በ32ኛው የቶኪዮ ኦሊምፒክ በመሳተፍ ላይ ካሉ ሃገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በተለይ በአትሌቲክስ ስፖርት የበላይነቱን እንደሚይዙ ከሚጠበቁት ሃገራት መካከል ትገኛለች። የመጀመሪያው የወርቅ ሜዳሊያም ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ በወንዶች 10ሺ ሜትር የተመዘገበ ሲሆን፤ ሁለተኛው ወርቅ ደግሞ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ውድድራቸውን በሚያደርጉት ሴት አትሌቶች ሊመዘገብ እንደሚችል ይጠበቃል።

ቀላል ግምት በማይሰጠው በዚህ ውድድር የዓለም ፈጣን ሰዓት ባለቤት የሆኑ አምስት አትሌቶች የኦሊምፒኩን ክብር ለማግኘት የሚፋለሙበት በመሆኑ ከወዲሁ አጓጊ ሆኗል። ሦስቱ ባለፈጣን ሰዓት አትሌቶች ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ፤ ሁለቱ ደግሞ ኬንያዊያኑ ሄለን ኦቤሪ እና አጄንስ ቲሮፕ ናቸው። የረጅም ርቀት ክብርን ከኢትዮጵያዊያን ለመንጠቅ አብዝታ የምትተጋው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ኔዘርላንዳዊት አትሌት ሲፈን ሃሰንም ከሌሎቹ የዘገየ ሰዓት ቢኖራትም ጠንካራ ተፎካካሪ እንደምትሆን ግን ይጠበቃል።
ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ ታሪክ በአጠቃላይ 13 የኦሊምፒክ ተሳትፎዎቿ 54ሜዳሊያዎችን በተለያዩ ርቀቶች ሰብስባለች። ሃገሪቷ የስኬት ታሪክ በማስመዝገብ ከታወቀችባቸው የረጅም ርቀት የመም ውድድሮች መካከል አንዱ ደግሞ 5ሺ ሜትር መሆኑ ይታወቃል። ታዲያ በዚህ ርቀት በሴቶች ብቻ 3 የወርቅ፣ 1 የብር እና 4 የነሐስ በድምሩ 8 ሜዳሊያዎች ተመዝግበዋል። በዚህ ርቀት ሦስተኛ ደረጃን በመያዝ መጀመሪያውን የስኬት ተሳትፎ ያስመዘገበችው አትሌት ጌጤ ዋሚ እአአ 2ሺ የሲድኒ ኦሊምፒክ ተሳትፎዋ ነው። ከአራትዓመት በኋላ በተካሄደው የአቴንስ ኦሊምፒክ ሌላኛዋ የርቀቱ ጀግና አትሌት መሰረት ደፋር የወርቅ ሜዳሊያውን ስትወስድ ጥሩነሽ ዲባባ ደግሞ የነሐስ ሜዳሊያው ባለቤት ነበረች።
በቀጣዩ የቤጂንግ ኦሊምፒክ የጥምር ስኬት ባለቤት የነበረችው አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ስትሆን፤ እርሷን ተከትላ የገባችው መሰረት ደፋር ደግሞ የብር ሜዳሊያውን ወስዳለች። በለንደን ኦሊምፒክ መሰረት ወደ ወርቅ ባለቤትነቷ ስትመለስ ጥሩነሽ ደግሞ የነሐስ ሜዳሊያውን ከእጇ አስገባቸው። ይኸው ከትውልድ ትውልድ የተላለፈ የስኬት ታሪክ ከአምስት ዓመት በፊት በተካሄደው የሪዮ ኦሊምፒክም ቀጥሎ በአልማዝ አያና የነሐስ ሜዳሊያ ሊመዘገብ ችሏል።
ኢትዮጵያ በርቀቱ ያላት የኋላ ታሪክ ከስኬት ጋር የተያያዘ ሲሆን፤ ብርቱዎቹ አትሌቶች ክብራቸውን አሳልፈው እንደማይሰጡም ይታመናል። የርቀቱ የዓለም ክብረወሰን ሃገሯን በ10ሺ ሜትር በምትወክለው ለተሰንበት ግደይ የተያዘ ሲሆን፤ ሃገሪቷ ቶኪዮ ላይ በምታደርገው 14ኛው የኦሊምፒክ ተሳትፎዋም በዚሁ ርቀት በአዳዲሶቹ የኦሊምፒክ አትሌቶች ሜዳሊያ ሊመዘገብ እንደሚችል ከፍተኛ ቅድመ ግምት ተገኝቷል። ቡድኑን የሚወክሉት ሦስት አትሌቶች ሲሆኑ፤ እነርሱም ጉዳፍ ጸጋይ፣ ሰንበሬ ተፈሪና እጅጋየሁ ታዬ የማጣሪያ ውድድራቸውን አልፈዋል።
በማጣሪያ ውድድሩ ምድብ አንድ የሮጡት ሁለት አትሌቶች ሲሆኑ፤ ሰንበሬ ተፈሪ 14፡48.31 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ስትወጣ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ ደግሞ 14፡48.52 በሆነ ሰዓት አራተኛ በመሆን ነበር ማጣሪያውን ያለፉት። ምድብ ሁለት የተካፈለችው አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ በበኩሏ 14፡55.74 የሆነ ሰዓት በማስመዝገብ ከምድቡ አንደኛ ሆና ነበር ያጠናቀቀችው።
በርቀቱ በተለይ ለአሸናፊነት የምትጠበቀው ጉዳፍ ጸጋይ ከወር በፊት ሄንግሎ ላይ በተካሄደው የሰዓት ማሟያ 14:13.32 ያስመዘገበች ሲሆን፤ ይህም ከምድቡ ቀዳሚ ነው። ሰንበሬና እጅጋየሁም በአንድ አንድ ሰከንድ ብቻ የዘገየ ሰዓት ሲኖራቸው በዛሬው ውድድር ከሚሳተፉት አትሌቶች ደግሞ እጅግ የፈጠነ ሰዓት ባለቤቶች ናቸው። ይህም አሸናፊ በመሆን ለሃገራቸው ተጨማሪ ሜዳሊያ እንዲያስመዘግቡ ሊደርጋቸው እንደሚችል ይጠበቃል።
ዛሬ ከሰዓት በኋላ የሚካሄደው ሌላኛው የፍጻሜ ውድድር የወንዶች 3ሺ ሜትር መሰናክል ነው። በዚህ ርቀት ሁለት አትሌቶች የሚሰለፉ ሲሆን፤ በማጣሪያው አንደኛ ሆኖ የገባው ለሜቻ ግርማ 8:09.83 የሆነ ሰዓት ነበር ያስመዘገበው። እርሱን ተከትሎ የገባው ጌትነት ዋለ ደግሞ 8:12.55 በሆነ ሰዓት ሮጧል። በርቀቱ የኢትዮጵያ ክብረወሰን ባለቤት የሆነው ወጣቱ አትሌት ጌትነት እአአ 2017 እና 2019 በተካሄዱት የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ሃገሩን የወከለው አትሌቱ በርቀቱ ያለውን ልምድ ተጠቅሞ የሜዳሊያ ባለቤት ይሆናል የሚል ተስፋ ተጥሎበታል።
ብርሃን ፈይሳ ኢዜአ
- AU Executive Council Chair Renews Push for Africa’s Permanent Seat on UN Security CouncilVOE NEWS | ADDIS ABABA | July 29, 2026 – The Chairperson of the African Union (AU) Executive Council, Édouard Nduwimana, has renewed Africa’s longstanding call… Read more: AU Executive Council Chair Renews Push for Africa’s Permanent Seat on UN Security Council
- Sudan’s Kurmuk Front Raises Regional Security Concerns as Reports Emerge of TPLF-Linked Fighters’ InvolvementVOE NEWS | ADDIS ABABA/KHARTOUM | July 9, 2026The military situation around Sudan’s strategic Kurmuk area in Blue Nile State is drawing increased attention in Ethiopia,… Read more: Sudan’s Kurmuk Front Raises Regional Security Concerns as Reports Emerge of TPLF-Linked Fighters’ Involvement
- EFF Condemns Zimbabwe’s Constitutional Changes as Mnangagwa Extends Rule to 2030By VOE News | July 9, 2026 – HARARE, Zimbabwe – South Africa’s opposition Economic Freedom Fighters (EFF) has strongly condemned Zimbabwean President Emmerson Mnangagwa after… Read more: EFF Condemns Zimbabwe’s Constitutional Changes as Mnangagwa Extends Rule to 2030
- Could the Horn of Africa Face Another Afghanistan? What a Stronger Al-Shabaab Could Mean for Ethiopia, Kenya and the RegionFor nearly twenty years, African Union peacekeeping forces have formed the backbone of Somalia’s campaign against Al-Shabaab, helping successive Somali governments reclaim territory, protect major cities,… Read more: Could the Horn of Africa Face Another Afghanistan? What a Stronger Al-Shabaab Could Mean for Ethiopia, Kenya and the Region
- Somalia Opposition Criticized for Accepting Turkish Intelligence Official as MediatorVOE NEWS | MOGADISHU | July 8, 2026 MOGADISHU – Prominent Somali senator and political scholar Abdi Ismail Samatar has sharply criticized Somalia’s opposition leaders for… Read more: Somalia Opposition Criticized for Accepting Turkish Intelligence Official as Mediator






