የትግራይ ሕዝብ ነሳ አውጪ ግንባር / ትህነግ ” ብቸኛ የአሜሪካና አውሮፓ ጥቅም አስጠባቂ ነኝ፣ የተረጋጋች አገር መምራት የምችለው እኔ ብቻ ነኝ” በሚል የአሚሪካን ፖሊሲ አውጭዎች ለማሳመን በወር ከአንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ እንደሚያደርግ ተጠቆመ። ወጪው የነሳ አውጪውን ድርጅት ዓላማ የሚስተጋቡ የሚዲያ ሰዎችና ነጭ አክቲቪስቶች የሚከፈለውን አይተቃልልም።
አምስት ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ለምግብ ችግርና አንድ ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች ለከፋ ችጋር እንደታጋለጡበት የሚነገርለት የትግራይን ክልል ነጻ ለማውጣት የትጥቅ ትግል ላይ የሚገኘው ትህነግ፣ ይህን ያህል ከፍተኛ ሃብት የሚያፈሰው ለስምንት ከወስዋሾች የገዘፉ የህዝብ ግንኙነት የሚሰሩላቸው ድርጅቶች ነው።
በቂ መረጃ እንዳላቸው ጠቅሰው ከኢትዮ 12 ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት ዶክተር ሓይማኖት እንዳሉት “ትህነጎች ስምንት የህዝብ ግንኙነት የሚሰሩላቸው ድርጅቶ ቀጥረዋል። ከለውጡ በፊት በወር አርባ ሺህ ዶላር ይከፍሏቸው ። ከልወጡ በሁዋላ ከ100 እስከ 140 ሺህ ዶላር እንደሚከፍሏቸው መረጃ አለኝ። ይህን ሁሉ ሃብት እያፈሰሱ ነው ኢትዮጵያ ስሟ እንዳየሳ፣ ጉዳይዋ እንዳይሰማ ሁሉንም በሮች የተቆጣጠሩት። ስልጣን ላይ እየሉ ባከማቹት የዘርፊያ ሃብት የህዝብ ግንኙነቱን ስራ በገንዘብ ቆላልፈው ይዘውታል።”
ለዲሞክራቶች፣ ለሪፐብሊካኖች፣ ለሃይማኖቶች ጥምረት፣ለጥቁር አፍሪካ አሜሪካኖች ጥምረት፣ ለዋይት ሃውስ፣ ለኮንግረንስ፣ Lesbian, Gay, Bisexual and Transgender. q ለሚባሉት ጥምረቶችና ለተቀረው የህብረተሰብ ክፍል በህዝብ ግንኙነት የሚሰሩ የታሰበባቸውና የተመረጡ አቅጣጫዎች መሆናቸውን የስምንቱን ተቋማት ሚና በማስረዳት ዶክተር ሃይማኖት አስረድተዋል። ሙሉ ቃለ ምልልሱን እዚህ ላይ ይመልከቱ። የዚዲዮውን ምልልስ ደግሞ በዩቱብ ቻናላችን እዚህ ላይ ያገኙት።
- ኢራን እኛ ላይ ምን ልታደርግ ትችላለች?ኢራን በእስራኤልና በአሜሪካ የተከፈተባትን ጦርነት ለመመከት በሚል ሰበብ በገልፍ ሃገራት ላይ በተለይም በዱባይ አረብ ኤምሬትስ ሚሳኤልና ዱረን እየተኮሰች ቀጠናውን… Read more: ኢራን እኛ ላይ ምን ልታደርግ ትችላለች?
- አስቸኳይ የአርበኛነት ጥሪ ለኢትዮጵያንኢትዮጵያን እንወዳለን፣ ኢትዮጵያ አገሬ ናት፣ ኢትዮጵያ እናቴ ናት፣ ሌላ እናት የለኝም የምትሉ ሁሉ፤ በኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል የምትሉ የመንግስት አካላት፣… Read more: አስቸኳይ የአርበኛነት ጥሪ ለኢትዮጵያን
- ትራምፕ ኢራንን እንደሚወጉ ፍንጭ ሰጡዶናልድ ትራምፕ ትኩረታቸውን ወደ ፐርሽያ ገልፍ ባላንጣቸው ኢራን በመመለስ፣ ቀደም ሲል በደቡባዊ ቻይና ባህር ትንቀሳቀስ የነበረችውን ግዙፏን “አብርሃም ሊንከን”… Read more: ትራምፕ ኢራንን እንደሚወጉ ፍንጭ ሰጡ
- “ኢትዮጵያ ወደ ባህር የመውጣት ፍላጎቷን እውቅና እንሰጣለን” ሶማሊላንድቪኦኢ – በዳቮስ የዓለም ኢኮኖሚ ፎረም ላይ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን ሞሐመድ (ኢሮ) ያስመዘገቡት ዲፕሎማሲያዊ ድል፣ በአፍሪካ ቀንድ ለዘመናት የነበረውን… Read more: “ኢትዮጵያ ወደ ባህር የመውጣት ፍላጎቷን እውቅና እንሰጣለን” ሶማሊላንድ
- የብር እርሻ – ስደተኛው ፋኖ “ገንዘብ በእህል ሚዛን እየተካፈሉ ነው” ስራ ብዙው የሰመራ ኢምግሬሽን የአሻራ ክፍያአዲስ ሪፖርተርት – “ነፍጥ ያነገቡ ከፍተኛ ሃብት እያፈሩ ነው” እጃቸውን ባፋቸው ጭነው የሚታዘቡ። ወደ ኬንያ ድንበር ያሉት የሸኔ ታጣቂዎች… Read more: የብር እርሻ – ስደተኛው ፋኖ “ገንዘብ በእህል ሚዛን እየተካፈሉ ነው” ስራ ብዙው የሰመራ ኢምግሬሽን የአሻራ ክፍያ







