Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የአየር ወለድ – በአዲስ ክብር
News

የአየር ወለድ – በአዲስ ክብር

Ethioreview newsEthioreview news—June 5, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

-የ61 አመቱ የእድሜ ባለፀጋ የአየር ወለድ ት/ቤት አሁናዊ ገፅታ፡፡

በኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል ማሰልጠኛ ማዕከል ስር ካሉ ትምህርት ቤቶች መካከከል አንዱ የአየር ወለድ ትምህር ቤት ነው፡፡ ይህ ትምህርት ቤት ተዋጊ አየር ወለዶችን በማሰልጠን ለ61 አመታት በብቸኝነት ያገለገለ የሀገር ባለውለታ ነው፡፡ ትምህርት ቤቱ አሁንም ይህንን ተግባሩን አጠናክሮ እየቀጠለ ሲሆን በአሁኑ ጊዜም ወደ ተሻለ ደረጃ እየተሸጋገረ ይገኛል፡፡

በአየር ወለድ ትምህርት ቤቱ ከትላንት እስከ ዛሬ ያሉ አሰልጣኞች እና አመራሮች እንዲሁም አዲስ እየገቡ ያሉ ተተኪ ሙያተኞች ታሪኩን እንዲህ አውገተውናል፡፡

በ1959 ዓ/ም ወደ ሠራዊቱ በመቀላቀል በአየር ወለድ ሰልጥነው ሀገራቸውን አገልግለዋል፡፡ ሌ/ኮሎኔል ደስታ ኃ/ገብርኤል ይባላሉ፡፡ በአሁኑ ጊዜም በሙያቸው ትምህርት ቤቱን ለማዘመን በሚደረገው ስራ ላይ የድርሻቸውን አስተዋፅኦ እያበረከቱ ይገኛሉ፡፡

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

በዚህ የአየር ወለድ ትምህርት ቤት ስልጠና የወሰዱት ሌ/ኮ ደስታ እንደነገሩን የአየር ወለድ ትምህርት ቤት የተቋቋመው በህዳር 19 ቀን 1953 ዓ/ም ነው፡፡ በወቅቱም 183 ባለሌላ ማዕረግተኛ እና አስር መኮንኖች ከሠራዊቱ ተመልምለው እስራኤል ሀገር በመሄድ የአየር ወለድ ስልጠና በመውሰድ ተመልሰው ሲመጡ የአየር ወለድ ትምህርት ቤት እንዲመሠረት ተደርጓል።

በዚህ ሁኔታ የተመሠረተው የአየር ወለድ ትምህርት ቤት ተዋጊ አየር ወለድ ሰራዊት ሲያሰለጥን ቆይቶ በ1969 ዓ/ም ስራ አቁሞ ነበር፡፡ ሆኖም ግን በ1973 ዓ/ም እንደገና ተከፍቶ የማሰልጠን ተግባሩን ማከናወን እንደጀመረ ሌ/ኮ ደስታ ነግረውናል።

በአንድ ሻምበል የተጀመረው የአየር ወለድ ክፍል ምስረታም በወቅቱ ወደ ብርጌድ ማድረስ የተቻለ ሲሆን ቀስበቀስም የአየር ወለድ ሠራዊት በክፍለ ጦር ደረጃ ማደራጀት እንደተቻለም ያስረዳሉ፡፡

ትምህርት ቤቱ በ1983 ዓ/ም በነበረው የመንግስት ለውጥ ምክንያት ተዘግቶ የቆየ ሲሆን ከ15 ዓመት በኋላ እንደገና በ1998 ዓ/ም በቀድሞ የአየር ወለድ አባላት አመካኝነት እንደገና ተከፍቶ የአየር ወለድ ከፍልን በማሰልጠን መልሶ ማደራጀት ተጀመረ፡፡

የአየር ወለድ ት/ቤት በ1953 ዓ/ም ከተመሰረተበት ወቅት ጀምሮ ከተራ ተዋጊ እስከ ከፍተኛ አመራሮችን ማፍራት የቻለ ት/ቤት ነው፡፡ ለምሳሌ ያህልም እነ ጄኔራል ደምሴ ቡልቶ፣ ጄኔራል ተመስገን ገመቹ፣ ጄኔራል ተስፋዬ ኃ/ማርያም፣ ጄኔራል ጌታቸው ናደውን እና በአሁኑ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ውስጥ የሚገኙትን የኮማንዶና የአየር ወለድ ኃይል አዛዥ ክቡር ሌ/ጄኔራል ሹማ አብደታን እና የመከላከያ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወደር የሌለው የጥቁር አንባሳ ሜዳይ ተሸላሚ ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላን ያፈራ የሀገር ባለውለታ ትምህርት ቤት ነው፡፡

ይህን ታሪክ ያወጉን ሌ/ኮሎኔል ደስታ ኃ/ገብርኤል ከ55 አመት በኋላም የመከላከያን የዘመናዊ ሠራዊት ግንባታን ለማሳካት በአየር ወለድ ት/ቤት እየተጉ ነበር ያገኘናቸው፡፡

የዛሬ 55 አመት የተመገብኩበትን ቤት ተመልሼ ዛሬ ልመገብበት በቅቻለው፡፡ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ ከዛሬ 61 ዓ/ም በፊት እንደተገነባ ቤቶቹ ጭምር ሳይቀር እስከ አሁን አገልግሎት ላይ ቆይቷል፡፡

አሁን ግን መከላከያ ባደረገው ሪፎርም እና ሠራዊትን ለማጠናከር ባለው ራዕይ ትምህርት ቤቱን በዘመናዊ መንገድ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ የስልጠና ወረዳ፣ የጅምናዚዬም መስሪያ መሰናክሎች ሳይቀሩ በአዲስ መልክ ተሰርተዋል፡፡

ዛሬ ኖሬ ትምህርት ቤቱ እንደ አዲስ ተገንብቶ ለውጥ ሲያሳይ በአይኔ በማየት ታላቅ ደስታ ተሰምቶኛል፡፡ ዘመኑን በሚመጥን ደራጃ ለሀገራችን የዘመነ የማይበገር ጠንካራ ተዋጊ የአየር ወለድ ሠራዊትን ማፍራቱን አጠናክሮ ይቀጥልበታል ብለውናል፡፡

የትምህርት ቤቱ ዋና አዛዥ የሆኑት ኮሎኔል አለማየሁ ጨዋቃ በበኩላቸው ከተቋማዊ ሪፎርሙ በኋላ በርካታ ስራዎች በማሰልጠኛው ተሰርተዋል፡፡ አሁንም ስራው ተጠናክሮ ቀጥለዋል፡፡ ት/ቤቱ በርካታ ተዋጊ አየር ወለዶችንም አሰልጥኗል፡ ያሰለጠናቸው ተዋጊ አየር ወለዶችን በህግ-ማስከበርና በህልውና ዘመቻው በመሳተፍ ውስብስብ ግዳጆችን በብቃት እና በታላቅ ጅግንነት የላቀ ውጤት አስመዝግበዋል፡፡

ለትምህርት ቤት ግንባታው ተቋሙም ከፍተኛ ትኩረት በማድርግ በአንክሮ እየተከታተለ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት ልክ እንደትላንቱ ብቻም ሳይሆን በተሻለ ደረጃ በየትኛውም ቦታ የትኛውንም ምድራዊ ፈተና በማለፍ ሀገራዊ ግዳጁን የሚወጣ አየር ወለድ ለመገንባት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡

የትምህርት ቤቱ ግንባታ አጠቃላይ ጥራት ተቆጣጣር የሆኑት መቶ አለቃ ኢ/ር በቃል ካሳሁን የትምህርት ቤቱ የጂምናዝየም ወረዳ ወቅቱን በመጠነ እና በዘመናዊ መንገድ በጥራት ተገንብቶ ማለቁን ገልፀውልናል፡፡

በእንጨት ተሰርተው የነበሩ በኮንክሪትና በብረት ተቀይረዋል፡፡ ይህም ከ50-60 አመት እንደሚያገለግል ታሳብ ተደርጎ የተገነባ ግንባታ መሆኑን ተናግሯል፡፡

የጥራት ተቆጣጣሪው ኢንጂነር በቃሉ ካሳሁን እና የፕሮጀክቱ ሳይት መሪ ፶/አለቃ ኢንጂነር ፋንታሁን ተማረ በጋራ በገለፁልን መሰረት የትምህርት ቤቱን ደረጃ ለማሳደግ እና ለስልጠና ምቹ ለማድረግም በአጠቃላይ ሰላሳ አራት ብሎክ ቤቶች በግንባታ ላይ ይገኛሉ፡፡

ግንባታውም የአሰልጣኝ፣ የመኮንኖች፣ የሰልጣኞች መኖሪያ፣ ቢሮዎች፣ ካፍቴሪያ፣ ሆስፒታል፣ ትላልቅ መጋዘኖችን፣ የአይ ቲ ክፍል፣ ቤተ-መፅሐፍት፣ የመማሪያ ክፍል የመሣሰሉትን ያካታተ ዘመናዊ ግንባታ ነው፡፡

፶/አለቃ ኢንጅነር ፋንታሁን ተማረ ይህንን ግንባታ እዚህ ደረጃ ያደርሰነው በብዙ ፈተናዎችን አልፈን ባደረግነው ከፍተኛ ጥረት ነው፡፡ የሚመለከተው አመራርም ማድረግ ያለበትን ጥረት ሁሉ አድርጓል፡፡

እንደሚታወቀው ሀገራችን ከነበረችበት ሁኔታ አኳያ ግንባታውን በሚፈለገው ደረጃ ለማስኬድም አዳጋች ሁኔታዎች ነበሩ፡፡ ሆኖም ግን ይህንን ተቋቁመን ግንባታውን ከ 70% በላይ አድረሰናል፡፡

በመጀመሪያ መሰረቱን ከማነጽ ጀምሮ የመሬቱ ተፈጥሮያዊ ሁኔታ ከታች አለታማ እና ድንጋያማ ስለነበረ ከማሽነሪ ጀምሮ ብዙ መስዋዕትነት አስከፍሎናል በማለት ሂደቱን በማስታወስ አውግተውናል፡፡

ፕሮጀክቱ ትውልድ የሚገነባበት ትልቅ ተቋም ነው፡፡ ዝም ብሎ የይድረስ የሚሰራ ስራ አይደልም፡፡ ከዚህ አኳያ ተቋማችንና እና ሀገራችን የጣሉብን ትልቅ ኃላፊነት መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ በዚህ መንፈስ ግንባታውን በጥራት እየሰራን ነው፡፡ ከጥቂት ወራቶች በኋላም ግንባታውን ሙሉ በሙሉ ጨርሰን እናሰረክባለን ብለውናል ሁለቱም ባለሙያዎች፡፡

፶/አለቃ ኢንጂነር ፋንታሁን እኛ ኢንጂነሮችም ወታደሮችም ነን፡፡ እንገነባለን ሀገራችን በጠላት ስትነካ ደግሞ እንዋጋልን፡፡ ወታደር ማለት በሁለት በኩል የተሳለ ሴይፍ ነው፡፡ ሰዎች ወታደርን ከጦርነት ጋር ብቻ ነው የሚያይዙት። ወታደር የከፍተኛ ሙያ ባለቤት ነው፡፡ እኛም የዚሁ አካል ነን በማለት ስለውትድርና ሙያ ክብርን ከፍታን ገልፀዋል፡፡

ማስተላለፍ የሚፈልገው መልዕክት ይላል ኢንጂነር ፋንታሁን በሀገር መከላከያ ውስጥ ዶክተሮች፣ ፓይለት፣ ኢንጂነሮች፣ መሀንደሶች፣ የግብርና፣ የህዝብ ግንኙነት፣ ምርጥ የማኔጅመንት ሰራተኞች፣ አካወንታንት፣ አርክቲክቸሮች ወዘተ… አሉ ወታደር ሙያው መተኮስ ብቻ አይደለም፡፡

ውትድርና እውቀት የሚገኝበት፣ የፈጠራ ሰዎች ያሉበት በመሆኑ መከላከያ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎች የሚፈልቁበት ተቋም ነው፡፡ በእርግጥ ማንኛውም ሰው በጥረቱ የፈለገውን መሆን ይችላል፡፡ ሁሉም ሰው ግን ወታደር መሆን አይችልም፡፡ በመሆኑም ውትድርና ማንም ሰው ፈልጎ የማያገኘው ሙያ ነው፡፡ ምክንያቱም ዕድሜ፣ አካላዊ ብቃት፣ የዲሲፕሊን ደረጃ ወዘተ… ይገድበዋልና፡፡

ውትድርና ታሪክ የሚፃፍበትም አውድ ነው፡፡ ታላለቅ ሰዎች የሚፈልቁበትም ነው፡፡ በመሆኑም ችሎታና ብቃቱ ያለው ዕድሜው የሚፈቅድለት ሰው ሁሉ ወደ ተቋሙ በመግባት በእውቀቱ ተጠቅሞ ጥሩ ስራ በመስራት ሀገርን ለትውልድ ማስተላለፍ አለበት፡፡

ሰው ማለት ለግሉ የኖረ ሳይሆን ለህዝብ እና ለሀገር ኖሮ የማይደበዝዝ ታሪክ የፃፈ ሰው ነውና እኛ እናልፋለን፡፡ ከእኛ የሚጠበቀው ሰርተን ለቀጣዩ ትውልድ ታሪክ አስቀምጠን ማለፍ ነው፡፡

እኛ ለሀገራችን ወታደር ሆነን በአንድ እጅ ክላሽ ይዘን አሁን እየገነባን ያለነው ለትውልድ የሚበቃ ግንባታ አንዱ የታሪካችን አካል ነው፡፡ ነገም ሌላ ታሪክ እንሰራለን በማለት ፶/አለቃ ኢንጂነር ፋንታሁን መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡

የአየር ወለድ ትምህርት ቤት ግንባታ የመከላከያ መሀንዲስ ዋና መምሪያ ራሱን ችሎ ከሚገነባቸው ግንባታዎች መካከል አንዱ በመሆኑ በዚህም እንኮራለን ሲሉ ሁለቱም ወታደር ኢንጂነሮች ተናግረዋል፡፡

ለሀገር ዕድገትና ብልፅግና ደግሞ ሠራዊት ወሳኝ ነው፡፡ ጠንካራ ሠራዊት ለሀገራዊ ልማት ለዜጎች ብልፅግና ጠንካራ መሰረት ነው፡፡ ጠንካራ ሠራዊት ያለው ሀገር የእድገትና ልማት እቅድን ያለምንም የሰላም ስጋት ማሳካት ይችላል፡ በመሆኑም ሁላችንም ይህንን መልዕክት ተገንዝበን ሀገራችንን ባለን ሙያ እና ችሎታ በታማኝነትና በቅንነት እናገልግል መልዕክታችን ነው፡፡

አብዱራህማን ሀሠን
ፎቶግራፍ አብዱራህማን ሀሠን defence FB

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“እስካሁን ድረስ ጎድተኸኛል ብሎ የተናገረኝ ሰው የለም” አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ
“አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ”
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2