” የሰማ ዕረፍት” ሲሉ የትህነግ ሃይል የገደላቸውን ወገኖቻቸውን ምስል ይዘዋል። ህጻናት የተፈናቀሉ ስደተኞች ቢሆኑም የዓለሙ የስደተኞች ድርጅት አንዳችም ድጋፍ እንዳላደረገላቸው በጽሁፍ ያሳያሉ። ስደተኞች እንጂ ወንጀለኞች አለመሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት እንዲያይላቸው፣ እዲሰማ ደጁ ቆመዋል። የኤርትራ ተፈናቃይ ሰደተኞች።
አንድ ጠይው ሕጻን ማስክ አድርጋ ” እነዛ በትግራይ ካምፕ ያሉ ባስቸኳይ ወደ ሰላማዊ ስፋር ይዛወሩ” ስትል ትጠይቃለች። ከጎኗ ” እኛ ስደተኞች ነን። እኛም እንደ እናንተ ሰዎች ነን” ትላለች። በርካታ ልብ የሚነኩ መፈክሮች የያዙት የኤርትራ ስደተኞች በተባበሩት መንግስታት ቢሮ ደጅ ቆመው ” የህግ ያለ” ሲሉ ላየ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ቢለኔ ስዩም ” ዓለም ትህነግን ዝም አለው። ለለም፣ ለምን፣ ለምን…?” ሲሉ የጠየቁት ጥያቄ አግባብ መሆኑንን ይረዳል። ግን ለምን የኤርትራ ስደተኞች በዓለሙ የስደተኞች ካምፕ ስር ሆነው ሳለ ይገደላሉ? ይንገላታሉ? ይዘረፋሉ? ይፈናቀላሉ? በሚደርስባቸው ግፍ መጠንስ ስለምን ተቆርቋሪ አጡ? የቢለኔ ስዩም ብቻ ሳይሆን የሁሉም ጥያቄ ነው።

በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞች በትግራይ ክልል ኤርትራዊያን ስደተኞች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና እንግልት በመቃወም ሠላማዊ ሠልፍ ሲያካሂዱ ያነሱት ጥያቄ ይህንኑ ” ለምን ዝም እንባላለን?” የሚለውን ነው። ኤርትራዊያኑ ስደተኞች በአዲስ አበባ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅት መስሪያ ቤት ተገኝተው ላሰሙት ጩኸት የተሰጠው ምላሽ ምን እንደሆነ አልታወቀም።
በኤርትራዊያን ስደተኞች ላይ የሚደረግ ጥቃት ይቁም’፣ ‘ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድምፃችንን ይስማ’፣ እና ሌሎችንም መፈክሮች በመያዝ የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በትግራይ ክልል የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞችን ከሚደርስባቸው ግፍና በደል እንዲታደጋቸውም ጥሪ አቅርበዋል።ስደተኞቹ ከዚህ ቀደም በተለያየ ጊዜ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና ለመንግስታቱ የስደተኞች ድርጅት በደብዳቤና በአካል በመገኘት መልዕክት ብናስተላለፍም ምላሽ አላገኘንም ሲሉ ምሬታቸውን አሰምተዋል።
በትግራይ ክልል በሚገኙ ስደተኞች ላይ ግፍና እንግልቱ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ፣ ስደተኞች እየተገደሉና በየጫካው በሽሽት ላይ ያሉትም ለከፋ ችግር እየተጋለጡ በመሆኑ አፋጣኝ መፍትሄ ይሰጠን ሲሉም ጠይቀዋል።
በሠላማዊ ሠልፉ ላይ አካል ጉዳተኞች፣ ሕፃናትና አዛውንት መሳተፋቸውን ኢዜአ ያተመው ምስል ያስረዳል። አሜሪካ በትናትናው ዕለት የኤርትራ ስደተኞች ጉዳይ እንደሚያሳስባት አምጣ፣ አምጣ ማስታወቋ አይዘነጋም።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ እስከታተመ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድንገተኛ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች ስህተት”… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






