።የሸሪያ ህግን የተከተለና ሁሉን አቀፍ የባንክ አገልገሎት በመስጠት በኢኮኖሚ ውስጥ ድርሻውን ለመወጣት እንደሚሰራም ወይዘሮ መሊካ ተናግረዋል።(ኢዜአ)
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






