Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  በአፋር ጭፍጨፋ ማግስት ኦነግ ከትህነግ ጋር ጥምረት መፍጠሩን ይፋ አደረገ፤ “ሃጫሉ” ነብስ ይማር!!
News

በአፋር ጭፍጨፋ ማግስት ኦነግ ከትህነግ ጋር ጥምረት መፍጠሩን ይፋ አደረገ፤ “ሃጫሉ” ነብስ ይማር!!

Ethioreview newsEthioreview news—August 11, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በህቡዕ የማይታወቀው ቀደም ሲል የኦነግ ሸኔ፣ አሁን ደግሞ የኦሮሞ ጦር መሪ እንደሆነ የሚነገርለት ጃል መሮ ከአጃንስ ከኤፒ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ ከትህነግ ጋር ግንባር ገጥሞ በጥምረት እየሰራ መሆኑንን በይፋ አስታወቀ። ዜናው ለመላው ኦሮሞ አስደንጋጭ ሆኗል። “ዜናው የሃጫሉ ትንቢት አስታውሷል” ያሉ ሃሜቱ በግልጽና በይፋ መነገሩ ለውሳኔ ያመቻል ያሉም አሉ።

ትህነግ እንደወትሮው በአማራ ክልልም ሆነ በኦሮሚያ ወደየትም ስፍራ እንዳሻው መንቀሳቀስ ስለማይችል፣ በኦሮሚያ ድሮ ሲያርደው፣ ሲጨፈጭፈው፣ ሲያሸማቀቀው፣ ሲያስረውና አካሉን ሲያጎለው ወደነበረበት ክልል ለመግባት የኦሮሞ ድርጅት ስለሚያስፈልገው ኦነግን እንደመረጠ፣ ከኦነግ የተከፈሉት ቡድኖች አስቀድመው ሲናገሩ መቆየታቸው ይታወሳል።

ዛሬ ጃል መሮ በይፋ እንዳለው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የሚመሩትን መንግስት ለመጣል ከትህነግ ጋር ህብረት መፍጠራቸውን አስታውቀዋል። “ከተመሳሳይ ሌሎች ታጣቂዎች ጋር በተለይም በወታደራዊ ትብብር ላይ ለመረዳዳት በመግባባት ደረጃ ተስማምተናል” ብሏል። «ጥምረቱ የጋራ ጠላትን በጋራ መፋለም » የሚሰኝ ሲሆን “ትህነግን ወደ ስልጣን ለመመልስ የጃልመሮ ሰራዊት ኦሮሞ ላይ ይተኩሳል እንደማለት ነው። ኦሮሞ ኦሮሞን ገድሎ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪን ሊያነግስ ዓለም ፊት ለኦሮሞ ህዝብ ያውጃል” ሲል ዜናውን ተከትለው አስተያየት የጻፉ አሉ።

ጃልመሮ አርቲስ ሃጫሉ በድንገት ሲገደል ከጫካ እሳቸው የሚመሩት ቡድን በስልክ ማስፈራሪያ እንዳደረገበት በይፋ መሰማቱን ይታወስዳል። ይህንኑ ተከትሎ በቪኦኤ ማስተባበያ እንዲሰጡ ሲደረጉ ከትህነግ ጋር ከቶውንም እንደማይተዋወቁ ገልጸው ነበር። ሃጫሉ ከትህነግ ጋር ዳግም አብሮ የሚሰራ ኦሮሞ ማንም ይሁን ማን ከሃጂ መሆኑንን በተደጋጋሚ በመናገሩና፣ ይህ ንግግሩ ለተጀመረው ህብረት ስለማይሆን ጥርስ እንዲጫንበት ማድረጉ ይታወሳል። በርካቶችም ይህንን በቁጭት አስታውቀዋል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

እድሜዎ ከ18 ዓመት በላይ ከሆነ ይህን ቪዲዮ ያድምጡ

ትህነግ በአፋር 240 ሰዎችን በግፍ መጨፍጨፉን ተከትሎ የተሰማው ዜና ኢህአዴግን ዳግም የማቋቋም ዓላማ እንዳለው ያስረዳል። ቃል በቃል ባይገለጽም ተመሳሳይ የብሄር ድርጅቶች ይህን ህብረት እንደሚቀላቀሉ ተመልክቷል።

ይህ ዜና ይፋ ከመሆኑ በፊት በኦሮሚያ ቁጥራቸው በርከት ብሎ የሚገኙ የአማራ ተወላጆች ባሉባቸው ስፍራዎች የጅምላ ጥቃት ለመፈጸም መታሰቡንና ይህንኑ የሚፈጽመው ደግሞ ጃል መሮ የሚመሩት ሃይል እንደሆነ የአማራ ክልል የወቅታዊ መረጃ ሲሰጥ ጠቁሞ አልፏል።

The #TDF – #OLA tactical alliance in #Ethiopia has been expected for some time. It seems «EPRDF 2.0» is in z making, as #Qemant, #Agaw, #Gumuz, #Gambella, #Sidama + others are establishing political fronts with similar political objectives vs. fed. gov. https://t.co/4rmSALEXh4

— Kjetil Tronvoll (@KjetilTronvoll) August 11, 2021

“የአፋር ህዝብ ሃዘን በተቀመጠበት ወቅት ጭፍጨፋውን ከማውገዝ ይልቅ፣ ጭፍጨፋውን ከፈጸመው አካል ጋር ግንባር መፍጠር እንደ ኦሮሞ አሳፋሪ ነው” ሲሉ አስተያየት የሰጡ ወገኖች ” ኦሮሞ ሆኖ ሸኔን የሚደግፍ ሸኔ ሳይሆን የትህነግ ባሪያ ነው። ሲቀጥልም የሃጫሉ ገዳይ ነው” ብለዋል።

“በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀው ሸኔ ከሌላው አሸባሪ ህወሓት ጋር በጋራ እንደሚሰራ ዛሬ ይፋ ማድረጉ እስከዛሬ ሲፈጸሙ የነበሩትን ዘግናኝ ወንጀሎች ገሃድ የሚያወጡ ናቸው” ሲሉ ዜናውን ተከትሎ ሃሳብ የሰጡ ” የኦሮሞ ህዝብ በይፋ ምላሽ ይሰጥበታል” ብለዋል።

የፖለቲካ ችግር ካለ በሚቻለው ሁሉ በመነጋገር ለመፍታት ደደቢት ድረስ ሄዶ ራስን መሸጥ አስፈላጊ እንዳልሆነ ያመለከተው የዲሲ ነዋሪና የዘወትር የዝግጅት ክፍላችን ተባባሪ ሂርጳሳ ” ያንን ሁሉ ረስቶ ፣ማንም ሆነ ማን የኦሮሞ ልጅ ከኦሮሞ ወንድሞቹ ይልቅ ትህነግ በልጦበት በራሱ ልጆች ላይ ጥይት ለመተኮስ መማማሉን መስማት ባይሳካም ያሳዝናል” ብሏል። አያይዞም ” ኤርትራ እድሚያቸውን ያሳለፉት ወገኖችቻን በትህነግ የዲፖሎማሲ ማዕረግ ወደ አስመራ አላቀኑም። ትህነግ አገራቸውን ነፍጓቸው፣ ቤተሰባቸውን ገድሎ፣ የቻለውን አስሮ፣ ያሻውን ቶርቸር አድርጎና አካል አጉድሎ ስላስጨነቃቸው ወደ በረሃ መግባታቸውን ዘንግተው ዛሬ ከሱ ጋር ተመልሰው ግንባር መሆናቸውን ይፋ አድርገዋል። መንገዱን ጨርቅ ያድርግላቸው” ሲል አስተአየቱን ሰጥቷል።

ፕሮፌሰር ሼትል ትሮቭል የሚባሉት ኖርዌያዊ የትህነግ ስትራቴጂስት ኢህአዴግ ቁጥር 2 መመስረቱን ይፋ አድርጓል። ቅማንት፣ ጋምቤላ፣ አገው፣ ጉሙዝ፣ ሲዳማ እና ሌሎች የትህነግንና የኦነግን ህብረት እንደሚቀላቀሉ ዜናውን ተከትሎ አስታውቀዋል። ሼትል በቀጥታ “ከጌታቸው ሰማሁ” ሰማሁ በሚል አስቀድመው መረጃ በማሰራጨት ስትራቴጂክ ሚና ያላቸው መሆናቸውን ባለፉት ዓመታት በይፋ አሳይተዋል።

በቪኦኤ ከኦነግ ሸኔ ወደ ኦሮሞ ሰራዊት ስም ሲቀይሩ “ለምን? እንዴትና ለመሆኑ እርስዎ ማን ነዎት?” የሚል ጥያቄ ያልረበላቸው ጃል መሮ ስምምነቱን አሁን ያለውን መንግስት ለመታል የተደረገ መሆኑንን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን በመዝለፍ ገልጸዋል።

ሸኔ ባሉት የተለያዩ አደረጃጀቶች ሰፊ ቁጥር ያላቸው የኦሮሞ ልጆችን፣ በክልሉ የሚኖሩ የሌሎች ብሄረሰብ አባላትን፣ እንዲሁም የመንግስት ሰራተኞችን በመግደል የሚከሰስ ደርጅት እንደሆነ ያታወቃል። አንዳንዶቹን ጥቃቶች በቪኦኤ በኩል ሲያስተባብልም ነበር።

ይህን ዜና ተከትሎ ከኦሮሚያ ያለውን ምላሽ አሰባስበን እንመለስበታለን። ዛሬ ወይም ነገ ማምሻውን ቪኦኤና ቢቢሲ ጃል መሮን በስፋት ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል። አሜሪካ በኢትዮጵያ ያለውን የተመረጠ መንግስት ለመጣል እቅድ ነድፋ እየሰራች መሆኑ፣ ዳግም ትህነግን ለማንገስ አቋም እንደያዘች፣ ከኦሮሞና እዚህ ጋር ስማቸውን ለጊዜው ከማናነሳቸው አንዳንድ የድርጅት መሪዎች ጋር በተደጋጋሚ አዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ አማካይነት ስትዶልት መቆየቷ የሚታወቅ ነው።

መንግስት ከጫፍ እስከ ጫፍ ክተት ጠርቶ ትህነግ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ባወጀበት በአሁኑ ወቅት ኢህአዴግ ቁጥር ሁለት ስለመቋቋሙ ይፋ መሆኑ አነጋጋሪ ሆኗል።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Ethiopia armed group says it has alliance with Tigray forces
MOFA- Statement Regarding Latest Report By Amnesty International
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2