Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  “ህወሓት በኮምቦልቻ ከተማ ሰርጎ በመግባት ዛሬ ሌሊቱን ከ100 በላይ የከተማዋን ወጣቶችን አሰልፎ ጨፍጭፏል”
News

“ህወሓት በኮምቦልቻ ከተማ ሰርጎ በመግባት ዛሬ ሌሊቱን ከ100 በላይ የከተማዋን ወጣቶችን አሰልፎ ጨፍጭፏል”

Ethioreview newsEthioreview news—November 1, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አማጺው ቡድን በኮምቦልቻ ከተማ ከ100 በላይ ወጣቶችን ገድሏል ማለቱን ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ዘገበ። 

“ህወሓት በኮምቦልቻ ከተማ ሰርጎ በመግባት ዛሬ ሌሊቱን ከ100 በላይ የከተማዋን ወጣቶችን አሰልፎ ጨፍጭፏል” ሲል ኢቢሲ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚንስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ጠቅሶ ዘግቧል።

ሚንስትሩ ህወሓት “ሰርጎ በገባባቸው” ደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች የግል እና የመንግሥት ሃብቶችን እየዘረፈ እና እያወደመ ነው ስለማለታቸው ተዘግቧል። 

በኢቢሲ ዘገባ ላይ ሚንስትሩ ህወሓት ወደ ደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች “ሰርጎ ገብቷል” ከማለታቸው ውጪ ሁለቱ ከተሞች በየትኛው አካል ቁጥጥር ሥር እንደሚገኝ አልተገለጸም። 

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

በዚህም ሁለቱ የደቡብ ወሎ ከተሞች ደሴ እና ኮምቦልቻ እስካሁን በየትኛው አካል ቁጥጥር ሥር እንደሚገኙ በግልጽ ማወቅ አልተቻለም። 

ባለፈው ሳምንት ለቀናት ሲካሄድ የነበረው ውጊያ የህወሓት ኃይሎች ደሴን ለመያዝ የፌደራሉ ሠራዊትና አጋሮቹ ደግሞ ከተማዋን ለመከላከል ሲያደርጉት የቆየ ነው። 

በዚህም ከባድ መሳሪያ ወደ ከተማዋ በተደጋጋሚ መተኮሱንና በነዋሪዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን የከተማዋ ባለሥልጣናትና ነዋሪዎች ለቢቢሲ መግለጻቸው ይታወሳል።

ለቀናት ሲካሄድ የነበረው ከተማዋን ለመከላከልና በቁጥጥር ስር ለማስገባት በተደረገው ውጊያ በሳምንቱ ማብቂያ ላይም ቀጥሎ ቅዳሜ ዕለት በደሴ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች ተኩስ መሰማቱንና የአማጺያኑ ተዋጊዎች መታየታቸውን ነዋሪዎች ለተለያዩ የዜና ወኪሎች ገልጸዋል። 

አርብ አመሻሽ ላይ በአንዳንድ የደሴ ከተማ አካባቢዎች ላይ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መቋረጡ የተነገረ ሲሆን ከቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ጀምሮ ደግሞ በደሴ ከተማ የስልክ ግንኙነት በመቋረጡ መረጃ ለማግኘት አስቸጋሪ ሆኗል። 

ከጥቅምት ወር መጀመሪያ አንስቶ ከደሴ ከተማ ውጪ ባሉ የደቡብ ወሎ አካባቢዎች ውጊያ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ጦርነቱ ወደ ከተማዋ ተቃርቦ ቆይቷል።

በአማራ ክልል ውስጥ ከሚገኙ ትላልቅ ከተሞች አንዷ የሆነችው ተራራማዋ የደሴ ከተማ ጦርነቱ ሲስፋፋ ከሰሜን ወሎ የተፈናቀሉ በርካታ ሰዎችን በተፈናቃይነት አስጠልላ መቆየቷ ይታወሳል። 

ባለፈው ሳምንት አማጺያኑ ወደ ከተማዋ መቃረባቸው ሲነገር ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመከላከያ ኃይል እንዲሁም ከተለያዩ የአማራ ክልል አካባቢዎች ሚሊሻዎችና ኢመደበኛ የሆኑ ታጣቂዎች ሲሰማሩ መቆየታቸውን የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ሲዘግቡ ነበር።

ቅዳሜ ረፋድ ላይ በከተማዋ የነበረው እንቅስቃሴን በተመለከተ ቢቢሲን ጨምሮ ለተለያዩ የዜና ምንጮች ነዋሪዎች እንደገለጹት በከተማዋ ዙሪያ የተኩስ ድምጽ እንደሚሰማና እንቅስቃሴዎች መቆማቸውን ገልጸው ነበር።

የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት በዚያኑ ዕለት የመንግሥት ወታደሮች ከከተማዋ እያፈገፈጉ መሆናቸውን ሲዘግብ ሮይተርስ የዜና ወኪል ደግሞ የአማጺያኑን ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳን ጠቅሶ ከተማዋ በህወሓት ኃይሎች እጅ መግባቷን ዘግቦ ነበር። 

ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ የአገሪቱ ሠራዊት የፀረ ማጥቃት እርምጃ በመውሰድ በደሴ ከተማ ላይ የተሰነዘረውን ጥቃት መክቶ “ደሴን ለመያዝ አሰፍስፎ የመጣውን ወራሪ ኃይል በመመከት” ከተማዋ በመንግሥት ቁጥጥር ስር እንዳለች ገልጾ ነበር።

ህወሓት በበኩሉ በደሴ በኩል በተካሄደው ውጊያ የበላይነት ይዞ ከተማዋን ከመቆጣጠሩ ባሻገር ከደሴ ከ20 ኪሎ ሜትሮች ርቃ የምትገኘውን የኢንዱስትሪ ከተማዋን ኮምቦልቻን ተዋጊዎቻቸው መቆጣጠራቸውን ገልጸዋል። 

እነዚህ የደቡብ ወሎ ዞን ዋነኛ ከተሞችን በተመለከተ በመንግሥት በኩል የተሰጠ ግልጽ ማብራሪያ ባይኖርም የመንግሥት ኮሙኒኬሽን እሁድ ዕለት ባወጣው መግለጫ ላይ ከአማጺያኑ ጋር የሚደረገው “ከባድ ውጊያ” እንደቀጠለ አመልክቷል። 

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ኃላፊ አንቶኒ ብሊንከን ሰኞ ረፋድ ላይ በትዊተር ገጻቸው ላይ አገራቸው እየወጡ ባሉ “ህወሓት ደሴንና ኮምቦልቻን መያዙን የሚያመለክቱ ሪፖርቶች” እንዳሳሰባት ገልጸዋል።

ጨምረውም የቀጠለው ውጊያ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለውን አስከፊ ሰብአዊ ቀውስ የሚያራዝመው በመሆኑ፣ ሁሉም ወገኖች ወታደራዊ ዘመቻቸውን አቁመው ካለቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም ድርድር መጀመር አለባቸው ብለዋል። 

መረጃ 

እነዚህ ከተሞች አሁን ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተ ከአማጺው ወገን ከሚሰጠው መረጃ እና በማኅበራዊ መገናኛ መድረኮች ከሚባለው ውጪ የስልክ አገልግሎት በመቋረጡ አስተማማኝ መረጃ ከነዋሪዎች ማግኘት አልተቻለም።

ከመንግሥት በኩልም ቢሆን ከባድ ውጊያ እየተካሄደ ከመሆኑ ውጪ ከተሞቹ ያሉበትን ሁኔታ የሚገልጽ መረጃ ማግኘት አዳጋች ሆኗል።

ከዚህ ውጪ በወሎ ግንባር እየተካሄደ ያለውን ከባድ ውጊያ ተከትሎ የአማራ ክልል መንግሥት ሁሉም መዋቅር እንዲሁም አቅሙ ያለው ነዋሪ “የህልውና” ያለውን ዘመቻ እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርቧል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም ጦርነቱን አስመልክተው እሁድ ምሽት ባስተላለፉት መልዕክት የአገሪቱ የመከላከያ ሠራዊት “በኢትዮጵያ ላይ የተከፈተውን ጥቃት ለመመከት በሁሉም ግንባሮች ተሰልፏል” በማለት “ሠራዊቱ በምድርና በአየር እየታገዘ እንዳይነሳ አድርጎ እየሰበረው ይገኛል” ብለዋል።

ጨምረውም አማጺው ያለውን ኃይል በሙሉ አሰባስቦ በወሎ ግንባር በኩል መሰለፉንና “ሰፊ ቁጥር ያለው ኃይሉን ያጣ ሲሆን፣ ጀግናው ሠራዊታችን በሁሉም መስክ መስዋዕትነትን ከፍሎ እየተጋደለ ነው” ሲሉ ውጊያው መቀጠሉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አመልክተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁሉም በዘመቻው እንዲሳተፍ ጥሪ ባቀረቡበት በዚህ መልዕክታቸው “ሕዝባችን የክት ጉዳዩን ለጊዜው አቆይቶ. . . ማናቸውንም መሣሪያና አቅም ይዞ፣ በሕጋዊ አደረጃጀት መዝመት አለበት” ሲሉ ሁሉም በሚችለው ሁሉ የበኩሉን እንዲያበረክት ጠይቀዋል። 

ትግራይ ውስጥ ተቀስቅሶ ወደ አማራና አፋር ክልሎች የተስፋፋው ጦርነት ወራትን ባስቆጠረበት ጊዜ በሰሜን ጎንደር፣ በደቡብ ጎንደርና በአፋር ክልል ውስጥ የነበሩት ጦርነቶች ለረጅም ጊዜ የቆዩ አልነበሩም።

ነገር ግን በሰሜ እና በደቡብ ወሎ ያለው ጦርነት ግን እየተጣናከረና እየተቀዛቀዘ እስካሁን ዘልቋል። በዚህም ሳቢያ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ግጭቱን በመሸሽ በተለይ በደሴ ከተማ ተጠልለው ቆይተዋል።

አሁን በደሴ ከተማ ያለው ሁኔታ በውል አለመታወቁ ከነዋሪወቹ ባሻገር ተፈናቅለው በችግር ላይ የሚገኙትን ሰዎች ለከፋ ሰቆቃ ሊዳርጋቸው እንደሚችል ተሰግቷል።

BBC Amharic

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የመረረውን ትግል ታግለን፣ ጣፋጩን ድል እናጣጥማለን።
Ethiopian Government Says TPLF Killed Over 100 Young Residents of Seized City
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2