Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የህወሓት የሽብር ቡድን በጋይንት፣ ወልዲያ፣ መርሳና ሰቆጣ ከባድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ እየደረሰበት ነው
News

የህወሓት የሽብር ቡድን በጋይንት፣ ወልዲያ፣ መርሳና ሰቆጣ ከባድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ እየደረሰበት ነው

Ethioreview newsEthioreview news—August 14, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የህወሓት የሽብር ቡድን በደቡብ ጎንደር ዞን ጋይንትና አካባቢው፤ በሰሜን ወሎ ዞን ወልዲያ፣ መርሳና አካባቢው፤ እንዲሁም በዋግህምራ ዞን ሰቆጣና አካባቢው እየተሰወደበት ባለው ወታደራዊ እርምጃ ከባድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ እየደረሰበት መሆኑን የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ገለፀ፡፡

የፅህፈት ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከኢቲቪ ጋር ባደረጉት ቆይታ የሽብር ቡድኑ ትላልቅ አዋጊዎች መገደላቸውን እና በርካታ የቡድኑ ታጣቂዎችም መማረካቸውን ገልፀዋል፡፡የህወሓት የሽብር ቡድን በኃይል በወረራቸው አካባቢዎች ወጣቶች ታፍነው ተወስደዋል፣ ሴቶች ተደፍረዋል፣ ንብረቶችም ተዘርፈዋል ብለዋል፡፡በዚህ ሳቢያ የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥርም በከፍተኛ ሁኔታ እያሻቀበ መሆኑን አቶ ግዛቸው አስታውቀዋል፡፡

የህወሓት የሽብር ቡድንን ለመደምሰስ የተላለፈውን ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ ህብረተሰቡ የሽብር ቡድኑን ግብዓተ መሬት ለማፋጠን ያሳየው ተነሳሽነትና ርብርብ የሚደነቅ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡አቶ ግዛቸው በአጠቃላይ ህብረተሰቡ በተለይ ደግሞ ወጣቱ ተደራጅቶ አካባቢውን በንቃት መከታተል እና ከሽብር ቡድኑ ሰርጎ ገቦች መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡በውጭ ሀገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የህልውና ዘመቻውን በገንዘብና አቅማቸው በፈቀደው ሁሉ እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በሌላ ተመሳሳይ የግንባር ዜና መከለክያ ይህን ዘግቧል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

በኢትዮጲያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ቀጠና የተሰማራው የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት የህወሀት ጁንታ ቅጥረኞችን በማሰስና በመደምሰስ ስኬታማ ግዳጆችን እየፈፀመ እንደሚገኝ የ22ኛ ክ/ጦር ዋና አዛዥና የመተከል የተቀናጀ ግብረ ሀይል ኮማንድ ፖስት የኦፕሬሽናል ዘርፍ አስተባባሪ ኮሎኔል ሰይፈ አንጌ አስታወቁ።

የህዳሴ ግድብ የሁለተኛ ዙር ሙሌት በስኬት መጠናቀቅ እረፍት የነሳቸው የውጭ ጠላቶችና የአሸባሪው የህወሀት ጁንታ ቅጥረኞች የአካባቢውን ሰላም ለማወክና የግንባታውን ሂደት ለማደናቀፍ ከማሰብ ተቆጥበው እንደማያውቁ ነው ዋና አዛዡ የገለፁት።

ሰራዊታችን ለአሸባሪዎችና ለተላላኪዎቻቸው ብቻ ሳይሆን በቀጠናው ሊፈጠር ለሚችል ለማንኛውም የውስጥና የውጭ ጠላት በፅናት እና በብቃት መመከት የሚያስችል የሰው ሀይልና የወታደራዊ ትጥቅ ዝግጁነት ያለው መሆኑን አረጋግጠዋል።

የሰራዊት አባላቱ በበኩላቸው የኢትዮጲያ ህዝቦች አይን የሆነውን የዚህን ፕሮጀክት ደህንነት ለመጠበቅ ማንኛውንም መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ነው የገለፁት።የኢትዮጲያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ቀጠናን ሰላም ለማረጋገጥ ከኢፌዴሪ መከላከያ ክፍለጦሮች በተጨማሪ የክልሎች ልዩ ሀይሎች ግዳጃቸውን በፅናትና በጀግንነት በመፈፀም ላይ ይገኛሉ።

አፋር ግንባር

የጁንታው አሸባሪ ሃይል ለገዛ ወገኑ እንኳን አዘኔታ የሌለው መሆኑን ያሳየ ተግባር እየፈፀመ እንደሚገኝ ተገለፀ ፡፡በአፋር ክልል ጭፍራ አከባቢ የሽብር ተግባር ለመፍፀም እና የህዝብን ሰላም ለማወክ የገባውን የአሸባሪው የህውሃት ጁንታ ቡድን በአካባቢው በሚገኙ የጸጥታ ሀይሎቻችን ድባቅ እየተመታ መሆኑንና ለገዛ ወገኑ እና አባላቱ ከሰውነት ክብረ ያለፈ ዘግናኝ ተግባር እየፈፀመ እንደሚገኝ በአካባቢው የሚገኝ ሻለቃ ም/አዛዥ ሻምበል አየለ አለሙ ተናግረዋል፡፡

አሸባሪ ሃይሉ አስገድዶ እድሜያቸው ያልደረሱ ህፃናትን ወደ እሳት እየማገደ የሚገኝ ሲሆን የሽብር ቡድኑ የሞቱ አባላቶቹንም አንስቶ በክብር ከመቅበር ይልቅ የአራዊት ሲሳይ እና በጎርፍ አስክሬናቸው በየቦታው እንዲወሰድ በማድረግ ከሰውነት ያፈነገጠ አረመኔያዊነት የተሞላበት ተግባር ከመፈፀሙም በላይ ለገዛ አባላቱ እንኳን ክብር የሌለው በመሆኑ ሰራዊታችንም አስክሬኖቹን በማንሳት የመቅበር ስራ እየሰራ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ጁንታው ታገልኩለት እና ለጥቅሙ ቆሜለታለሁ የሚለውን የትግራይ ህዝብ እንደሚለው በተግባር ከማገልገል ይልቅ ለስልጣን ጥማቱ ሲል ወጣቱን እና ህፃናቱን በአደንዛዥ ዕፅ እና ሀሺሽ አንገታቸው ላይ በማሰር ወደ አፈሙዝ ላንቃ በመማገድ ታሪክ ተረካቢ ትውልድ እንዳይኖር እያደረገ መሆኑን በገሀድ እያሳዬ ነው ሲሉ ሻ/ል አየለ አለሙ አክለዋል፡፡

ህዝባችን ከኋላ ደጀን በመሆን በቁሳቁስም በሞራልም እያደረገልን ያለው ድጋፍ ከምንም በላይ የሚመሰገን ነው ሰራዊቱም በጀግንነት እና በታታሪነት የአሸባሪውን ሃይል አከርካሪ በመስበር ግብአተ መሬቱን እንድናፋጥን የሚያደርገን በመሆኑ ህዝባችንም በጁንታው የሽብር በሬ ወለደ ወሬ መደናገር የለበትም በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ፡፡

ጥቁር ውሃ

May be an image of outdoors

በከሃዲው የቀድሞው የ31ኛ ክ/ጦር አዛዥ አሸባሪው ከበደ ፍቃዱ የሚመራው የጠላት ጦር በወልድያ መግቢያ ጥቁር ውኃ አካባቢ ተደምስሷል፡፡ በዚህ ውጊያ ከ70 በላይ የጠላት ኀይል ሊደመሰስ ችሏል ፡፡ ጀግኖቹ የ21ኛ ክ/ጦር የሰራዊት አባላት የድል ችቦዋቸውን ከፍ አድረገው እያውለበለቡ በጥቁር ውኃ ላይ ሌላ አዲስ ታሪክ መስራታቸውን ቀጥለዋል።

ክፍለ ጦሩ በጥቁር ውሃ አካባቢ በወገን ጦር ላይ ጥቃት ለማድረስ በእንቅስቃሴ ላይ የነበረውንና በከሃዲው ጀነራል ከበደ ፍቃዱ የሚመራውን የጠላት ጦር በአስደናቂ የወታደራዊ ስልት መደምሰስ መቻሉን የ211ኛ ብርጌድ ዋና አዛዥ እና ም/አዛዥ ለኦፕሬሽናል አስታውቀዋል። አዛዦቹ እንዳስታወቁት ፣ በሰራዊቱ እልህና ቁጭት አስደናቂ የጀግንነት ተግባር ፈፅመናል ብለዋል።

ክ/ጦሩ በጥቁር ውሃ አካባቢ ለይ በፈፀመው የጀግንነት ውሎው ከ70 በላይ የጠላት ሃይል ሲደመሰስ ፣ 19 ክላሽን ኮቭ መሣሪያ ፣ 5 ስናይፐር እና በርካታ ቁጥር ያላቸው ከከባድ እስከ ቀላል የጦር መሳሪያዎች ተማርከዋል። ሠራዊቱ አሁንም የህልውና ዘመቻውን በአስተማማኝ የጀግንነት መንፈስ ለመወጣት ከመቸውም ግዜ በላይ ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል ሲል የሀገር መከላከያ ሠራዊት አስታውቋል።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“…የማይተኩስ ነገር ግን ወደ ጠላት ምሽግ ሰተት ብሎ ለመግባት የሚሞክር ተዋጊ” የትህነግ “ስልጡን” የውጊያ ስልት
በጅግጅጋ- አሸባሪውን ህወሓት የሚያወግዝ፣ የመከላከያ ሠራዊትን የሚያገን ሰልፍ ተካሄደ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2