Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ሔማን በቀለ – ታይም መፅሄት የዓመቱ ምርጥ ያለው ህልመኛ ታዳጊ ሳይንቲስት

    September 4, 2024

    በዩክሬን በኩል ወደ አውሮፓ የሚደርሰው የሩሲያ የተፈጥሮ ጋዝ  ስራው እንዲቆም ተደረገ

    January 1, 2025

    በኦሮሚያ ክልል ማን፣ ምን ፈጸመ? የኢሰመኮ ሪፖርት

    August 5, 2025

    በኦሮሚያ በሌብነት ጉዳይ አናቱ ተፈርቷል፤ በ289 ሺህ ካሬ.ሜ.መሬት ላይ ማጣራት ተጀምሯል

    December 3, 2022

    የአፋር ክልል ከ፴ ዓመታት በሁዋላ በትግራይ ክልል የተወሰደበትን ኣንድ ቀበሌ “ነጻ አ ወጣሁ” አለ

    June 7, 2021
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  POLITICS  አዲስ ዲፕሎማሲ አሁኑኑ!! ” 115 ሚሊዮን ሕዝብ ያላት አገር ባልተገባ ጫና ለማፍረስ መሞከር ቅድሚያ የሚጎዳው ጫና ፈጣሪዎቹን ነው”
POLITICS

አዲስ ዲፕሎማሲ አሁኑኑ!! ” 115 ሚሊዮን ሕዝብ ያላት አገር ባልተገባ ጫና ለማፍረስ መሞከር ቅድሚያ የሚጎዳው ጫና ፈጣሪዎቹን ነው”

Ethioreview newsEthioreview news—July 11, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ስምንት የህዝብ ግንኙነት የሚሰሩላቸው ድርጅቶ ቀጥረዋል። ከለውጡ በፊት በወር አርባ ሺህ ዶላር ይከፍሏቸው ። ከልወጡ በሁዋላ ከ100 እስከ 140 ሺህ ዶላር እንደሚከፍሏቸው መረጃ አለኝ። ይህን ሁሉ ሃብት እያፈሰሱ ነው ኢትዮጵያ ስሟ እንዳየሳ፣ ጉዳይዋ እንዳይሰማ ሁሉንም በሮች የተቆጣጠሩት። ስልጣን ላይ እየሉ ባከማቹት የዘርፊያ ሃብት የህዝብ ግንኙነቱን ስራ በገንዘብ ቆላልፈው ይዘውታል። እኛ ደግሞ ዲፖሎማቶቻችን ብር ከመሰብሰብ ያልፈ ስራ አይሰሩም። በዚህ አካሄድ መቀጠል አይቻልም። ጊዜው የአዲስ አሳብ፣ አሰራርና ትገበራ ነው…

ዶ/ር ሃይማኖት አሰፋ ናደው በትምህርታቸው የፋርማሲ ሳይንስ ባለሙያ ቢሆኑም ፍልስፍና፣ ታሪከ፣ ሳይንስ፣ ባሕል፣ ኪነ ጥበብ ወዘተ ጉዳዮች ላይ ማንበብ፣ ማጥናት እና መመራመር እንደሚወዱ ግል ታሪካቸው ያስረዳል። ከጥቃቅንና አነስተኛ የንግድ አስተዳደር ጀምሮ በዩኒቨርሲቲ በማስተማር፣ በዓለምአቀፍ ልማት፣ በምርምር፣ በማማከር፣ በትርፍ አልባ ድርጅቶች እና በመንግሥታዊ መሥሪያ ቤቶች እስከ አመራር የዘለቀ የሥራ ልምድ ያካበቱ ናቸው።

ዶ/ር ሃይማኖት

ጋሙጎፋ ሳውላ ከተማ ተወልደው ያደጉት ዶክተር ሃይማኖት ለሰው ማሰብ፣ ለሰው መኖር፣ የሰዎችን ስቃይና ችግር መካፈል ካስተዳደጋቸውና ከአካባቢያቸው ማኅበረሰብ እንድተማሩ ይናገራሉ።ምንም እንኳን ኑሯቸው ከአገር ቤት፣ ከሚወዱት ማህበረሰብ ርቆ ቢኖርም በየዕለቱ በአገራቸው ጉዳይ ላይ ከማሰብ ወደኋላ አላልሁም። ይህንኑ ያደጉበትን እሴት በመጠበቀ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ የሚሰጠው አመለካከታቸውን እያራመዱ ነው።

የሁለት ሴት ልጆች አባት የሆነው ሃይማኖት፤ እናታቸው ወ/ሮ ታየች ዘውዴ ወልደሚካኤል የመኖር ምክንያታቸው እንደሆኑ ግለታሪካቸው ላይ በጉልህ አኑረዋል። ኢትዮ 12 አሁን ላይ ” አዲስ አሰራር፣ አዲስ አሳብና አዲስ ዲፖሎማሲ” በሚል በጀመሩት ስራ ዙሪያ እንግዳ አድርገናቸዋል። ዶክተር ሃይማኖት ዜጎች ሁሉ አቅም ያላቸው የአገራቸው አምባሳደር ይሆኑ ዘንዳ የሚያተባበርና የሚመራ Ethiopian Americans Voting Bloc EAPAC Global የሚባል ድረጅት መስረተዋል። ወደ ቃለ ምልልሱ


ኢትዮ 12 – እንደ መነሻ ከዋናው ትኩረት ለመነሳት፣ አሜሪካኖች ሊረዱት የሚገባቸውና የሳቱት፣ እርስዎና ድርጅትዎ አጥበቀው ለማሳወቅ የምትጥሩበት ቁልፍና ከባዱ ጉዳይ ምንድን ነው

ዶ/ር ሃይማኖት – ኢትዮጵያ ላይ አላስፈላጊ ጫና እየተደረገ ነው። ይህ አላስፈላጊ ጫና ኢትዮጵያ ላይ አደጋ ካመጣ የመጀመሪያዋ ጥቅሟን የምታጣ አገር አሜሪካ ናት።፡ኢትዮጵያ 115 ሚሊዮን ህዝብ አላት። ጫናው በዚህ መልኩ ከቀጠለ ኢትዮጵያ ወደ አላስፈለጊ መበትን ልታመራ ትችላለች። ይህ ከሆነ ምስራቅ አፍሪቃ የአክራሪ መናኸሪያ ይሆናል። ሰፊ ቁጥር ያለው ሕዝብ ለስደትና ለሰብአዊ ቀውስ ይዳረጋል። ወደ አውሮፓ የሚሰደደው ስፍር ቁጥር የለውም። በጥቅሉ ማህበራዊ ቀውሱ እጅግ ከፍተኛ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ቀጠናው እንዳለ ይናወጣል። በዚህ ቀውስ ውስጥ አሜሪካንም ሆነች አውሮፓ አንዳች አያተርፉም። ፍላጎታቸም አይሟላም። በተቃራኒው 115 ሚሊዮን ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ ሰላሟ የተረጋገጠና አንድነቷ የተጠበቀ ሲሆን ጥቅማቸው እንደሚከበር ቢያውቁም በቂ መረጃ እንዲሰጣቸው አልተደረገም። ከዚህ አንጻር መሰራት እንዳለበት እናምናለን።

ኢትዮ12 – አሜሪካኖች ኢትዮጵያን መስማት አቁመዋል ይባላል? ለመሆኑ ትገናኛላችሁ? በምን ደረጃ?

More stories

ግደይ እናመሰግናለ! አትሌቲክስ በልዩ ታክስ ፎርስ ይመርመር

August 7, 2021

“የትህነግ ርዝራዦች ኢትዮጵያን ለማዋረድ የሚያደርጉትን ጥረት ለመቀልበስ በቁጭት ተነሳስተናል”አቶ ደስታ ሌዳሞ

July 15, 2021

አል-ሲሲ በቅድመ ሁኔታ ኢትዮጵያን በልማት ማገዝ እንደሚፈልጉ አስታወቁ፣ ለ”ትብብር” ጥሪ አቀረቡ

July 16, 2021

ከሁሉም በላይ ዋናው [ማህበራዊ ትስስሩ መበጠስ] ሬድዋን ሁሴን

November 14, 2022

ዶ/ር ሃይማኖት – እንገናኛለን። ጉዳዩ መስማት የመፈለግና ያለመፈለግ ሳይሆን ችግሩ ያለው ቀድሞ መረጃ ማድረሱ ላይ ነበር። ያገኘናቸው የአሜሪካ ህግ አውጪዎች የመረጃ ችግር እንዳለባቸው ነግረውናል።

ኢትዮ12 – ያስደነግጣል ምን ማለት ነው?

ዶ/ር ሃይማኖት- አያስገርምም ለዓመታት አገራችን የዲፕሎማሲ አቅጣጫዋ ድርጅት ላይ የተቸከለና በመርህ ደረጃ የተቃኘ አልነበረም። ስለዚህ ለውጡ ሲመጣ ለድርጅት ጥቅም የተሰመሰረተው መስመር በተቋቋመለት መስመር ቀጠለ። እንደ አገር ግን ያው እንደታየው ውጤቱ ሽንፈት ሆነ። የመረጃ እጥረቱና ክፍተቱ መነሻው ይህ ነው። ቀደሞ ያልተሰራ ስራ …

ኢትዮ12- የሚቃና ይመስልዎታል?

ዶ/ር ሃይማኖት– በሚገባ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ስንለው የነበረውን ሰምተዋል። መንግስት ሰማ ማለት ነው። ተወደደም ተጠላም ዲፕሎማሲው በህዝብ መሰራት አለበት። ፑብሊክ ዲፕሎማሲ እጅግ ወሳኝ ነው። ከአሁን በሁዋላ የዲፕሎማሲው ስራ የሚሰራው እንደ እኛ ባሉ ድርጅቶችና በጎ ፈቃደኞች ነው። አሁን የሚቀረው ለሃላፊነቱ መዘጋጀት ነው። በቀናነት፣ በታማኝነትና በፍጹም ፈቃደኛነት ከሰራን እንቀይረዋለን። ዋና ጉዳይ አዲስ አሳብ፣ አዲስ አሰራርና አዲስ የትግበራ መንገድ መከተሉ ላይ ነው። በቀድሞው የስህተት መንገድ መጓዝ ለሌላ ስህተት ይዳርጋል እንጂ ወደ ከፍታ አይወስድም። ያለፈው ሽንፈታችን ጥሩ አስተምሮናል።

ኢትዮ12- አሁን ኢትዮጵያ ላይ የተከፈተው ዘመቻ የተደራጀና ማዘዣ ጣቢያ ያለው እንደሆነ እየተነገረ ነው። ታላላቅ የሚባሉ መንግስታት፣ መገናኛዎችና ዓለም ዓቀፍ ተቋማት ሳይቀሩ እየተሳተፉበት ነው። እርስዎ በትክክል ምን ተፈልጎ እንዲህ ያለ ዘመቻ እንደተከፈተ ያውቃሉ? ወይም መረጃ አለዎት?

ዶ/ር ሃይማኖት- መቶ በመቶ የሚያውቁት ዘመቻውን የሚያካሂዱት የጠቀስካቸው ክፍሎች ናቸው። ግን የተጠጋጋ መልስ መስጠት ይቻላል።

ኢትዮ12- መፍትሄ ለመፈለግ ዋናውን ጉዳይ ማወቅ አስፈላጊ እንደሆነ ስለሚታመን ነው ጥያቄውን ያነሳሁት፤

ዶ/ር ሃይማኖት- ትክክል ነው እንዳልኩት እጅግ በተቀራረበ ደረጃ ከዚህ ሁሉ ዘመቻ ያለውን ፍላጎት እንረዳለን።

ኢትዮ12- ይቀጥሉ ዶክተር

ዶ/ር ሃይማኖት– ትህነግ ስምንት የህዝብ ግንኙነት የሚሰሩላቸው ድርጅቶች ቀጥሯል። ከለውጡ በፊት በወር አርባ ሺህ ዶላር ይከፍሏቸው ነበር። ከልወጡ በሁዋላ ከ100 እስከ 140 ሺህ ዶላር እንደሚከፍሏቸው መረጃ አለኝ። ይህን ሁሉ ሃብት እያፈሰሱ ነው ኢትዮጵያ ስሟ እንዳየሳ፣ ጉዳይዋ እንዳይሰማ ሁሉንም በሮች የተቆጣጠሩት። ስልጣን ላይ እየሉ ባከማቹት የዝርፊያ ሃብት የህዝብ ግንኙነቱን ስራ በገንዘብ ቆላልፈው ይዘውታል። እኛ ደግሞ ዲፖሎማቶቻችን ብር ከመሰብሰብ ያለፈ ስራ አይሰሩም። በዚህ አካሄድ መቀጠል አይቻልም። ጊዜው የአዲስ አሳብ፣ አሰራርና ትገበራ ነው የምለው ለዚህ ነው።

ኢትዮ12- አልመለሱልኝም? ደግሞስ በምን እንመን?

ዶ/ር ሃይማኖት- ሲጀመር አሜሪካን አገር በተባለው ስራ ዘርፍ የሚሰሩ ተቋማት ጉዳይ ሚስጢር አይደለም ዳታ አለ። በዚህ ላይ በበቂ መረጃ የተደገፈ ጣናት አድርገን የደረስንበት በርካታ ጉዳዮች አሉ። ይህንን ጉዳይ እንደም ሃይል ሊያስተባብል አይቻለውም። እነዚህ ስምንቱ ተቀጣሪ የህዝብ ግንኙነት ስራ የሚሰሩት ድርጅቶች ከሎቢስት/ ወስዋሾች ከፍ ያሉ ናቸው። በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የፖለቲካ መዋቅ፣ ተቋማትና አስፈለጊ ሰፍራዎች ውስጥ ዘልቀው በመግባት የትህነግን ስራ ይሰራሉ።

ኢትዮ12- ምንድን ነው የሚሰሩላቸው?

ዶ/ር ሃይማኖት- ለአሜሪካ ጥቅም መከበር ትክክለኛ አማራጭ እነሱ መሆናቸውን፣ በተቃራኒ ኢትዮጵያ የአሜሪካንን ጥቅም ማስተበቅ እንደማትችል አድርገው ያሳያሉ። በዚህ መልኩ ፖሊሲ አውጪዎቹም ሆኑ አስፈሳሚዎቹ ከአሜሪካ ጥቅም አንሳር ትህነግን እንዲመርጡ እንዲገደዱ ይሆናል። በዚህ ላይ መሃል ያለው አገር ሰላም ማጣቱ እንኳ የአሜሪካንን የራሱንም ሕዝብ ሰላም ማስከበር የማይችል ደካማ መንግስት ሆኖ እንዲታይ ያደርጋሉ። ጨዋታው መንታ ነው።

ኢትዮ12- ስምንት የህዝብ ግንኙነት የሚሰራ ድርጅት መቅጠር አይበዛም? ወይስ ስምንት የሆኑበት ልዩ ምክንያት አለ?

ዶ/ር ሃይማኖት- ታስቦበት ነው። ልዘርዝርልህ። ለዲሞክራቶች፣ ለሪፐብሊካኖች፣ ለሃይማኖቶች ጥምረት፣ለጥቁር አፍሪካ አሜሪካኖች ጥምረት፣ ለዋይት ሃውስ፣ ለኮንግረንስ፣ Lesbian, Gay, Bisexual and Transgender. q ለሚባሉት ጥምረቶችና ለተቀረው የህብረተሰብ ክፍል በህዝብ ግንኙነት የሚሰሩ የታሰበባቸውና የተመረጡ አቅጣጫዎች ናቸው። እነዚህ ሁሉ በየቀኑ ስለ ትግራይ እንጂ ስለ ኢትዮጵያ አይሰሙም። ዘመቻውም ጠንካራ የሆነው በዚሁ መነሻ ነው። እነዚህ አካላት ሚዲያውን ጨምሮ ሁሉም ፕሮፓጋንዳ በጃቸው ነው። ቀደም ብዬ እንዳልኩት ቀደም ብሎ አገራችን በመርህ ላይ የተመሰረተ የዲፕሎማሲ አግባብ ስላልነበራት ወይም እንዲኖራት ስላልተደረገ ዛሬ ልንፈተን ችለናል። ትህነግ የተመረጠው በዚህ አግባብ ነው። ከሰራንበት ግን በአጭር ጊዜ ይቀየራል።

ኢትዮ12- “አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ አሰራርና፣ አተገባበር” ያልሉ ምን ድን ነው?

ዶ/ር ሃይማኖት– ያለፈው አካሄድ እንዳከሰረ ታይቷል። ክርክር የለውም። ስለዚህ አዲስ አስተሳሰብ ግድ ነው። ትህነግ እያልን መሟገት ማቆም አለብን። 115 ሚሊዮን ሕዝብ ያላትን አገር አሜሪካ ከከሰረች ምን እንደምታጣ ማሳየትና በምስራቅ አፍሪቃ ቀጣና ምን ሊከሰት እንደሚችል እንዲረዱ ማድረግ ግድ ነው። ትህነግ መረጃ እያምታታና በሚዲያ የበላይነት ራሱን ኢትዮጵያ ከምታክል አገር ይልቅ ለአሜሪካ ፍላጎት የተሻለ አድርጎ የሚያቀርበበትን አግባብ የእኛን ጉዳይ በማጉላት ብቻ ማሳየትና አሁን የሰፈነውን አመለካከት መገልበጥ ይቻላል። ስለዚህ አዲስ አሳብ ስል ዲፕሎማሲውን ከተራ ገንዘብ ሰብሳቢነት አላቆ ወደ ህዝብ ተሳትፎ ከፍ ማድረግ፣ እንደ እኛ ያሉ ድርጅቶችና ቀና አሳቢ ዜጎች ኢትዮጵያን የሚወክሉ አምባሳደሮች እንዲሆኑ ማስተባበር። አዲስ የትግበራ መንገድ መከተል ለማለት ነው። ( ዝርዝሩን ከቪዲዮው ያድምጡ)

ኢትዮ12- ስለዚህ አዲሱ አስተሳሰብ ኢትዮጵያን ማጉላት ነው እያሉ ነው?

ዶ/ር ሃይማኖት- በሚገባ። ፖሊሲ አውጭዎቹ እኮ በገሃድ የመረጃ ችግር እንዳለባቸው ነግረውናል። ራሳችንን ከትህነግ ጋር ማወዳደርና ትህነግን በመክሰስ ላይ የተመሰረተ ዲፕሎማሲ ውጤቱ ታይቷል። ያን መድገም አያዋጣም። አዲሱ እሳቤ ኢትዮጵያ ለአሜሪካ ጥቅም መከበር የማይተካ ሚና እንዳላት ማሳየትና ማረጋገጥ ነው። ከዚህም በላይ ኢትዮጵያ ለአሜሪካ ጥቅም ብቸናዋ የማትተካ አገር ብቻ ሳትሆን ሰብአዊ ቀውስ በመቀነስ ረገድ በቀጣናው እጅግ ታላቅ ሚና እንዳላት መረጃ መስጠትና ማሳመን ይጠይቃል። 115 ሚሊዮን ሕዝብ እንዲበተን መስራት፣ ስድስት ሚሊዮን ሕዝብ መደገፍ የመረጃ ክፍተት ካለሆነ በስተቀር ለማንም ግልጽ የሚታይ ጉዳይ ነው …

ኢትዮ 12- ትህነግ የኢትዮጵያን መንግስት ደካማ አድርጎ በየጊዜው የሚስለውና ይህንኑም የትህነግን ፍላጎት ሚዲያዎች የሚያራግቡት የተሻለ መሆኑንን ለመምስከርና ጫና ለመፍጠር ነው?

ዶ/ር ሃይማኖት – ምን ጥያቄ አለው? በሶማሊያ፣ በሱዳን የአሜሪካንን ፍላጎት ለማስጠበቅ ጥሩ ቅጥረኞች እኛ ነን በሚል ለአሜሪካ የደህንነት ጥያቄ መልስ ሰጪ ሆነው ኖረዋል። ዛሬም ” እኛ ካልሆንን ” እያሉ ነው በህዝብ ግንኙነታቸው በኩል የሚሰሩት። የሰላም ማስከበሩ ትህነግ ከወረደ በሁዋላ ያለ ችግር ቀጥሏል። ስለዚህ ኢትዮጵያ ይህን ተግባር በተሻለ ደረጃ እንደምትሰራ አሳይታለች። ወደፊትም ይህንኑ ታደርጋለች በሚል የተዛውን ፕሮፓጋንዳ ኢትዮጵያን በማጉላት መቀየር ይገባል።

ኢትዮ 12- ምን አልባት የሰሜን ዕዝ እንዲጠቃ የተደረገው ለዚህ ይሆን?

ዶ/ር ሃይማኖት- “የተረጋጋች ኢትዮጵያን መምራት የምችለው ብቸኛ ድርጅት እኔ ነኝ” የሚለው ትህነግ ፣ ሰሜን ዕዝን ሲያጠቃ ሰማኒያ በመቶ የኢትዮጵያ ጦር እንደወደመ፣ መሳሪያውን እንደተቆጣጠረ፣ በማወጅ የአሜሪካን ጥቅም በማስከበር ደረጃ ብቸኛ ድረጅት መሆኑንን ለማሳየት ነበር እቅዱ። በገሃድም ተናግረዋል። በዓለም አቀፍ ተቋማት የሚሰሩት እንደ ቴዎድሮስ አድሃኖም ዓይነት የትህነግ ሰዎች፣ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ቢሮ በአፍሪካ ጉዳይ አስፈጻሚ ዲፓርትመንት፣ በኮንግረንስ የአፈሪካ ጉዳዮች በተመከተ የሚሰሩ ሃላፊዎች … በግንዘብና በተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች አስረዋቸዋል። በአሜሪካ የፖለቲካና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በእጅጉ ከጥቅም ጋር የተሳሰረ ነው። ከለውጡ በፊት ጥቅም ሲያገኙ የነበሩና የቆመባቸው ያንን ጥቅም ለማግኘት በግለሰብ ደረጃ በሚሰጣቸው መጠን ሁሉንም ደጅ ያንኳኳሉ….

ኢትዮ 12- አሁንም በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ የሚነዛው ፕሮፓጋንዳ የዛው ቀጣይ ነው ማለት ይቻላል?

ዶ/ር ሃይማኖት – አገር መምራትና አረጋግተን ማስቀተል የምንችለው፣ የአሜሪካን ጥቅም ማስተበቀ የምንችለው እና ብቻ ነን የሚለውን ለማሳካታን ያሰቡትን ለመያዝ የማያደርጉት ነገር የለም። ለዚህ ነው ሁሉም ለአገሩ አምብሳደር፣ ዲፕሎማት መሆን አለበት የምንለው። ድርጅታችን እንደራጅ የሚለው ለዚህ ነው። ስንደራጅና መደራጀታችንን በየዕለቱ ስናውጅ ሃይል እንዳለን ያውቃሉ። ሃይላችን ሲሰባሰብ በምርጫ ላይ ያለንን ጉልበት ይረዳሉ። በአሜሪካ ድምጽ ዋጋው ውድ ነው። ድምጻችንን አስተባበረን ለመብታችን መሟገቻና መደራደሪያ ማድረግ አለብን። Ethiopian Americans Voting Bloc – EAPAC Global በግል፣ በማህበራዊ ጉዳይ፣ በንግድ ድርጅቶቻችን፣ በልጆቻችን፣ በጤናችን … በብዙ መልኩ ተጠቃሚ ለመሆን ኢትዮጵያ አሜሪካንስ እንደራጅ። ዋናው ጉዳይ መመዝገብ ብቻ ነው።


This image has an empty alt attribute; its file name is 217391620_843127696581497_1533589810883676736_n.jpg
EAPAC

EAPAC Global is by all Ethiopian Americans for all Ethiopian Americans. We are all in this together. One Ethiopian American for all and all Ethiopian Americans for one.

ዝግጅት ክፍሉ – እዚህ ቃለ ምልልስ ውስጥ የተጠቀሰው በቃለ ምልልሱ ያልተባለ ነው። ቪዲዮውን ታደምጡ ዘንዳ እናበረታታለን። ዶ/ር ሓይማኖት ሰፊ ራዕይና አሳብ አንግበው በመነሳታቸው ቀና ዜጎች ሁሉ እንዲያግዟቸው ጥሪ እናቀርባለን። ይህን መረጃ የምታነቡ ሁሉ ሼር በማድረግ ይህ ሃሳብ ዜጎች ዘንድ እንዲደርስ ታደርጉ ዘንድ እናሳስባለን። በተከታታይ የድርጅቱን ተግባርና ውጤት እየጠየቅን ለማሳወቅና ይህን ሃሳብ ለማስፋፋት እንደምንሰራ እናረጋግጣለን

ከድርጅቱ ገጽ የተወሰደ አስፈንጣሪውን ተጭነው ዝርዝር ይመልከቱ


[jetpack_subscription_form show_subscribers_total=”false” button_on_newline=”false” custom_font_size=”16px” custom_border_radius=”0″ custom_border_weight=”1″ custom_padding=”15″ custom_spacing=”10″ submit_button_classes=”has-text-color has-white-color has-background has-vivid-cyan-blue-background-color” email_field_classes=”” show_only_email_and_button=”true”]
    INTERVIEW
    FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
    “በትግራይ በዕርዳታ ስም የልዩ ኦፕሬሽን ኤጀንቶች ጦርነቱ ውስጥ እየተሳተፉ ነው”
    ትህነግ ለህ.ግ ለነጮች በወር ከ1.1 ሚልዮን ዶላር በላይ ይከፍላል፤ ወጪው የሚዲያና ሌሎች ተከፋዮችን አይጨምረም
    Related posts
    • Related posts
    • More from author
    POLITICS

    ኢራን እኛ ላይ ምን ልታደርግ ትችላለች?

    March 28, 2026
    POLITICS

    አስቸኳይ የአርበኛነት ጥሪ ለኢትዮጵያን

    March 4, 2026
    POLITICS

    ትራምፕ ኢራንን እንደሚወጉ ፍንጭ ሰጡ

    January 28, 2026
    Load more
    Read also
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    WORLD

    ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    WORLD

    አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

    April 26, 2026
    WORLD

    የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

    April 26, 2026
    WORLD

    የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

    April 26, 2026
    Load more
    Recent Posts
    • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
    • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
    • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
    • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
    • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
    • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
    • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
    • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
    • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
    • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
    • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
    • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
    • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
    • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
    • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
    Social networks
    FacebookLikes
    X TwitterFollowers
    PinterestFollowers
    InstagramFollowers
    YoutubeSubscribers
    VimeoSubscribers
      VOE
      The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

      MENU

      NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
      © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
      • CONTACT
      • law
      • INTERVIEW
      • ያበደው
      • ECONOMY
      • Home demo times
      • VOE VIDEO
      • ENGLISH PAGE
      • Home Demo default 2