የግብጽ ተንታኞች ስለ ኢትዮጵያ አየር ሃይል ያቀረቡትን ትንተና ኡስታዝ ጀማል እንደሚከተለው ያቀረበውን እንዳለ ለጥፈነዋል።
ይሄው ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያን የአየር ሃይል ብቃት በዝርዝር እየተነተኑ ነው!!!!
ግብፃዊ የጦር ተንታኝ የኢትዮጵያን አየር ሃይል ከአመሰራረቱ ጀምሮ እስከዛሬ ያለውን ብቃት በአረብኛ ፕሮግራማቸው ላይ አንድ በአንድ እያነሳ ገለፃ እየሰጠ ነው!!!!
ዝርዝር ትርጉሙን ወንድማችን ኡስታዝ ጀማል አቀረበው!!!! በጣም ደነቀኝ!!!! ስገረም አመሸሁ!!!! ለውድ ኢትዮጵያውያን ላካፍላችሁም ወደድኩ::
.
ግብፃዊው ተንታኝ ንግግሩን የሚጀምረው እንዲህ ብሎ ነው
ስለ ኢትዮጵያ አየር ሃይል ብቃት የማታውቁትን ላስታውቃችሁ ብሎ ነው:: ይቀጥልና
የአስዋንን ግድብ የሚያሰጋው የኢትዮጵያ አየር ሃይልን ብቃት ላስቃኛችሁ ይልና
በኢትዮጵያ እና በግብፅ መካከል ያለው ግንኙነት ተበላሽቶ ውጥረት ነግሶና መሪወቹ ዛቻ እየተቀያየሩ ባሉበት በዚህ ወቅት
ግብፅ ውስጥ ያለውን አስዋን ግድብን የሚሰጋው ጉዳይ የኢትዮጵያ አየር ሃይልን ብቃት ነው:: በማለት ወደ ዝርዝሩ ይገባል:: ንግግሩ በስጋት ተጀምሮ በስጋት ያልቃል::
ግብፃዊው ተንታኝ ከተናገራቸው ንግግሮች መሃል የኢትዮጵያ አየር ሃይል በዓፄ ኃ/ስላሴ ዘመን በ1929 እንደተመሰረተ
ከ1929-1936 ኢትዮጵያ 19 የጦር አውሮፕላኖች እንደነበራት
ጣልያንን ካስወጣች በኃላ በ1944 አየር ሃይሏን ዳግም እንዳደራጀች እና የአየር ሃይል ማሰልጠኛ ተቋም እንደከፈተች
የተወሰኑ አውሮፕላኖች/ጀቶች እና መምህሮችን ከፈረንሳይ እና ከአሜሪካ እንዳገኘች
ከዚያም ማሰልጠኛ ተቋሟን አስፋፍታ 75 ቶፕ ሰልጣኞችን እንዳስመረቀች
በ1957 ከስዊዝ ሃገር ኤፍ-83 የሚባሉ 3 የጦር አውሮፕላኖች/ጄቶችን እንዳገኘችና ይህም በወቅቱ ቤስት የሚባል እንደነበር
በ1965-70 አሜሪካ ለኢትዮጵያ F-5ES የተሰኘ ሚሳኤል የሚተፋ ጄት እንደሰጠች
በጂሚ ካርተር ጊዜ ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ግንኙነታቸው ተቋርጦ አሜሪካ ፊቷን እንዳዞረች
ከዚያም ኢትዮጵያ ከቀድሞ ወዳጇ ራሽያ ጋር ግንኙነቷን እንደቀጠለች
ራሽያም በወቅቱ አሉ የሚባሉ ሚግ 23 ሚግ 21 ሚግ 17 የሚባሉ ተዋጊ ጀቶችን ሰጠቻት
በነዚህ ጄቶች እና በነበራት የአየር ሃይል ብቃት የሱማሊያ ጦርነትን ኢትዮጵያ በድል እንደተወጣች
ከዚያም ቀጥላ ኢትዮጵያ የአየር ሃይሏን በሚገባ እንዳደራጀች
በተለይ F 16 : ሚግ 23 : ሚግ 27 : SU 25 ሱ 30 እና SU 27 ፍላንከር በሚባሉ ራሽያ ሰር ተዋጊ ጄቶች ራሷን እንዳስታጠቀች
እነዚህን ጄቶች ራሽያ የሰራቻቸው አሜሪካንን ለመግጠም እንደነበር
ከነዚህም ውስጥ SU 27 ፍላንከር ጄቶች ከየትኛውም ጄት በላይ በአናትህ ላይ ሆኖ መብረር የሚችሉ መሆኑን
አንዱ SU 27 ፍላንከር ጄት ለግጥሚያ ሲወጣ ስምንት ሚሳኤሎችን: RBK መትረየሶችን እና ረዥም እና አጭር ተምዘግዛጊ አረሮችን የመሸከም ብቃት እንዳለው
በአንድ ሰዓት ውስጥ 3530 ኪ.ሜ እንደሚያቋርጥ
የጄቱ ክብደት 30,450 ኪሎ ግራም ሲሆን
9400 ኪሎ ግራም መሳሪያ መጫን እንደሚችል በዝርዝር ይተነትናል::
አክሎም ራሽያ ሰራሽ Mil Mi 24 የተሰኙ ስምንት ሰው መጫን የሚችሉ አደገኛ ተዋጊ ሄሊኮፕተሮች አሏት ይላል::
በዚያ ላይ ሚግ 23 አላት::
ሶቪየት ሰራሹ ሚግ 23 ከእይታ ውጭ (beyond-visual-range) የሆኑ ሚሳይሎችን የታጠቀ ነው:: ወዘተ:: እያለ በስጋት ይተነትናል::
ከዚያም አለ የስጋት ተንታኙ….
ኢትዮጵያ በዚህ ወቅት በአጠቃላይ ከ 92 በላይ የጦር ጄቶች እና አውሮፕላኖች እንዳሏትና ከነዚህም ውስጥ
24 ተዋጊ :20 መለማመጃ: 9 ማጓጓዣ : 33 የጦር ተዋጊ ሄሊኮፕተር: 8 አጥቂ ልዩ አንቶኖቭ አውሮፕላኖች ወዘተ እንዳላት ያትታል:: (የማያውቀው እንዳለ ሆኖ)::
በዚህም ሳቢያ ይላል የግብፁ ተንታኝ
በዚህ አቅሟ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ 4ኛ ደረጃን ይዛለች:: ይህ ትልቅ አቅም ነው::
ያሏት ጄቶች እጅግ አደገኛ ናቸው::
የ SU 27 ጄቶች ባለቤት ናት::
NATO (ኔቶ) ይህ ራሽያ ሰራሹን SU 27ን አይወደውም:: ኔቶ በግልፅ አስቀምጦታል::
በሰዓት ከ2500 ኪሜ እስከ 3530 ኪ.ሜ ይምዘገዘጋል::
ከኢትዮጵያ ግብፅ 2237 ኪሜ ብቻ ነው::
ይህም ከኢትዮጵያ ተነስቶ ግብፅ ለመድረስ አንድ ሰዓት አይወስድበትም ማለት ነው::
አስዋን የተሰራበት አቅም SU 27 በሚተፋቸው ሚሳኤሎች የመፍረስ እድል አለው::
በአንፃሩ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በጄት ድብደባ እንደማይፈርስ አዋቂዎች አረጋግጠዋል::
እንግዲህ በዚህ ስሌቱ ነው የግብፁ ተንታኝ
አስዋን ግድብን የሚያሰጋው የኢትዮጵያ የአየር ሃይል ብቃት እያለ በስጋት ተውጦ ሲተነትን ያመሸው::
ታላቅ ምስጋና ለጀግናው አየር ሃይላችን!!!!!
ታላቅ ምስጋና ለጀግናው የመከላከያ ሃይላችን!!!!
ግብፃዊያኑ እንዲህ ተጨንቀው ቢተነትኑም….
እኛ ግን ሰላም እና እድገት ፈላጊዎች ነን!!!!
ማንንም ለመጉዳት አስበንም ተመኝተንም አናውቅም!!!!
በሰው ጉዳይ እንፈትፍት ያልንበት ታሪክም የለንም!!
ሃይላችን እና ትምክህታችንም ፈጣሪ ነው!!!!
ፈጣሪ ደግሞ የእውነት እና የፍትህ አምላክ ነው!!!!
ፈጣሪ ከኢትዮጵያ ጋር ነው!!!!!
ሃይሉን እና ጥበቡን
ማሸነፍና ድሉን እሱ ይሰጠናል!!!!
ውዶቹ የኢትዮጵያ ልጆችም ለእናት ሃገራቸው ክብር እና ጥቅም ነፍሳቸውን ለመስጠት ሳስተው አያውቁም!!!!
ጠላትን በአንድነት ሆነው ይገጥማሉ!!!!!
ያሸንፉማል!!!!
በውጭ ጠላት ተንበርክከው በፍፁም አያውቁም!!!!!
ልባችንም…ታሪካችንም… እውነታችንም ይሄው ነው!!!!
ሁሌም ድሉ የእኛ
ክብሩ የፈጣሪ ነው!!!!!!
#Ethiopia ሼር ይደረግ!!!!
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






