Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  መንግስ የጸጥታ ሃይሎች ለየትኛውም ዓይነት ትንኮሳ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ ማድረጉን አስታወቀ
News

መንግስ የጸጥታ ሃይሎች ለየትኛውም ዓይነት ትንኮሳ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ ማድረጉን አስታወቀ

Ethioreview newsEthioreview news—May 15, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ለየትኛውም አይነት የጦርነት ትንኮሳ ምላሽ ለመስጠት የጸጥታ ኃይሉ ከየትኛውም ጊዜ በበለጠ መልኩ ዝግጁ መሆኑን መንግስት አስታወቀ። ይህ የተገለጸው የአማራ ክልልና በተለይም የውልቃይት ጠገዴ አስመላሽ ኮሚቴ የአንድ ወር ስንቅ በማዘጋጀት “ክተት” ሲባል እንዲነሳ መታዘዙን ተከትሎ ነው። ትህነግ በበኩሉ ሰሞኑንን ከበባውን ለማስከፈት ጦርነት ለመክፈት ከህዝብ ጋር ተወያይቶ መስማማቱን በቪኦኤ በኩል ማስታወቁ ይታወሳል። የሰላም አማራጭንም እንደ መጀመሪያ አማራጭ እንደሚያይ አመልክቶ ነበር።

ሰሞኑንን በተለያዩ ግንባሮች በመዘዋወር የመከላከያ አባላትን የጎበኙትና ያነቃቁት ጠቅላይ ሚኒስትር የጦርነትን አስከፊነት በማጉላት፣ በኢትዮጵያ ከተመጣ ግን መከላከያ የተለመደውን ክንዱን በተንኳሾች ላይ እንደሚያሳርፍ በግልጽ ሲናገሩ ሰንበተዋል። በተመሳሳይ ለዓለም አቀፍና ዲፕሎማቶችና ለአሜሪካ አምባሳደር መንግስት “ምከሩልን” ማለቱንም ውጭ ጉዳይ አስታውቋል።

በጦርነት የትግራይን ህልውና እንደሚያስጠብቁ ይፋ ያደረገው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር፣ ሕዝቡ ከጎኑ እንደሚሰለፍ ማረጋገጡን ቢያስታውቅም ሱዳን ፖስት ከትናንት በስቲያ ትህነግ በግድ የተመለመሉ ሲጠፉ እየያዘ ማሰሩን ከሶስት ሰዎች በኢሜል ደረሰኝ ሲል መዘገቡ ያታወሳል።


TPLF detaining civilians fleeing forced conscription

In an e-mail sent to Sudans Post this morning, three Tigrayans living in Amsterdam, the Netherlands, said seven of their relatives and five of their friends were arrested at Adi Ramet village last Monday by Tigray forces after trying to flee forced conscription to neighboring Sudan.


More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ትህነግ አስገድዶ ወደ ግዳጅ ያስገባቸው ምልምሎች መካከል ለመሸሽ የሞከሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን እያሰረ መሆኑን ዘመዶቻቸው እንደነገሩት ያመለከተው የሱዳን ፖስት ዘገባ ትህነግ ከፍተኛ የፖለቲካና ወታደራዊ መሪዎችን ያሳተፈ ቅስቀሳ በማድረግ ለጦርነት እየተዘጋጀ መሆኑን የሚያመለክቱ መረጃዎች እየወጡ መሆኑንን አመልክቷል።

ሱዳን ፖስት ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ሦስት የትግራይ ተወላጆች በኢሜይል መልዕክት አድርሰውኛል ብሎ እንደዘገበው ትህነግ የሚያደርገው ጦርነት ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግሥት ጋር ብቻ ሳይሆን የክልሉን ሰላማዊ ዜጎች በማሰር ትርጉም የለሽ ተግባር እየከወነ ማለታቸውን አስታውቋል።

“በመቶዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆችና ሰላማዊ ዜጎች የሕወሓትን የሽብር ተግባር ለመቀላቀል ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሲታሰሩ ይህ የመጀመሪያ አይደለም” ያሉት ነዋሪዎቹ ዓለም ዐቀፉ ማኅበረሰብ ትህነግ ጦርነት ውስጥ እንዳይገባና ሰላምን እንዲቀበል ጫና ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መጠየቃቸውን ዘገባው አመልክቷል። ከላይ ሙሉውን ያንብቡ። የመንግስት ኮሙኒኬሽንን ጠቅሶ ኢፕድ ከታች ያለውን ተያያዥ ዜና አስፍሯል።

መንግሥት ለሕዝብ ተቆርቋሪ መስለው አፍራሽ ተልዕኮ በማንገብ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።እየተስተዋለ ያለውን የኑሮ ውድነት ለመቅረፍ መንግሥት የአጭርና የረጅም ዕቅድ ተነድፎ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ በአገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ትናንት በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ መንግሥት በመላ አገሪቱ ሰላምን ለማስፈን በሰራው ተግባር በአብዛኛው የአገሪቱ አካባቢዎች አንጻራዊ ሰላም ማስፈን ተችሏል። መንግሥት ለሕዝብ ተቆርቋሪ መስለው አፍራሽ ተልዕኮ በማንገብ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ ይቀጥላል።

ለሕዝብ ተቆርቋሪ መስለው አፍራሽ ተልዕኮ በማንገብ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ መንግሥት የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹት ለገሰ ቱሉ (ዶክተር)፤ የግጭት ነጋዴዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ መንግሥት ያስጠነቅቃል። በተለያየ መንገድ የሕዝብን ሰላም የሚያውኩ ቡድኖች ከአሸባሪዎቹ ሸኔና ሕወሓት ተለይተው የማይታዩ በመሆናቸው እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት መንግሥት ለየትኛውም አይነት የጦርነት ትንኮሳ ምላሽ ለመስጠት የጸጥታ ኃይሉ ከየትኛውም ጊዜ በበለጠ መልኩ ዝግጁና አስተማማኝ በሆነ ቁመና ላይ ይገኛል ብለዋል።

እንደ ዶክተር ለገሰ ገለጻ፤ መላው የጸጥታ መዋቅር በወሰደው የተቀናጀ ኦፕሬሽን የአገሪቷን ጸጥታ ለማወክ ከሰሞኑ ብቻ በአዲስ አበባ፣ በሶማሌ ክልል በተለያዩ ዞኖች፣ በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ሀረርጌና በምስራቅ ባሌ ለሽብር ተግባር የተሰማሩ 45 የአልሸባብ የሽብር ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ነው።

ከሽብር ቡድኑ አባላት 105 ክላሽ እንኮቭ ጠመንጃ፣ 13 ብሬል፣ 25 አረቤጅ፣ 25 ሳጥን የተለያዩ መጠን ያላቸው ጥይቶች፣አራት መትረየስ፣ አራት ስናይፐር መሳሪያዎች ተይዘዋል። በተጨማሪም በየቤተ እምነቶች የተቀበሩ ፈንጂዎች፣ የእጅ ቦንቦችና የነፍስ ወከፍ መሳሪዎች በሚሰጥ ጥቆማ እየተሰበሰቡ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

እንደ ሚኒስትሩ ማብራሪያ፤ እየተከናወነ ባለው ህግ የማስከበር እርምጃ በኦሮሚያ ክልል በጉጂ፣ በወለጋና በሌሎች አካባቢዎች ላይ በሚንቀሳቀሰው ሸኔ ላይ በተወሰደ ኦፕሬሽን በርካታ የቡድኑ አባላት ተደምስሰዋል፤ ተማርከዋል፤ በርካታ ትጥቆችና ተተኳሾችም በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የመንግሥትን የሕዝብን ሰላምና ደህንነት የማረጋገጥ ስራ በመቃወም ድምጻቸውን የሚያሰሙ አንዳንድ አካላት መኖራቸውን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ እነዚህ አካላት ወይ ወደ ሰላም መንገድ አሊያም ወደ ቡድኖቹ መግባትና ጎራቸውን መለየት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በትግራይ ክልል ያልተገደበ የሰብአዊ እርዳታ እንዲቀርብ መንግሥት አሁንም ቁርጠኛ አቋም እንዳለውና በዚያ ልክም እየሰራ መሆኑን ያስታወሱት ሚኒስትሩ፤ ባለፈው ሳምንት ብቻ 165 ከባድ ተሽከርካሪዎች መቐሌ መድረሳቸውን ተናግረዋል።

አሸባሪው ቡድን ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ለማደናገር በወረራ ከያዛቸው አካባቢዎች እንደወጣ ቢያወራም አሁንም በአማራ ክልል በወረራ ከያዛቸው አዲአርቃይ፣ ጸለምት፣ አበርገሌ እና ሌሎች አካባቢዎች እንዲሁም ከአፋር ክልል ደግሞ ኮኖቫ፣ በራህሌ፣ አብአላና መጋሌ ወረዳዎች እንዳልወጣ ገልጸዋል።

ከበባውን ለማስከፈት ሲባል የግድ ወደ ጦርነት ለመግባት እገደዳለው በሚል በአሸባሪው ሕወሓት የሚገለጸው የጦርነት ጉሰማና ፉከራ ዳግም የትግራይን ወጣቶች ለማስጨረስ ያለመ መሆኑን የሚያመለክት መሆኑን ገልጸው፤ ይህን እኩይ እንቅስቃሴ የትግራይ ሕዝብ መታገል እንዳለበት አሳስበዋል።

መንግሥት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኑሮ ውድነትንና፣ የስራ አጥነት ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኘ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተስተዋለ ያለውን የኑሮ ውድነት ለመቅረፍ መንግሥት የአጭርና የረጅም ጊዜ እቅድ ነድፎ እየሰራ መሆኑንም ሚኒስትሩ በመግለጫው አስታውቀዋል።

ዋናው የኑሮ ውድነት ችግር ከምርት አቅርቦት ጋር የሚያያዝ በመሆኑ ችግሮችን ለመፍታት ስንዴ፣ ዘይት፣ አልሚ ምግብና ስኳር የመሳሰሉ ምግብ ነክ ፍጆታዎች በአጭር ጊዜ ለመቅረፍ በፍራንኮ ቫሉታ አሰራር የራሳቸውን የውጭ ምንዛሬ ተጠቅመው እንዲያስገቡ ፍቃድ ተሰጥቷል። በተጨማሪም በግዥ ስርዓቱ ላይ ያሉ መስተጓጉሎችን ለመቅረፍ እየተሰራ ስለመሆኑ ለገሰ ቱሉ (ዶክተር) በመግለጫቸው አመላክተዋል።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በትግራይ 5.2 ሚሊዮን ሕዝብ ዕርዳታ እየደረሰ ነው፤ ከሺህ በላይ የጭነት መኪኖች ታግተዋል፤ 76 ቢሊዮን ብር ወደ ትግራይ ተልኳል
ሕንድ ስንዴ ወደ ውጪ መላክ አቆመች
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2