አሜሪካ በትግራይ ክልል ያለው ችግር እንዲረጋጋ ፍላጎት እንደሌላትና በተቃራኒ ችግሩ እንዲባባስ እያደረገች ነው ስትል ኤርትራ ወቀሳ መሰንዘሯ ተሰምቷል፡፡
የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ትላንት ሰኞ በላከው ደብዳቤ ደብዳቤ እንደገለጸው የባይደን አስተዳደር በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳይረጋጋ ፍላጎት እንደሌለው መግለጹ ተዘግቧል፡፡
ለዚህም አሜሪካ ላለፉት 20 ዓመታት ለአሸባሪው ህወሃት ቡድን ስታደርግ የነበረውን ድጋፍ በማስታወስ ለችግሩ መከሰት ኤርትራን ተጠያቂ ማድረግም መሰረት የሌለው እንደሆነ ገልጿል፡፡የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳልህ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የጻፉት ደብዳቤ አሜሪካ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ላይ በምታደርገው ጣልቃ ገብነትና እየፈጠረች ባለችው ያልተገባ ጫና ተጨማሪ ችግር እንዲፈጠር እያደረገች መሆኑንና ችግሩ እንዳይቀረፍ እንቅፋት እየሆነች እንደሆነ የሚገልጽ ይዘት ያለው መሆኑን በዘገባው ተገልጿል፡፡
በተጨማሪም ኤርትራ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በላከችው ደብዳቤ ላይ አሜሪካ የሽብር ቡድኑ ቀደሞ ወደ ነበረበት ስልጣን ለመመለስ ፍላጎት እንዳላትም መግለጹ ተነግሯል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኦስማን ሳልህ የህወሃት ቡድን አሁን ሀገሪቱን እያስተዳደረ ያለውን የዶ/ር አብይ አስተዳደርን በዓለም አቀፉ ማህበረሰቡ ዘንድ አሉታዊ ገጽታ እንዲይዝ የሚያደርጉ የተዛቡ መረጃዎችን በማሰራጨት መወጠሩን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትም ፍትህን ማረጋገጥ የሚያስችሉ እርምጃዎች መውሰድ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡
ሚኒስትሩ አክለውም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ሰሞኑን በኢትዮጵያና በኤርትራ ባለስልጣናት እና በወታደራዊ ሀላፊዎች ላይ የጣለውን የጉዞ ዕገዳ በተመለከተም ተገቢነት የጎደለው እና በሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ የመግባት አንዱ ማሳያ ሲሉ መተቸታቸውን አልጀዚራ በዘገባው አስነብቧል፡፡
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






