Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  በአማራ ክልል መፈንቅለ መንግስት ታቅዶ ነበር
News

በአማራ ክልል መፈንቅለ መንግስት ታቅዶ ነበር

Ethioreview newsEthioreview news—May 23, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ለአማራ ክልል ሙሉ የጨለማ፣ ለመላው ፍትህ ወዳድ ዜጋ ሕመም የሆነው የሰኔ 15ቀን 2011 ዓ.ም ድራማ ጠባሳው ክፉ ነው። ይህ ጠባሳ ምርጥ የሚባሉ የአማራ ክልል መሪዎች፣ የኢትዮጵያን ልጆች የተገደሉበት ነው። በዚህ የዕብዶች ሂሳብ የደረሰው ጉዳት ዛሬ ድረስ ቁስሉ ያልሻረ ቢሆንም በድጋሚ ተመሳሳይ ድርጊት ለመፈጸም ዝግጅቱ ተጠናቆ እንደነበር ለዝግጅት ክፍላችን መረጃ ደርሷል።

በባሕር ዳር ከተማ በክልሉ መስተዳደር ጽህፈት ቤት ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት ፕሬዝዳንቱን ዶክተር አምባቸው መኮንን፣ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አቶ ምግባር ከበደ እና የርዕሰ መስተዳደሩ አማካሪ አቶ እዘዝ ዋሴ መገደላቸው ይታወሳል። በዚህ “መፍንቅለ መንግስት” በተባለ ሙከራ የወቅቱ የክልሉ ልዩ ሃይል አዛዥ ብ/ጄነራል አሳምነው ሃይሉን እየመሩ ወደ አስተዳደሩ ቢሮ መግባታቸው፣ ሁሉንም ጉዳይ እሳቸው ይመሩት እንደነበር ባልደረባቸውና ምክትላቸው ጀነራል ተፈራ በወቅቱ ምስክርነት መስጠታቸው ይታወሳል።

መረጃውን ያደረሱን እንዳሉት በአማራ ክልል በተመሳሳይ መፈንቅለ መንግስት ለማካሄድ በልዩ ሃይሉ ውስጥ ሰርጎ ለመግባትና ሃይሉን ለመቆጣጠር ሲሰራ እንደነበር ስለላው በደንብ ያውቅ ነበር። በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ጉዳዮች ክላስተር አስተባባሪ ዶክተር ሰማ ጥሩነህ ባይዘርዝሩትም የክልሉን ልዩ ሃይል ለማስከዳት፣ ከነትጥቁ እንዲኮበልል፣ መከላከያ ውስጥ ያሉ አባላትን ለማሸፈት ሲሰራ እንደነበር ሰሞኑን በአማራ ክልል ማስ ሚዲያ በግልጽ አስታውቀዋል።

“አደገኛ መዛባሪዎችና ሃብት ያካበቱ” ድልድይ ሆነው በሚሳተፉበት የአማራ ክልልን መንግስት በሃይል የመገልበጥ ዝግጅት ውስጥ እነማን፣ እንዴትና፣ ከነማን ጋር ይሰሩና ይዘጋጁ እንደነበር ስለላው ያውቅ እንደነበር ያመለከቱት የመረጃው ምንጮች፣ የሕግ ማስከበሩ ስራ ሲጀመር ቀድሞ የመከነ ተግባር መኖሩን አስታውቀዋል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

በእቅዱ መሰረት በባህር ዳር በለሊት የሚፈጸም የመፈንቅለ መንግስት እንዲካሄድ ታስቧል። ይሁን እንጂ ጊዜ አልመረጠም። ለዚህ ደግሞ ዋናው ምክንያት በባህር ዳር አንዳች ሙከራ ቢደረግ የመከላከያ ሃይል በቅጽበት እርምጃ ስለሚወስድና፣ መከላከያ ዙሪያ ክፈተት አለመገኘቱ የፈጠረው ስጋት ነው።

መፈንቅለ መንግስት አሳቢዎቹ የሰለጠኑ ታጣቂዎች ያላቸው ሲሆኑ በገንዘብና በሚዲያ ድጋፍ የሚደረግላቸው ናቸው። በውጭ አገር ባሉና አገር ቤት በተደራጁ ሚዲያዎች በተዘዋዋሪ ቅስቀሳ የሚሰራላቸው እንደሆኑ ለማንም የተሰወር እንዳልሆነ የመረጃው ባለቤቶች አመልክተዋል።

“አማራ ክልል ልክ እንደ ትግራይ የራሱ የሆነ ከመንግስት ቁጥጥር ውጭ የሆነ መከላከያ ማቋቋም አለበት” በሚል በ360 አዘጋጆች በተደጋጋሚ ቅስቀሳ ሲደረግ እንደነበር በማስታወስ፣ ይህንንም ተከትሎ ጎጃም አካባቢ በፋኖ ስም ኢመደበኛ የሆነ ሃይል ማደራጀት ከተጀመረ ዓመት ማለፉን የሚገልጹት ክፍሎች ” አሁን ሁሉም ነገር ከሽፏል” ሲሉ አብዛኞቹ መያዛቸውን ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ ብዛታቸውንና የአቅማቸውን መጠን አላብራሩም።

የተያዙ ያሉ ቢሆኑም ጭካ ገብተው ራሳቸውን የደበቁ መኖራቸውናና እነሱን ለመያዝ ዘመቻው እየተካሄደ መሆኑ ታውቋል። ክልሉም እንደሚገፋበት ይፋ አድርጓል። የህግ ማስከበሩ ዘመቻ በስፋት እየተካሄደ ባለበት ወቅት ነው ትህነግ “ምርኮኛ እለቃለሁ” ሲል የተናገረው። ወደ አማራ ክልል አስጠግቶ እንደሚለቃቸው ማስታውቁን ተከትሎ ቀይ መስቀል ጉዳዩን እንደማያውቀው፣ መንግስትም የሰለተኑ ሰርጎ ገቦችን የማስገባት ዓላማ ያካተተ ተግባር እንደሆነ አስታውቋል። ሰርጎ ገብ ማስገባት የተፈለገበት ዋና ምክንያት ከህግ ማስከበሩ ጋር ስለመያያዙ የተባለ ነገር የለም።

በአማራ ክልል መፍነቅለ መንግስት ለማካሄድ መታሰቡን አስመልክቶ የአዲስ አበባ ተባባሪያችን ለክልሉ ባለስልጣናት ቅርብ የሆኑ ወገኖችን ጠይቆ ” ሃሳቡ አላቸው። ግን እንቅስቃሴያቸው ሁሉ ከቁጥጥር ውጭ አልነበረም” ሲሉ ትዝብታቸውን እንደገለጹለት አስፍሯል። ” እንደው ነገሩ አንዳንዴም የውርጋጥ አይነትም ነው” ያሉትም አሉ።

አሁን ያለው የመንግስትም ሆነ የክልሉ ሃይል በደንብ የደረጀ እንደሆነ ጠቅሰው “መፈንቅለ መንግስት አይታሰብም። እንኳን መፍንቅለ መንግስት ትህነግ እንኳን ጦርነት አይከፍትም” ሲሉ አስተያየታቸውን አክለዋል። ዳያስፖራ ውስጥ ያሉት ወገኖች መሬት ላይ ያለው ሃቅ እንዳልገባቸውም አመልክተዋል።

ከመቶ የወልቃይት ሕዝብ የት እንደገባ አይታውቀም”

አሸባሪው ሕወሓት በወልቃይት፣ ጠገዴና ጠለምት ሕዝብ ላይ ላለፉት አርባ ዓመታት በፈፀመው ስልታዊና የተቀናጀ የዘር ማፅዳት ወንጀል ከእያንዳንዱ ቤተሰብ 29 ከመቶ ለህልፈት፣ 26 ነጥብ 5 ከመቶ ለስደት መብቃቱንና 19ነጥብ 5 ከመቶ ደግሞ የት እንደገባ እስካሁን እንደማይታወቅ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጥናት አመላክቷል። 12 የጅምላ መቃብር

አማራ ክልል ለሚንቀሳቀሰው ክፍል በዲያስፖራ በኩል ከፍተኛ ሃብት እየትሰበሰበ እንደሆነ ይታወቃል። ይህን ሃብት በተከታታይ ለመቀበል አገር ቤት እንቅስቃሴ መደረግ አለበት። በዚህም ሳቢያ ዘወትር የሁከት ዜና እንዲሰራጭ ይፈለጋል። በሚል የነገሩን አካሄድ በተደጋጋሚ የሚገልጹ ” ዲያስፖራውን ደም ተፍቶ የሚየገኘውን ብር በብከት እያስረከበ አገሩ ላይ ቢንዚን ይረጫል።” ሲሉ ወቀሳቸውን ይሰነዝራሉ።

በአማራ ክልል የተጀመረውን አመጽ ተከትሎ የትህነግ ደጋፊዎች በይፋ “እኔም የአማራ ትግል ይመለከተኛል” በሚል በማህበራዊ ገጾቻቸውና ሚዲያዎቻቸው እያስተጋቡ እንደሆነ ለማየት ተችሏል። የትህነግ አመራሮችም “አማራ ወገናችን” የሚል አሳብ ሲያራምዱ እየተሰማ ነው።

ትህነግ ከወራት በፊት አማራና አፋር ክልልን በወረረበት ወቅት በአማራ ክልል እናቶች፣ አረጋዊያን፣ ህጻናት ላይ ያደርሰው ዘግናኝ ተግባር ሰሞኑንንበመረጃ ተደግፎ በጎንደር ዩኒቨርስቲ አማካይነት ይፋ መሆኑ ይታወሳል። በወረራው ወቅት በጅምላ የተረሸኑ፣ የጥይት ማብረጃ የሆኑ፣ የተደፈሩ ሲትና ወንዶች፣ የት እንደደረሱ የማይታወቁ ሰዎች፣ የወደመና የተዘረፈ ንብረት በዝርዝር ነው ጥናቱ ያስረዳው። ይህን የፈጸሙና ያስፈጸሙ ሃይሎች በውጭ አገር ካሉ “አማራ ነን” ከሚሉ ወገኖች ጋር አንድ ላይ ሆነው “እኔም የማራው ትቃት ይመለከተኛል” እያሉ መሆኑንን ያስተዋሉ በነሱ ሳይሆን “አማራ ነን” በሚሉ ወገኖች ማዘናቸውንና ማፈራቸውን እየገለጹ ነው። ለነሱ ድጋፍ የሚሰጡትን ወገኖች ጤንነት እንደሚጠራጠሩም እየገለጹ ነው።

በአማራ ክልል ምን ታቅዶ እንደነበር የሚገባቸውና የሚያውቁ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው የህግ ማስከበሩን ስራ እየተቃወሙ ሲሆን፣ ሕዝብ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ የሰላም ያለህ፣ የህግ ያለህ በሚል ተቃውሞ ሲያሰማ ነበር።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Fuel poverty to hit British households, energy chief warns
በሕግ ማስከበር ዘመቻ ከ4 ሺህ በላይ ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ዋሉ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2