Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የአጋዚ ሰራዊት አዛዥ ቤተሰቦቻቸው ባሉበት በድንገት ህይወታቸው አለፈ – የህክምና ምርመራ ውጤት ይፋ አልሆነም
News

የአጋዚ ሰራዊት አዛዥ ቤተሰቦቻቸው ባሉበት በድንገት ህይወታቸው አለፈ – የህክምና ምርመራ ውጤት ይፋ አልሆነም

Ethioreview newsEthioreview news—May 4, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በትግራይ ሰፍሮ በነበረው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ ትህነግ ” መብረቃዊ” ሲል የሰየመውና መንግስት “ክህደት” ሲል ይፋ ያደርገው ወንጀል ሲፈጸጸም አዲስ አበባ ተቀምጠው የግንኙነት መስመር በመቆለፍና በማቋረጥ ከፍተኛ የሀገር ክህደት ወንጀል ተከሰው የፍርድ ሂደታቸውን እየተከታተሉ ያሉት የጦር መኮንን ሞቱ። ትህነግ ከመቀለ “ተገለዋል” ቢልም በስፍራው ነበሩ የተባሉት የቤተሰብ አካላት እስካሁን መረጃ አልሰጠም።

የቀድሞ የመከላከያ ሚኒስቴር የኮሚኒኬሽን ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ ኃላፊ ሜ/ጀ ገብረመድህን ፍቃዱ በእስር ላይ እያሉ ሰኞ ሚያዝያ 24/2014 ዓ.ም ሕይወታቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር እየተነጋገሩ ባለበት ወቅት በድንገት ራሳቸውን እንደሳቱ ተመልክቷል። የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን “ከረፋዱ ሦስት ሰዓት ተኩል አካባቢ በቤተሰብ ጥየቃ ሰዓት ባለቤታቸው እና ልጃቸው አስጠርተዋቸው እያወሩ እያለ በድንገት በመውደቃቸው ወዲያውኑ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ሕክምና ቦታ ቢወሰዱም ህይታቸው አልፏል” ሲል ሂደቱን በፌስ ቡክ አመልክቷል።

ማረሚያ ቤቱ ቤሰቦቻቸው ባሉበት ወይም እያዩ በድንገት መውደቃቸውንና ከቤተሰቦቻቸው ጋር በአንድነት ወደ ህክምና መሄዳቸውን ጠቅሶ ህልፈታቸውን ይፋ ማድረጉን ቢቢሲና ቪኦኤ ዘግበው የሟችን ባለቤት ማግኘት አለመቻላቸውን አመልክተዋል። ዘመድ ያነጋገረው ቢቢሲ “ጤነኛ መሆናቸውን አውቃለሁ” ማለቷን አመልክቷል።

የፌደራል ማረሚያ ቤት በቅጽል ስማቸው “ወዲ ነጮ” በሚል ስያሜ የሚጠሩት የቀድሞ የአጋዚ ሰራዊት ዋና አዛዥ ህልፈት ቤተስብ ባለበት በድንገት ወደቀው ወደ ሃኪም ቤት ቢወሰዱም ሊተርፉ እንዳልቻሉ መግለጹን ተከትሎ እስካሁን ቤተሰብ ያለው ነገር የለም። ማረሚያ ቤት የሰጠውን ቃል “ሃሰት ነው። እኛ በቦታው አልነበርንም። ስማችን ያለ አግባብ ተጠቅሷል…” በሚል ሲከሱም ሆነ መረጃውን ሲያስተባብሉ አልተደመጠም።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ዘርዝር መረጃ ለመስጠት ቤተሰብ ምን አልባትም በድንጋጤና በትኩስ ሃዘን ላይ መሆናቸው እንደ ምክንያት ቢቀርብም ትህነግ ሩቅ ሆኖ ባለው መልኩ የተፈጸመ ነገር ስለመኖሩ ይህ እስከታተመ ድረስ የተሰጠ መረጃ የለም።

ትህነግ ባወጣው መግለጫ የቀድሞው የትህነግ ታማኝ የአጋዚ ሰራዊት አዛዥ የሜጀር ጀነራል ገብረመድህን ሕይወት በማለፍ ሐዘን እንደተሰማው አስታውሶ፣ ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናት ይሁን ብሏል። አያይዞም የፌዴራል መንግሥት ወንጅሎ ጉዳዩን ማንነትን ላይ ያነጣጠረ ነው” ብሎታል። ሲቀጥልም “የህልፈታቸው መንስኤ በገለልተኛ አካል ይጣራልኝ” ብሏል። ማረሚያ ቤቱ የከፍተኛ መኮንኑ ህልፈት ምክንያቱ በሃኪም እየተጣራ መሆኑንን አመልክቷል።

የሜጄር ጄኔራሉን ሕልፈተ ሕይወት በተመለከተ ከቤተሰቦቻቸውና ከጠበቃቸው መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ሊሳካለት እንዳልቻለ ያስታወቀው ቪኦኤ. በ97 ምርጫ ወቅት በርካታ ሰላማዊ ዜጎችን ጭንቅላት እየመታ ሲደፋ የነበረው አጋዚ ሰራዊት አዛዥ የነበሩት ሜጀር ጀነራል ገ/መድህን ፍቃዱ፣ የመከላከያ ሚኒስቴር የኮሚኒኬሽን ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ ኃላፊ በነበሩበት ወቅት፣ ጥቅምት 24/2013 ዓ/ም መከላከያ ሰራዊቱ ከሰሜን ዕዝ ጋር የነበረውን የሬዲዮ ግንኙነትን በማቋረጥ እንዲሁም የሬዲዮ መገናኛ መሳሪያ ለህወሓት ወታደራዊ ቡድን አሳልፈው ሰጥተዋል በሚል በዓቃቤ-ህግ የቀረበባቸውን ከፍተኛ የሀገር ክህደት ክስ ሂደት በመከታተል ላይ ነበሩ ሲል የክሳቸውን ጭብጥ አስታውሷል።

በቀድሞ የመከላከያ መኮንኖች የክስ መዝገብ ላይ 1ኛ ተከሳሽ የሆኑት ሜጀር ጀኔራሉ ሕይወታቸው በድንገት ማለፉን ተከትሎ በሌሎች ተከሳሾች ላይ የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመስማት ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን የፍትህ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረሽብርና የህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ቀሪ የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመስማት ለዛሬ ተይዞ በነበረው ተለዋጭ ቀጠሮ፣ 7ኛ እና 15ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክሮች ቃላቸውን ለመስጠት ተገኝተው ቃለ መሀላ ፈፅመው ነበረ ብሏል ሚኒስቴሩ በፌስቡክ ገጹ ባወጣው መረጃ፡፡

ይሁንና የ1ኛተከሳሽ ድንገተኛ ሕልፈተ ሕይወትን ተከትሎም በክስ መዝገቡ የተካተቱ ሌሎች ተከሳሾችና የተከሳሽ ጠበቃ የሟች አስከሬን ባልተቀበረበት ሁኔታ ዐቃቤ ህግ የሚያሰማብንን ምስክሮች ለመከላከል የሚያስችል የስነ ልቦና ዝግጅት ስለሌለን ተለዋጭ ቀጠሮ ይሰጠን ሚል ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቶ፣ ቀሪ የዐቃቤ ህግ ምስከሮችን ለመስማት ከግንቦት 08 እስከ ግንቦት 12/2014 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ገልጿል፡፡

በመዝገቡ የተካተቱት ሌሎች ተከሳሾች አጃቢ ተመድቦልን በቀበር ሥነ ስርዓቱ ላይ እንድንገኝ ለማረሚያ ቤት ደብዳቤ ይፃፍልን ሲሉም ፍርድ ቤቱን የጠየቁ ሲሆን፣ ዐቤ ሕግ በበኩሉ ሁኔታው “ያልተለመደና ለደህንነት አስጊ” መሆኑን ገልፆ ማረሚያ ቤትም ጉዳዩን ቢመለከተው መልካም ነው ሲል ማሳወቁ ተመላክቷል።

በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረ ሽብርና የህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በፅ/ቤት ከተወያየ በኋላ በፅ/ቤት በኩል ትዕዛዝ እንደሚሰጥበት ገልጾ፣ ሌሎቹ ተከሳሾች በቀብሩ ላይ ለመገኘት ያላቸውን ፍላጎት በፅሑፍ እንዲያቀርቡና መወሰኑንም ነው ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በአስር ዓመት 4.4 ሚሊዮን ቤቶች ይገነባሉ
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት ድንበር አካባቢ በርካታ የፀጥታ ኃይል አሰማራች
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2