Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ጌታቸው ረዳ “ሰራዊታችን የደረሰበት ጉዳት የለም፤በቅርቡ አዲስ አበባ…”
News

ጌታቸው ረዳ “ሰራዊታችን የደረሰበት ጉዳት የለም፤በቅርቡ አዲስ አበባ…”

Ethioreview newsEthioreview news—August 26, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

“አሸባሪ” ተብሎ የተስየመው ትህነግ አፈ ቀላጤ አቶ ጌታቸው በአማራና አፋር ክልል በመልሶ ማጥቃት ምን ጥቃት እንዳልደረሰባቸው አስታወቁ። አቶ ጌታቸው ሊያጠቃ የመጣውን ሃይል በሙሉ የትህነግ ሃይል ሙሉ በሙሉ እንደመሰሰና በቅርቡ አዲስ አበባ ከመግባት የሚያግዳቸው ሃይል እንደሌለ አስታውቀዋል።

በትናትናው ዕለት ከትግራይ ሚዲያ ሃውስ ጋር ወይይት ያደረጉት አቶ ጌታቸው፣ አሸባሪው ድርጅታቸው ምንም ጉዳት እንዳልደረሰበት ሲያስታውቁ በወረራ ይዟቸው የነበረውን ስፍራዎች እንዴት እንደለቀቁ አልተናገሩም።

ሰሞኑንን በርካታ ቦታዎች መለቀቃቸውና በትህነግ ሃይል ላይ ከፍተኛ የሰብአዊና ቁሳዊ ውድመት መድረሱን፣ በርካታ መማረካቸውንና የተረፈውም ወራሪ ሃይል ተከቦ መውጣት እንደማይችል በተደጋጋሚ የተለቀቁት ቦታዎች በምስል እየታዩ፣ አርሶ አደሩ ምስክርነት እየሰጠ፣ የወደሙ ሃብትና መሰረተ ልማቶች እየታዩ ምስክርነት ስለመቅረቡ አቶ ጌታቸው አልተጠየቁም።

በደፈናው የትህነግ ሃይል የሪፕብሊካን ጋርድ ሳይቀር ሙሉ በሙሉ መደምሰሳቸውን አቶ ጌታቸው የገለጹት እጃቸውን ከጃቸው ጋር በማፋጨት ነው። ” እጅግ ያሳዝናል” ሲሉ በተደጋጋሚ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ስም በመጥራት ሰራዊታቸው ጭንቅላት ለይቶ የሚመታ ብቃት እንዳለው ያስታወቁት አቶ ጌታቸው “የአማራ ልዩ ሃይል የመዋጋት አቅም የለውም” ሲሉ ተደምተዋል። የትህነግ ሃይል በርካታ ቀያይ ኮፍያ ከገደላቸው የሪፐብሊካን ሃይል ወታደሮች ላይ ቢረከበም መጠኑ ሰፋፊ ስለሆነ ለጭንቅላታቸው እንደበዛባቸው አመልክተዋል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ድራማ በሚመስል አገላለጽ ውይይታቸውን ያደረጉት አቶ ጌታቸው፣ አዲስ አበባ ለመግባት የሚከላለክላቸው አካል እንደሌለም አስታውቀዋል። አቶ ጌታቸው ከዳር እስከዳር በተደጋጋሚ “አሸባሪ” በሚል የተቃውሞ ስልፍ እያደረገ ስላለውና በመቶ ሽህ የሚቆጠር ሰራዊት በፈቃደኛነት በሳምንት ጊዜ ውስጥ ወደ ማስለጠኛ በምግባቱን አስመልክቶ ምንም አላሉም። ወደ አዲስ አበባ መግባት እንደሚችሉ ከመናገራቸው ውጭ እንዴትና በየት በኩል ህዝቡን አምልጠው አዲስ አበባ እንደሚገቡ አላመለከቱም።

“በተለመደው የጥያቄና መልስ መርህ ሳይሆን በርካታ ቦታዎችን በመልቀቃቸው ሳቢያ የተፈጠረውን የስነ ልቦና ሽንፈት ለማስታገስ የተሰጠ የሚመስል ውይይት ነው” ያሉ፣ ስለተማረኩ አዋጊዎች፣ ስለወደሙ የሕዝብ ሃብቶችና የጤና ተቋማት እንዲሁም በጅምላ በትህነግ ተፈጁ ትብለው ምስክርነት ስለሰጡ ወገኖች አቶ ጌታቸው አልተናገሩም። በውይይቱም አለመጥየቃቸውን አምለክተዋል። እናም ዓላማው ግልጽ ነው።

“ከአርሶ አደሩ ጋር ችግር የለብንም” ያሉት አቶ ጌታቸው ልማቶችን እንደማይነኩ ደጋገመው አመልክተዋል። ይሁንና ሰራዊታቸው በርካታ መሰረተ ልማቶችን፣ አንድ ከተማና ሆስፒታል ሙሉ በሙሉ ማውደሙን ተጠይቀው አላስተባበሉም። ከወረሩት ስፋራዎችና ከተሞች የትኞቹ አሁን ድረስ በትህነግ እጅ እንደሚገኝ ይፋ አላደረጉም። የአማራ ክልል ግን ነጻ የወጡ ከተሞችንና አካባቢዎችን በስም ዘርዝሮ በምስል አስደግፎ ይፋ እያደረገ ነው።

እሳቸው ይህንን ውይይት በሚያደርጉበት ወቅት አስተያየት ሲያካፍሉ የነበሩ የትህነግ ቁልፍ ደጋፊ የሚባሉ በግንባር ሽንፈት እየደረሰ መሆኑንን ጠቅሰው የተቀያየሩትን የማህበራዊ ገጽ ቅጂ እየለጠፉ “አቤት ውሸት” ሲሉ ነበር።

አቶ ጌታቸው ” መዋጋት አይችልም” ያሉት የአማራ ልዩ ሃይል ቀጣይ እጣው መደምሰስ እንደሆነ ደጋግመው ተናግረዋል። ከወር በፊት ጎንደርን፣ ባህር ዳርንና ደብረብርሃንን ተቆጣጥረው ወደ አዲስ አበባ እንደሚያቀኑ በቲወተር ገጻቸው ደጋግመው ያስታወቁት አቶ ጌታቸው ብቻ ሳይሆኑ፤ የሚዲያና የማህበራዊ ገጹን የሚመሩት ነጮች ጭምር ነበሩ። መከላከያው ዋጋ እንደሌለው፣ ልዩ ሃይሉ የመዋጋት ብቃት እንደሌለው የገለጹት አቶ ጌታቸው ያሉት ተጋባራዊ እንዳይሆን ማን እንዳገዳቸው አልገለጹም።

“ድሮንም ቢመጣ ጦረንቱን አይቀይረውም” በሚል አቶ ጌታቸው አስታውቀዋል። ይህን እንጂ በአፋር ግንባርም ሆነ በአማራ ግንባር ከአየር ስለደረሰው ጥቃት አየር ሃይል ላለው ማስተባበያ አልሰጡም።

በንግግራቸው መካከል እጅግ አድርገው ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚኮንኑትና ለሳቸው ሲባል የሚደረግ ጦርነት እንደሆነ በመጥቀስ ህዝብ ጦርነቱን በማውገዘ ” አልዋጋም” እንዲል ጥሪ አቅርበዋል። በቢቢሲው የሃርድ ቶክ ክፈለ ጊዜ መብራት፣ ስልክ፣ ባንክ የመሳሰሉት አገልግሎቶች መክፈት ብቻ ለሰላም እንዲቀመጡ በቂ መሆናችውን ያስታወቁት አቶ ጌታቸው ቀደም ሲል ያስቀመጡትን ስምንት ነጥቦች ለምን እንደቀየሩ ይፋ አላደረጉም።

The federal forces counteroffensive restarted after Addis Ababa lifted the unilateral ceasefire it declared late June. መንግስት ጥሎት የነበረውን የተናጠል ተኩስ አቁም ካነሳ በሁዋላ መልሶ ማጥቃት መጀመሩን ያስታወቀው አሶሲየትድ ፕሬስ ለመቀለ ቅርብ የሆኑት አላማጣና ኮረምን መያዛቸውን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ይሁን እንጂ አቶ ጌታቸውም ሆኑ ትህነግ ይህንን አላስተባበሉም። ከተተቀሱት ከተሞች ቀጥላ ያለችው አንድ ቀበሌ ስትቀር ቀጣይዋ ከተማ መቀለ ነች።

ባለፉት ሁለት ሳምንታት የጦር ግንባር ዜናዎች ሙሉ በሙሉ ስለመቀየራቸው የውጭ ሚዲያዎች ሳይቀሩ እየገለጹ ነው። ትህነግ አንድ መንደር ሙሉ በሙሉ ማውደሙ፣ የጅምላ ጭፍጨፋ ማካሄዱ ቦታና እየተጠቀሰ በሰዎች ምስክርነትና በሳተላይት መረጃ ይፋ እየሆነ ነው። ይህንን አስመለክቶ አቶ ጌታቸው ያሉት ነገር የለም። ይህ የጦር ወንጀል ስለመሆኑ ግን በስፋት እየተሰራጨ ይገኛል።

ሊጥ፣ ሌማትና ዱቄት ሳይቀር እየሰረቃቸው እንደነበር በሚያሳዝን ሁኔታ ስለገለጹት፣ ከብቶቻቸው ስለተጨፈጨፉባቸው አርሶ አደሮች ለቅሶና ምስክርነት ምን ያላሉት አቶ ጌታቸው ” የማይታጠፍ ሃይል አለን” ሲሉ ወደ አዲስ አበባ ለመገስገስ የሚያዳግታቸው አንዳችም ሃይል እንደሌለ ደጋግመው ተናግረዋል።

መንግስት በበኩል በሙሉ ማጥቃት ትህነግን ታሪክ የማድረጉን ዘመቻ ለመጀመር የዝናቡን ጋብ ማለትና የጭቃውን መጥገግ እንደሚጠባበቅ በስፋት እየተነገረ ነው።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ቻይና የኢትዮጵያ መንግስት የውስጥ ጉዳዮቹን በአግባቡ መያዝ የሚችልበት አቅም እንዳለው ታምናለች
ሕወሓት ምንድነው? ለማን ታገለ? አሁንስ በትራፊው ለማን እየታገለ ነው?
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2