Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  አትለቲክስ ፌዴሬሽ በሙስና ተነክሯል፤ የ30 ሚሊዮን ብር ቼክ ተያዘበት- ባለሪኮርዱ አትሌት በውዝግብ ተመዘገበ
News

አትለቲክስ ፌዴሬሽ በሙስና ተነክሯል፤ የ30 ሚሊዮን ብር ቼክ ተያዘበት- ባለሪኮርዱ አትሌት በውዝግብ ተመዘገበ

Ethioreview newsEthioreview news—July 25, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አትሌቲክስና ኦሊምፒክ ውስጥ ያለው ምዝበራ በውጤት እየተደገፈና ታዋቂ ህዝብ የሚያከብራቸውን አትሌቶች ተገን እያደረገ የሚፈጸም ነው። ከፊት ለፊት የሚታዩት “ህዝብ የሚያከብራቸው” የሚባሉትን ደፍሮ የሚናገር አለመኖሩ ደግሞ ቁማሩን፣ ሌበነቱንና ህገወጥነቱን ይበልጥ እንዲሰፋ አድርጎታል። ” ስመ ጥር” የሚባሉትን የነካ በደቦ የሚዲያ እሩምታ ስለሚወርድበት ዝምታን ይመርጣል። ቀደም ባሉት ዓመታት ኦሊምፒክ የዶላር መገበያያና መመንዘሪያ የግለሰቦች ሱቅ በደረቴ እንደነበር ያታወቃል። ለማስቆም ሲሞከር “ለምን አልዘርፍንም” በሚል ፍርድ ቤት ሄደው ሙግት የገቡም አይን አውጣዎችም አሉ። ወደ ዛሬው ሃሳብ እንለፍ።

ቼክና ክፍያው

ዛሬ የደረሰን መረጃ ማንኛውም አካል ሊያስተባብለው የማይችለው እውነት ነው። ሊመረመር የሚገባው ሃቅ ነው። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለመነሻ ተብሎ የቀረበ. ሌላ ተጨማሪ ክፍያ የሚቀርብበት የአትሌቶች የሆቴል ወጪ ለጊዜው ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲከፍል ጥያቄ ቀርቦለት ” አልፈርምም” ሲል ቼኩን ይዞታል።

ቀደም ሲል አትሌቶች ያረፉት በጥሩነሽ ዲባባና ስለሺ ስህን ሆቴል በቀን 17 ዶላር ሂሳብ ነበር። በኮቪድ ምክንያት አትሌቶች ከልምምድ ስለራቁ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ትዕዛዝ አስቀድመው ሆቴል የገቡት አትሌቶች ምንጩና በውል ባልታወቀ ምክንያት ወደ ኔክሰስ ሆቴል እንዲዛወሩ ተደርጓል።

More stories

የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚጥሰው HR6600/S3199 ሕግ ተቋረጠ

April 6, 2022

አጫጭር ወቅታዊ መረጃዎች

June 30, 2021

የብረት ሌባ “ባለሃብቶች” – ነዳጅ ስር የሚርመጠመጡ ባለስልጣናት

December 20, 2022

“ጥምቀትና መተጫጨት”

January 18, 2023

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር /ትህነግ ከፈጠራቸው ልማታዊ ባለሃብቶች መካከል እንደሆኑ የሚነገርልቃቸው ትልቅ ሰው ከአቶ ዳዊት ላይ በ850 ሚሊዮን እንደገዙት የሚነገርለት ኔክሰስ ሆቴል በምን ዓይነት ጨረታ፣ ውልና የተለየ ድርድር አትሌቶቹን ለማሳደር እንደተስማማ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አያውቅም። አልተጠየቀም። በሃስብ ደረጃም አልተነገረውም። ነገር ግን ሆቴሉን በቅርብ ጊዜ የገዙት ወ/ሮ ትልቅ ሰው የአትሌቲክስ ፌዴሬሽ ስራ አስፈሳሚ ናቸው። ይህ ድንግዝግዝ ውል እሳቸው ሆቴሉን ከምግዛታቸው በፊት የተፈጸመ ቢሆንም፣ ከአቶ ዳዊት ላይ ሆቴሉን ለመግዛት ረዥም ጊዜ ግንኙነት ያደርጉና ይደራደሩ ስለነበር በአትሌቲክስ ስራ አስፈጻሚነታቸው አትሌቶቹ ከእነ ስለሺ ሆቴል እንዲወጡ እንደ ደራርቱን ከጸሃፊው ጋር ሆነው እንደተመዘዙ የሚናገሩ አሉ።

አትሌቶቹ በቀን በሰው 17 ዶላር ሂሳብእየተከፈለ ልምምዳቸውን ሲያደርጉበት ከነበረው ሆቴል፣ ለነጠላ 40፣ ለሁለት አልጋ 60 ዶላር እንዲከፈል ተደርጎ የተደረሰው ስምምነት ማን፣ እንዴትና ለምን እንዳደረገው አይታወቅም። ማብራሪያም አልቀረበበትም። ማብራሪያ ሲጠየቅ ወደ ሚቀርቧቸው ሚዲያዎች በመሮጥ ከጉዳዩ ጋር ያልተያያዘ ለቅሶ ለማሰማት መታቀዱን ስለ ጉዳዩ የሚያውቁ ነግረውናል።

በኦሊምፒክ ወቅት አትሌቶችን ማዘጋጀትና ለኦሊምፒክ ኮሚቴ ማሳውቅ፣ ለኦሊምፒክ ኮሚቴ አሳውቆ ቴክኒክ ስራውን በጋር መስራት ከትሌቲክስ ፌዴሬሽን የሚጠበቅ ቢሆንም፣ ፌዴሬሽኑ ከተሰጠው ማንዴት እላፊ ሄዶ ውል መፈጸሙ ከአሰራር አንጻር ህገወጥ ብቻ ሳይሆን የሚያስጠይቅ ነው። የፌዴሬሽኑ ሊቀመንበር ሻለቃ ደራርቱ ቱሉ ከመንግስት አሰራር ውጪ ይህ ውስኔ ማሳለፏ ያስጠይቃታል። ተጠቅመውባት ከሆነም ግልጽ ምላሽ ልትሰጥበት ይገባል።

ለዚህም ይመስላል ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከኔክሰስ ሆቴል የቀረበለትን ከሰላሳ ሚሊዮን ብር በላይ የመጀመሪያ ክፍያ ቼክ ” አልፈርምም” ብሎ ኦዲት እንዲደረግ የመራው። ” ኦዲት ካልተደረገ አንከፍልም” በሚል የቀረበው የክፍያ ጥያቄ ለጊዜው መያዙን ኢትዮ12 አጣርቷሎ። ወደፊት ዘርዝሩን እንመለስበታለን።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወይም ሻለቃ ደራርቱ ቱሉ በዚህ ጉዳይ ላይ ግልጽ መመሪያ ቢሰጡ ይመረጣል። ወይም ለዝግጅት ክፍላችን ምላሽ ካላቸው ሊያደርሱን ይችላሉ።

የኔክሰስ ሆቴል ባለቤት ትልቅ ሰው የሚባሉት ወይዘሮ ጋር ስለ ጉዳዩ ለመጠየቅ ሞክረን አልተሳካልንም። እሳቸውም የሚሉት ካለ ዝግጅት ክፍሉን ማግኘት ይችላሉ።

Girma’s one-year journey from unknown runner to global medallist

Lamecha Girma picks a up a victory in the 3000m SC men. The Ethopian athlete ran a new WL of 8:07.75 🔥#HerculisEBS #MonacoDL
📸: @DanVernonPhoto pic.twitter.com/zIdP7O4mWj

— Herculis (@MeetingHerculis) July 9, 2021
ለሜቻ ዋጋ የለህም በተባለ በሳምንቱ ሪኮርድ ሰብሮ ሲያሸንፍ

ለሜቻ ግርማ የአንድ ዓመት ጉዞ ከጓዳ አውጥቶ ወደ ዓለም ዓቀፍ ታዋቂነት፣ ብሎም ሜዳሊስት የበቃ ተዓምረኛ አትሌት ስለመሆኑ የዎርልድ አትሌቲክስ ዘገባ ያረጋገጠለት የአርሲ ልጅ ነው።

ይህ ምርጥ አትሌት ጉዞውን በ2018 በ1500 ሜትር የኢትዮጵያ ሻምፒዮና አሃዱ አለ። ከዛም ተክለ ሰውነቱ ለ3000 ሜትር መሰናክል የሰጠ መሆኑንን የተረዱት አስልጣኙ ከፍያለው በሰጡት ምክር ወደ ተባለው እርቀት ተዛውሮ ልምምድ መስራት ጀመረ። በዓለም ሻምፒዮና የነሃስ ሜዳሊያ አገኘ።

ይህ ድንቅ ልጅ ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ብቁ እንዳልሆነ አትሌቲክስ ፌዴረሽን ውስጥ ከነዱቤ ጋር የኖሩት፣ በግል የተወሰኑ አትሌቶች አጫዋችና አገልጋይ እንደሆኑ የሚታሙት ዶክተር አያሌው ወሰኑ። ሃኪም ናቸውና ” አይመጥንም ” ብለው መሰከሩበት። በእሳቸው ሙያዊ ውሳኔ ለሜቻ ከቶኪዮ ኦሊምፒክ ልዑካን መካከል ስሙ ተሰረዘ። ለሜቻን የሚያውቁ ሁሉ ጉዳዩ አሳዘናቸው። ነገሩ የገባቸው ሚዲያዎች ቢኖሩም ተሸበቡ።

ይህ በሆነ በሳምነቱ ለሜቻ ሞናኮ ሄዶ በ3000 መሰናክል አዲስ ክብረውሰን አስመዝግቦ ተመለሰ። የዶክተር አያሌውን ” ሙያዊ” ውሳኔ አፈር አስጋጠው። በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ውስጥ እንደ ጉለተኛ እድሚያቸውን የፈጁት ዶክተር አያሌው በዚህ ውሳኔያቸው ሳያፍሩ ” አይመጥንም” ብለው ደረቁና ሃይለማርያም የሚባለው አትሌት እንዲያዝ ምክረ ሃሳብ ለገሱ። በውል ባልታወቀ ምክንያት ለሜቻ ” ዞር በል” ተባለ። ይህ ሲሆን ታዋቂ ነገር ግን አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገለላቸው ሯጮች ውሳኔው አግባብ እንዳልሆነ ቢናገሩም ደራርቱን ጨመሮ ሊሰሙ አልፈለጉም። ለምን? ይህም ምላሽ ያስፈልገዋል።

ከትናት በስቲያ ባገኘነው መረጃ መሰረት በመጨረሻ የአትሌቶች ስም ማስተላለፊያ ቀን ስሙ የተዘለለው ለሜቻ በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴና አኖካና ድጋፍ በከፍተኛ ውዝግብና ምልጃ ከዋናው የባህር መዘገብ ላይ ስሙ ስለሚገኝ በተወዳዳሪነት እንዲያዝ ተደርጓል።

ይህ አትሌት ተገፍቶ፣ አትችልም ተብሎ፣ እንደ ባጣ ቆዩኝ እንዲወዳደር ተደርጎ ውጤት ቢበላሽበት ተጠያቂው ማን ነው? ስማቸውን እንዳንጠስ የተየቁን አሰልጣኞች ” በሚሆነው ሁሉ የምናውቀ ነገር የለም። ጉዳዩ ሆድ ይፈጀው ነው። ከውድድሩ መልስ ማንም ሆነ ምን ውጤቱ መንግስት ዘነድ እንቀርባለን” ብለዋል።

አትሌት ደራርቱ ቱሉን ሽፋን አድርገው ወይም አውቃ ሊሆን ይችላል እነ አቶ ቢልልኝ በርካታ ህገወጥ ተግባር እየፈጸሙ እንደሆነ መረጃ አለ። የፌዴሬሽን ቅጥር ሰራተኛ ሊይዘው የማይገባ የአማተር ሃላፊነት ውስጥ ገብተው ተነክረዋል። ይህ ደራርቱ እያወቀች የሆነ ጉዳይ ነው። አቶ ቢልልኝ ተቀጣሪ የአትሌቲክስ ጽሐፊ ሆነው ሳለ ብመን መስፈርት በአማማተር የሚሰራ ስራ ውስጥ ገቡ? እሳቸው የዳርት ፌዴሬሽን ሊቀመንበር ሲሆኑ የዛሬው ሚኒስትር ” የተከበሩ” ዱቤ ጅሎ እንዴት እውቅና ሰጡ? መመሪያውን ሰማያውቁ? ወይስ እንዴት?

በሌላ ፌዴሬሽን ” አማተር ነኝ” ብሎ መሪ የሆነ ሰው ሻለቃ ደራርቱ ደሞዝ እየከፈለች የምታሰራው ለምንድን ነው? ሻለቃ ደራርቱ ይህን ህግ የመጣስ ስልጣን ከየት አገነች? ወይስ ጮሌዎቹ አሞኟት? ምንም ይሁን ምን ግን ይህ ሊያስወቅሳት እንደሚገባ በርካቶች ይስማማሉ። ሚዲያውም ከተራ ስድብና ውዳሴ ወጥቶ ደንብና መመሪያ በማጣቀስ እዚህ ጉዳይ ላይ ሊሞግት እንደሚገባ አስተያየት እየተሰጠ ነው። በኢትዮጵያ የኦሊምፒክ ቡድን የመክፈቻ ሰነ ስርዓት ላይ ምን እንደሆነ ዝናና ስም ሳይፈራ ማጣራት እንዲደረግ እዛው ያሉ ጠቁመዋል። መመሳቀሉ የተፈጠረው ጭቃ ለመቀባባት ሆን ተብሎ የተሰራ ስለመሆኑ መረጃ ቢኖርም ጉዳዩን በስፍራው ላሉ ጋዜጠኞች መተውን መርጠናል።

በሌላ የአትሌቶች ዜና የመጨረሻ የምርጫ ውድድር ሄንግሎ ውጤት ላይ እንዲመሰረት ከተባለ በሁዋላ ገንዘቤ ዲባባ ” ኮቪድ ይዟታል” በሚል የሃሰት ሪፖርት ለብቻዋ ተወዳድራ ሰዓት እንድታሟላ የተኬደበት አግባ በራሱ ህግን የጣሰ መሆኑ ተጠቅሶ ምላሽ እንዲቀርበበት ሊጠየቅ እንደሚገባ ታዛቢዎች ነግረውናል። ውጤቱ ላይ ጫና ላለማሳደር ቀጣዩን እንመለስበታለን። ሁሉንም እያነሱ ዶክተር አሸብር ላይ መለጠፉ ብቻውን አያዋጣም። እሳቸው ሊጠየቁ በሚገባቸው ጉዳዮች ብቻ መጠየቅ አለባቸው። ከዚህ ውጭ በደቦ ሁሉንም ጉዳይ ወደ አንድ ሰው በመግፋት ወንጀል ውስጥ መደበቅ ሊፈቀድ አይገባም።መፍትሄ አይሆንም።

ደራርቱ ምርጥ የኢትዮጵያ ጀግና ናት። ደራርቱ ብቻ ሳትሆን ብዙ የማይረሱ የስፖርት ጀግኖች አሉ። መለኪያው ሪኮርድ፣ ብዙ ማሸነፍ፣ የሜዳሊያ ብዛት … ነውና ኢትዮጵያን ያኮሩ፣ ለአሸናፊዎች ድጋፍ የሰጡ፣ ያቅማቸውን የሞከሩ፣ ባይሳካም እንደ ችሎታቸው የተሳተፉ ሁሉ በየደረጃው ጀግኖች ናቸው። ጀግና መሆን ግን ማንንም ከምንም በላይ ሊያደርግ አይገባም። ደራርቱ አበጀሽ ተብላ የምትሸለመውን ያህል ልትጠየቅም ይገባል። በነገራችን ላይ የደራርቱ ሽልማት በራሱ ትልቅ አነጋጋሪና ጤነኛ ያልሆኑ ገጽታዎች ያሉት እንደሆነ ዝግጅት ክፍላችን ያምናል። ጀግናዋ ደራርቱ በባርሴሎና እንደ ዋላ ተንሳፋ ያስመዘገበችው ድል የሚረሳ አይደለም። ከእኛ አልፎ የአፍሪካም ነው። ሃይሌስ? ቀነኒሳስ? ፋጡማስ? ጌጤስ? መሰረት ደፋርስ? ጥሩነሻስ? ብረሃኔስ? …. መስፈርቱ ምንድን ነው?፡ወደፌት ይህንንም በዳታና በመረጃ እናየዋለን። ችግሩ ሚዲያው ረጋ ብሎ አለመመርመሩ ነው። ሚዲያው ዝም ብሎ ማመኑና በአመክንዮ ላይ ተመስርቶ አለምስራቱ ነው።


[jetpack_subscription_form show_subscribers_total=”false” button_on_newline=”false” custom_font_size=”16px” custom_border_radius=”0″ custom_border_weight=”1″ custom_border_color=”#ff6900″ custom_padding=”15″ custom_spacing=”10″ submit_button_classes=”has-ff-6900-border-color has-text-color has-accent-font-color has-background has-vivid-cyan-blue-background-color” email_field_classes=”has-ff-6900-border-color” show_only_email_and_button=”true”]
Donate Button with Credit Cards
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ እስከታተመ ድረስ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ ግለሰቦች… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም አውርደው… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድንገተኛ አደጋ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
    ቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች ስህተት” መሆኑን… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ወደ ደብረ ብርሃን፣ ጎንደርና አዲስ አበባ እንደሚያኮበኩብ የገለጸው ትህነግ በርካታ ሰራዊት ተማረከበት፤ ቆቦን ተነጠቀ
በመንግስት የሚሰጡ መግለጫዎች ሁሉ የሚያመለክቱት የትግራይን ህዝብ ሳይሆን ወንጀለኛውን ህወሓት ብቻ ነው– ወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2