አቶ ጌታቸው ረዳ ” ወደ ደብረብርሃን ወይስ ጎንደር” ሲሉ ወዳሻቸው የሽር ሽር ያህል እንደሚያቀኑ ባስታወቁ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ ቆቦን መነተቃቸው ተሰማ። በአፋር ግንባር ከፈተኛ ቁጥር ያላቸው ምልምሎች መማረካቸው ታወቀ።

የአሸባሪው ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው እንዳሉት እሳቸው የሚወክሉት ጦር ወደ ፈለገው አቅጣጫ ለመሄድ የሚገድበው አንዳች ሃይል የለም። መደራደር እንደሚፈልጉ የሚነገርላቸው ጄነራል ጻድቃንም ” ወደ አዲስ አበባ ለመገስገስ የምያግድ አንዳችም ነገር የለም” የሚል ቃለ ምልልስ አድርገዋል።
ዛሬ ረፋዱ ላይ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለቱት ትህነግ ቆቦን ከሙሉ ኪሳራ ጋር ተነጥቋል። በአፋር ግንባር ሰፊ ቦታ የሚሸፍን ጦርነት ለመክፈት ሲያጋግዛቸው የነበሩ ምልምል ወታደሮች ከመኪና ሳይወርዱ ተይዘዋል። ከአካባቢው ምስክሮች መረዳት እንደተቻለው የተያዙት ከመኪና ሳይወርዱ በመሆኑ ” ተማረኩ” ሊባል አይችልም።
ከተማረኩት በተጨማሪ በሺህ የሚቆጠሩ መደምሰሳቸውን በስፍራው ያሉ ምስክሮች ገልጸዋል። የጅቡቲ ባቡርና የየብስ መንገድ እንደሚቆርጡ ከሳምንት በፊት የተነገረላቸው የትግነግ ተዋጊዎች እስካሁን በአፋር ግንባር ይህ ነው የሚባል ማስመዝገባቸውን አልተቆሙም።
የጦርነት መረጃ ሁሉ እንደማይነገር የሚገልጸው መንግስት የመከላከያ ሃይል ከድካምና ከባይተዋርነት አገግሞ ሰንጋ እየበላ ደጀን መካከል ሆኖ መዋጋት ከጀመረ አንስቶ በትህነግ ላይ ከፈተኛ የሚባል ሰባዊ ቀውስ እያደረሰ ነው።
ለደጋፊዎቻቸው ብርታት ሰፊ የፕሮፓጋንዳ ድል ዘመቻ የሚያስተጋቡት የትህነግ ደጋፊዎች በተመሳሳይ ” ትግራይ እያለቅች ነው” የሚል የማህበራዊ ዘመቻ ጀምረዋል። በተመሳሳይ ትህነግ አሸባሪ መሆኑንን የሚያበስር ሎጎ ኢትዮጵያን የሚወዱ ዜጎች እያሰራጩ ነው።
ትህነግ ቆቦን መያዙን ሲያስታውቅ ካሰራጨው ፎቶ በተለይ ቆቦን ስለመነጠቁ ለደጋፊዎቹ ያለው ነገር የለም። በግንኙነት መረጃውን ከመስማት ውጪ መንግስት ቆቦ ስለመያዟም ሆነ ስለመለቀቋ ያለው ነገር የለም። አቶ ተሻገር ዛሬ ባሰሙት የክተት ጥሪ ‘ ስለወታደራዊ ውሎ በዚህ ገባን ወጣን እያልን መናገር አያስፈልግም። ይህን አሸባሪ ግን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እናተፋዋለን ” ማለታቸው ይታወሳል።
መከላከያ አሁን ላይ በትግራይ ክልል ውስጥ ገብቶ መዋጋት ያቆመ ሲሆን የትህነግ ሃይል ሊያተቃ ሲመጣ አፈግፍጎ አመቺ ቦታ ላይ ሲደርሱ በሂሊኮፕተር እያሳደዱ እንደሚመታቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ እስከታተመ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድንገተኛ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች ስህተት”… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






