ወደ አማራ ክልልና ትግራይ በመግባት ሁለቱም አካላት ለትግራይ ስጋት በማይሆኑበት ደረጃ እስኪደርሱ ጥቃት እንደሚሰነዝር ሲያስፈርራራ የነበረው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ትህነግ ባስቸኳይና ሙሉ በሙሉ ተኩስ እንዲያቆም ታዘዘ። ግንባሩ ጥቃት ለማድረስ በዛተው መሰረት በማድመ ሽራሮና ኮረም ጥቃት ለመክሰት ሞክሮ የፈለገው እንዳልሆነለት ተገለጸ።
የተባባሩት መንግሥታት ድርጅት ጸጥታው ምክር ቤት “በአስቸኳይ እና ሙሉ በሙሉ” ሲል ትህነግ የተኩስ አቁም እንዲያደርግ ያሳሰበ በይፋ የትግራይን ጉዳይ አንስቶ በተወያየበት ወቅት ነው።
የድርጅቱ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ ሮዝመሪ ዲካርሎ ተጨማሪ ችግር ሊፈጠር እንደሚችል ስጋታቸውን አኑረዋል። አያይዘውም የተካረረ ግጭት ሊነሳ የሚችልበት ሁኔታ አለ።ይህ ደግሞ አሁን ያለውን የጸጥታ አግባ በቅጽበት ወደ ቀውስ ኪቀይረው እንደሚችል አስረድተዋል። ሃላፊዋ ስጋታቸውን ከዘረዘሩ በሁዋላ ነው “የትግራይ መከላከያ ኃይል የተኩስ አቁም ስምምነቱን በአፋጣኝ እና ሙሉ በሙሉ እንዲያጸድቅ እንጠይቃለን” ሲሉ የተደመጡት። ይህን ተከትሎ የትህነግ ሃላፊዎች በይፋ ምን እንደመለሱ አልታወቀም።
ይህን በሚልበት ወቅት አቶ ጌታቸው በተመድ ተሽከርካሪ ሲንቀሳቀሱ የሚያሳዩ ምስሎች በራሱ በተባበሩት መንግስታት የምግብ ድርጅት አስተባባሪ ሲሰራጭ ነበር። ተመድ በቀውስ ቀጠና ውስጥ ገለልተኛ ሆኖ የሚሰራ፣ ያለመነካት መብት ያለው፣ የህግ ከለላው የተጠበቀ ተቋም ሆኖ ሳለ በዚህ መልኩ አንድ ሉዓላዊ አገር ‘ሽብረተኛ” ያለችውን አካል ከላይ በተሰጠው ያለመነካት መብት ጥላ ስር አድርጎ አገልግሎት መስጠት አግባብ እንዳልሆነ፣ ተቋማቱ ገለልተኛ አለመሆናቸውን የሚያሳይ፣ ለወገንተኛነታቸው ገሃድ መውጣት ምስክር እንደሆነ በስፋት በየአቅጣጫው ሲገልጽ ነበር።
ተመድ ከመርሁ በሚጻረር መልኩ እንዲህ ባለ ተራ ተግባር ውስጥ ተነክሮ ከስፍራው የኢትዮጵያን መንግስት የሚደበድብ ሪፖርት ከስፍራው ሲደርሰው የሚያትምና እውነት ነው ብሎ ዓለም እንዲስት የራሱን ሚና የሚጫወት መሆኑ በበርካቶች በቲዊት እየተነቀፈ ነው።
ትህነግ የተኩስ አቁም እንዲያደርግ መታዘዙ ይፋ ከመሆኑ በፊት በኮረም ትንኮሳ አድርጎ እንደነበር አቶ ሬድዋን አስታውቀዋል። የኦቻ ሪፖርት ደግሞ ባድመና ሽራሮ ብሎ ባይጠቅስም ውጊያ እንደነበር ማስታወቁ አይዘነጋም።ኤርትራ ይህን አስመልክቶ ያለችው ነገር የለም። የአማራ ክልል ግን ትንኮሳውን እንዳመከነ ተመልክቷል። ከዚያም በላይ ክልሉ የትህነግ ሃይል በጦርነት ምንም ነገር ለማድረግ ከሞከር አጻፋ ለመመለስ በቂ ዝግትና ቁርጠኛነት እንዳለ አመልክቷል።
በተያያዘ ሌላ ዜና የአማራ ልዩ ሃይል አከባቢ ለቅቆ እንደማይወጣ በተባበሩት የኢትዮጵያ አምባሳደር በይፋ አመልክተዋል። በተባበሩት መንግስታት የፕሬስ ኮንፍራንስ ስለወልቃይት ጉዳይ ” የአማራ ሃይል ከምዕራብ ትግራይ” እንደሚወጣ የተጠየቁት በተባበሩት መንግስታት አምባሳደር ታዬ ስለአካባቢው ከፖለቲካው በላይ በቂ እውቀት እንዳላቸው ለማመላከት እንደ አጋጣሚ በእናታቸው ወገን የወልቃይት አከባቢ ተወላጅ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ደጋግማ ለወተወተቻቸው ጠያቂ “አከባቢው በትግራይ ክልል ስር የተጠቃለለው ህወሓት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ ነው። ይህም የሆነው ያለ ምንም ህጋዊ መሠረት እና የህዝብ ፍቃድ ነው። በመሆኑም የአከባቢው ነዋሪዎች ያነሱት የማንነት እና የወሰን ጥያቄ በህጋዊ መንገድ መፍትሄ እስከሚሰጠው ድረስ የአማራ ልዩ ሃይል ሆነ የመከላከያ ሰራዊት ከወልቃይት አከባቢ ለቅቆ አይወጣም። ይኸው ነው” ብለዋል። አምባሳደሩ ለጸጥታው ምክር ቤት የተዋጣለት ንግግር ማድረጋቸው በርካቶችን አስደስቷል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






