Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ሪፖርተር “አውድ በማሳት ደቡብ ሱዳን ወረራ ፈጸመች” ሲል ያሰራጨው ዜና እየተመረመረ መሆኑ ተሰማ
News

ሪፖርተር “አውድ በማሳት ደቡብ ሱዳን ወረራ ፈጸመች” ሲል ያሰራጨው ዜና እየተመረመረ መሆኑ ተሰማ

Ethioreview newsEthioreview news—June 27, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ሪፖርተር ጋዜጣ “አነጋገርኳቸው” ሲል ስማቸውን የጠቀሳቸው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ “ሪፖርተር የዜናውን አውድ ስቷል” ሲሉ ዜናው እንዲስተካከል ጠየቁ። የዜናው እንደምታ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ እጅግ በጥንቃቄ የምትይዘውን የደቡብ ሱዳንን ወዳጅነት የሚያጠላሽ በመሆኑ በጥብቅ እንደሚመረመር ተመለከተ። ለፅንፈኛ ሀይሎች አጀንዳ ጆሮ መስጠት እንደማይገባ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት አመልክቷል።

በግብጽ አቀናባሪነት ሱዳ በሚገኙ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር / ትህነግ ምልምሎችና ራሷ ሱዳን በጋር ኢትዮጵያ ላይ የሚፈጽሙትን ጥቃት በመቃወምና መተላለፊያ በመዝጋት ደቡብ ሱዳንን የኢትዮጵያ የችግር ወቅት ወዳጅ መሆኗ ይታወሳል። “አውዱን ስቷል” የተባለው ሪፖርተር ዜና እንዲስተካከልና ጉዳዩ የተለመደ የአርብቶ አደሮች የግጦሽ መሬት ግጭትና ዝርፊያ እንደሆነ ተመልክቷል።

“የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የወርቅ ማውጫ አካባቢን መቆጣጠራቸው ተሰማ” ሲል የሪፖርተሩ ዘጋቢ አማኑኤል ይልቃል “ታጣቂዎቹ የወርቅ ማውጫውን ከተቆጣጠሩ አንድ ወር ገደማ እንደሆናቸውና ወርቅ በማውጣት ሥራ እንደተሰማሩ፣ የክልሉ የሰላምና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል፡፡ በዚህም ምክንያት ክልሉ በባህላዊ መንገድ ሲያከናውን የነበረውን ወርቅ የማውጣት ሥራ እንዳቋረጠም የቢሮው ዋና ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ ለሪፖርተር ተናግረዋል” ሲል ጽፏል።

በተመሳሳይ አዲስ ዘመን የጠቀሳቸው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ ሪፖርተር በሰኔ 19/2014 እትሙ የደቡብ ሱዳን የታጠቁ ሀይሎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ወረራ ፈፅሟል ብሎ ያወጣው ዘገባ ስህተት እንደሆና የደቡብ ሱዳን የታጠቁ ሀይሎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የፈፀሙት ወረራ እንደሌለ አለመኖሩን በመጥቀስ ሪፖርተርን ከሰዋል። ዜናው አውዱን የሳተና የተሳሳተ በመሆኑ ማስተካከያ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። ይህ እስከታተመ ድረስ ሪፖርተር ማስተካከያ ወይም ለክሱ መልስ አልሰጠም።

የሪፖርተር የፊት ዜና ምስልና ርዕስ
More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

አቶ አንድነት አሸናፊ በመግለጫቸው ክልሉ እንደወትሮዉ በሁሉም አቅጣጫ ሰላም እንደሆነ ጠቅሰዉ፣በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምዕራብ ኦሞ ዞን ሱርማ ወረዳ ከደቡብ ሱዳን ጋር የሚያዋስን አካባቢ በመሆኑና በሁለቱም አካባቢዎች ያሉ የማህበረሰብ ክፍሎች አርብቶ አደር ስለሆኑ በግጦሽ ሳርና በውሃ ምክንያት አልፎ አልፎ ግጭትና ዝርፍያ ይፈፀማሉ ብለዋል።

አሁንም በአካባቢው የተስተዋለው በአርብቶ አደሮች የአኗኗር ባህሪይ የተከሰተ ግጭትና አለመግባባት መሆኑን ገልጸዉ ፣የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል እንደ ክልል ከመደራጀት በፊትም የነበረ እንደሆነ አቶ አንድነት አብራርተዋል። አክለውም በርወረራ ደረጃ የሚገልጽ እንዳልሆነ አመልክተዋል።

“አሁን ያለውን የሀገርቱን ወቅታዊ ሁኔታ በማሳበብ የሪፖርተር ጋዜጣ በሰኔ 19/2014 እትም ያወጣው ዘገባ ከነባራዊ ሁኔታና ከአውድ ያፈነገጠ ነው” ሲሉ ሃላፊው ተናግረዋል። “የአገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ በመንተራስ” ሲሉ ሪፖርተር ሆን ብሎ ዜና ማዛባቱን ያመለከቱት ሃላፊው ዜናው ሆን ተብሎ የተዛባበትን ሚስጢር አላብራሩም።

የዝግጅት ክፍላችን ያነጋገራቸው ባለስልጣን ” ከደቡብ ሱዳን ጋር ባለን ወሳኝ ህብረት ላይ ያነጣጠረ ዜና በመሆኑ ከህግና ከአገር ጥቅም አንጻር ዜናውና የዜናው እንደምታ ይመረመራል” ሲሉ ተናግረዋል። ዝርዝር መረጃ ከመስጠትም ተቆጥበዋል።

በድንበር አካባቢ የሚፈጠረውን ግጭትና አለመግባባትን የፌዴራልና የክልል መንግስት ከደቡብ ሱዳን መንግስት ጋር በውይይት ለመፍታት እንደ ከዚህ በፊቱ ሰፊ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝም ያስታወቁት አቶ አንድነት፣ የህዝቡን ደህንነትና ሰላም ማስጠበቅ የክልሉ መንግስት ቀዳሚ ተግባር ስለሆነ የክልሉን ህዝብና የፀጥታ ሀይሉን በማስተባበር በትኩረት እየሰራ መሆኑን ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከተናገሩት ለማወቅ ተችሏል።

በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች በአንፃራዊነት የተረጋጋ ሰላም እንዳለ የገለፁት አቶ አንድነት ፣ሰላም ለሁሉም ስለሚተርፍ ሁሉም የክልሉ ህዝብ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት የአከባቢውን ሰላም እንዲያስጠብቅና ለፅንፈኛ ሀይሎች አጀንዳ ጆሮ መስጠት እንደሌለበት ማሳሰባቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አመልክቷል።

ሪፖርተር የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ወረራ ማካሄዳቸውን ጠቅሶ ያሰራጨውን ዜና የተለያዩ የዩቲዩብ ዜና አቅራቢዎች እንዳለ በመውሰድ አሰራጭተውታል። አንዳንዶች ሰሞኑንን በወለጋ ከተፈጸመው ጭፍጨፋ ጋር በማያያዝ መንግስትን ዘልፈዋል። አገር ሲወረር ዝምታን የሚመርጥ ልፍስፍስ መንግስት እንደሆነ በመግለጽ ህዝብ እንዲቆጣ እንደ ተጨማሪ ግብአት የተጠቀሙበት አሉ።

ሪፖርተር በስፋት የዘገበው ዜና ” አውዱ የሳተ ነው” ሲሉ በአዲስ ዘመን ማስተባበያ የሰጡትን ሃላፊ ገልጾ በመሆኑ ምን አልባትም የሃላፊውን የድምጽ ማስረጃ ማቅረብ ግድ ሊሆን እንደሚችል ይጠበቃል። ዜናውን እየመረመረ ያለው ክፍል ሪፖርተር የጠቃሳቸውን ሃላፊም እንደሚያጠናቸው ለማወቅ ተችሏል።

በኢትዮጵያ በተለይም የኦን ላይን ሚዲያዎች ዜና ማረም፣ ይቅርታ መጠየቅና ማስተካከያ ማድረግ አልለመዱም። ከዚህ ቀደም ዋዜማ አባይ መሸጡንና ኢትዮጵያ ግብጽ ላቀረበችው ሰነድ እውቅና ሰጥታ መፈረሟን ቢጽፍም ማስተባበያ ሳይዘጥ ማለፉ ይጠቀሳል። “አክቲቪስ ነን” የሚሉትና የዩቲዩብ ገበያተኞችም እጅግ በርካታ ስህተት ቢሰሩም ይቅርታ ሲጠየቁ ተሰምቶ አያውቅም።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሮፌሰር – የዓለምፀሐይ መኮንን
ትህነግና ኦነግ ሸኔ በሕብረት የአማራ ሕዝብ ላይ ጥቃት እንደሚፈጽሙ ምስክሮች ገለጹ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2