Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የአማራ፣የትግራይና የኤርትራ “ቀይ መስመሮች” የሰላም የዜሮ ድምርና መንግስትና ዓለም ወዴት?
News

የአማራ፣የትግራይና የኤርትራ “ቀይ መስመሮች” የሰላም የዜሮ ድምርና መንግስትና ዓለም ወዴት?

Ethioreview newsEthioreview news—June 19, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

መንግስት ትህነግ እንዳይቀጠቅጠው ፈርቶ እርዳታ እንዲገባ የፈቀደ በመሆኑ ወደ ውጊያ መግባቱ ብዙም ጥቅም አለው ብለው እንደማያስቡ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ለዚህ አባባል ቃል በቃል መልስ ባይሰጥም ” ዛሬ ላይ ምንም ሃይል ኢትዮጵያን መተንኮስ እማያስበበት፣ ካሰበም ምነው ባላደረኩት እሰከ ሚልበት ደረጃ የሚዘልቅ ምላሽ ይሰጠዋል” ሲል በጥቅሉ አስታውቋል። ይህን ያስታወቁት የኮሙኒኬሽን ሃላፊው ሲያጠቃልሉ ” የኢትዮጵያ ሕዝብ አሳብ አይግባህ” ነበር ያሉት። ትህነግ ሰራዊት አጠናክሮ በክረምት በሃይል ይገቡኛል ያላቸውን ስፋራዎች መልሶ ለመያዝ ማቀዱ በተደጋጋሚ ቢገለጽም በመንግስት በኩል ተመጣጣኝ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ቁመናና ብቃት ስለመኖሩ እየተነገረ ነው። በየአቅጣጫው ያለው ሃይልም ዝግጁ መሆኑንን እያስታወቀ ነው። ሰራዊቱም ቀደም ሲል የተፈጸመበት በደል ዛሬ ድረስ የሻረለት እንዳልሆነ በልዩ ስሜት እያስታወቀ ነው።

የአማራ ክልል መሪ ዶክተር ከፍያለ ” ወልቃይት ለአማራ ቀይ መስመር ነው። ለድርድር አይቀርብም” ሲሉ በይፋ አስታውቀዋል። ቀደም ሲል አሁን ወልቃይትን እያስተዳደረ ያለው አካልም ” በጉልበት የተወሰደ መሬት በጉልበት ተመልሷል” ሲሉ ድርድር እንደማይታሰብ በተደጋጋሚ አመልክቷል። የትግራይ ክልል መሪ ዶክተር ደብረጽዮንም ሰሞኑንን ለድርድር የማይቀርቡ ሲሉ በዝርዝር ካስቀመጧቸው ነጥቦች መካከል አንዱ “ወልቃይት ለድርድር አይቀርብም” የሚለው ሃሳብ ነው። ትህነግ ስልጣን ሲይዝ “ምዕራብ ትግራይ” ያለው ማለት ነው።

ክልሎቹ አቋማቸውን “በቀይ መስመር” ቢያስታውቁም የፌደራል መንግስቱ ከትህነግ ጋር የሚደራደረው ምን ዓይነት ሁኔታዎች ሲሟሉ እንደሆነ የሚያጠና ኮሚቴ ተቋቁሞ እያጠና እንደሆነ አመልክቷል። ይህ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የሚመራው ኮሚቴ ግፋ ቢል በሁለት ሳምንታት ውስጥ ለብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የጥናቱን ሪፖርት እንደሚያቀርብ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለፓርላማ ሲያታውቁ ነው የተሰማው።

“ኮሚቴው ሰላሙን በሚመለከት ኢትዮጵያ ምን ምን ትፈልጋለች? ምን ሲሳካ ነው የምንደራደረው? እንዴትስ ነው የምንነጋገረው? የሚለውን ጉዳይ ሲያጠና መቆየቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አመልክተዋል። ይህን ያሉት በድብቅ ድርድር ስለመኖሩ ተጠይቀው ህዝብ ሳያውቅ የሚደረግ ድርድር እንደማይኖርና ሁሉም ነገር የሚሆነው እንደ አገር ኢትዮጵያን በሚጠቅም አግባብ ብቻ መሆኑን በገለጹበት ወቅት ነው።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ዶክተር ደብረጽዮን ይህንኑ አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ” እስካሁን ድርድር ውስጥ አልገባንም።ወደ ድርድር የምንገባ ከሆነ ግን ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነቱን የተቀበልን ጊዜ ያሳወቅነውን አቋም አንቀይርም።በወቅቱ የያዝነው አቋም ለድርድር የሚቀርብ አይደለም” ብለዋል። አቋም ያሉትን ሲዘረዝር “የትግራይ ህዝብ ወደፊት ሪፈረንደም ማካሄድ አለበት የሚለው አቋማችን ለድርድር የሚቀርብ አይሆንም” ሲሉ ትግራይ ሪፈረንደም ለማካሄድ እንደምትፈልግ አስታውቀዋል። ቀጥለውም “የትግራይ ሉዓላዊ ግዛት ጉዳይ ቢያንስ ከጦርነቱ በፊት ወደ ነበረበት መመለስ አለበት።ያ ማለት በህገ መንግስቱ የምትታወቀዋ ትግራይ ማለቴ ነው” ሲሉ “ምዕራብ ትግራይ” በተባለው አዲስ አከላል ውስጥ የተካተቱት የወልቃይት ጠገዴ ምድር ለድርድር እንደማይቀርብ አመልክተዋል።

“ሌላው የትግራይ ሰራዊት ጉዳይ ለድርድር አይቀርብም።ሰራዊታችን ትጥቁን አይፈታም።በህግ በስርዓት የሚባል ነገር አይሰራም፤አልፎበታል።” ሲሉም ዋና ዋና ጉዳያቸውን በይፋ አመልክተዋል። አሁን ባለው ህገ መንግስት መሰረት ወልቃይትን ማካለል ለድርድር አይቀርብም ሲሉ በህገመንግስቱ የክልል የጸጥታ ሃይል መታጠቀ የማይገባውን መሳሪያና ትጥቅ አስመልክቶ ” ህግ አይሰራም” ሲሉ ሁለቱን እንዲያስታርቁ ጥያቄ አልቀረበላቸውም።

የአማራ ክልል በተደጋጋሚ እንዳስታወቀውና በወላቅይት ጠገዴ ጉዳይ ድርድር አያደርግም። ምን ነገር የመስሚያ ጆሮ የለውም። ዛሬ ላይ ፋኖናና የአካባቢ ሚሊሻ አደረጃጀትን ሳይጨምር በመቶ ሺህ የሚቆጠር ልዩ ሃይል ማደራጀቱን፣ የአገር መከላከያ ሰራዊት ሜካናይዝድ ሃይል በተጠንቀቅ በቆመበት የድንበሩ አካላይ ትህነግ “ወልቃይት ቀይ መስመሬ ናት” ሲል ላስታወቀው አቋሙ ” አይሆንም”የሚል መልስ ሲሰጠው አቶ ጌታቸው ረዳ እንዳሉት በሃይል ማስመለስ ይቻለዋል ወይ የሚለውን ጉዳይ ዛሬ ላይ አከራካሪ አይመስልም።

ትህነግ ሰራዊት አጠናክሮ በክረምት በሃይል ይገቡኛል ያላቸውን ስፋራዎች መልሶ ለመያዝ ማቀዱ በተደጋጋሚ ቢገለጽም በመንግስት በኩል ተመጣጣኝ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ቁመናና ብቃት ስለመኖሩ እየተነገረ ነው። በየአቅጣጫው ያለው ሃይልም ዝግጁ መሆኑንን እያስታወቀ ነው። ሰራዊቱም ቀደም ሲል የተፈጸመበት በደል ዛሬ ድረስ የሻረለት እንዳልሆነ በልዩ ስሜት እያስታወቀ ነው።

በዚህ ሁሉ ውስጥ የሰላም ድርድሩ እንዴት ሊሄድ እንደሚችል ለመገመት የሚቸገሩ እንደሚሉት የጎንደር ዩኒቨርስቲን ጥናት ይፋ ያደረገው፣ ከወልቃይት ጠገዴ የስደት ተመላሽ ነዋሪዎች እንደተደመጠው ከሆነ ሰፊ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ከትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች ወደ ተጠቀሱት አካባቢዎች የሰፈሩ ሲሆን በተመሳሳይ በርካታ የአካባቢው ተወላጆች እንዲሰደዱና እንዲባረሩ ተደርገዋል። በርካቶች የደረሱበት እንደማይታወቅ ተመልክቷል። የውጭ ሚዲያዎችም አሁን ላይ አካባቢው በሰው ልጆች ላይ ወንጀል የተፈጸመበት ምድር እንደሆነ እየመሰከሩ ነው። በዚህ መነሻ አካባቢውን በሪፈረንደም አግባብ እንኳን መፍትሄ ለመስጠት ዛሬ ላይ በአማራ ክልል ዘንዳ ቀልድ ነው።

ከግጭቱ ጋር በቀጥታ አብራ የምትነሳዋ ኤርትራ በይፋ ባወጣቸው መግለጫ ትህነግ በአፍሪካ ቀንድ ቀውስ ለመፍጠር በኤርትራ ላይ ጦርነት ማወጁን አስታውቆ ኤርትራ በሁሉም ረገድ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ እንደሆነች ከረር ባለ ቃል ማስታወቋ አይዘነጋም።

ትግራይን የሚያስተዳድረው አካል ኤርትራን አስመልክቶ ያለውን አቅም በመጠቀም ያለውን መንግስት እንደሚያስወግድ በይፋ እያስታወቀ፣ አልፎ አልፎም ግጭት መኖሩና ድል እንደተቀዳጀ እያስታወቀ ነው። ቀደም ሲል ጀምሮ እንደሚገለጸው የኤርትራን ደጋማ አካባቢዎች በመያዝ ታላቋን ትግራይ የመገንባት ዕቅድ እንዳለ ሲገለጽ ነበር።

የኢርትራን መንግስት መንቀል እንደሚችሉ ቢገልጹም ከፌደራል መንግስት ጋር ምንም ዓይነት ድርድር እየተደረገ እንዳልሆነ ዶክተር ደብረርጽዮን ሲያስታውቁ እግረመንገዳቸውን “ኤርትራ ከትግራይ ክልል የያዘቻቸውን አካባቢዎች እስካሁን አልለቀቀችም” ሲሉ ተደምጠዋል። መንግስት ይህን አስመልክቶ ምንም ያለው ነገር የለም። ቀደም ሲል ግን በኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ አቶ መልስ የፈረሙት የአልጀርሱ ስምምነት ተፈጻሚ እንዲሆን ከውሳኔ ላይ የተደረሰውን ስምምነት መንግስት እንደሚቀበል ማስታወቁ አይዘነጋም።

ኢህአዴግ ከመፍረሱ በፊት ህዝብ የጠየቀውን ለውጥ በግድ መቀበሉን ሲያውጅ አቶ መለስ ዜናዊ የፈረሙት ይግባኝ የሌለው የአልጀርሱ ስምምነት ወደ ተግባር እንዲለወጥ በሙሉ ቃል መወሰኑን ለሕዝብ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ዶክተር ደብረጽዮን የቦታዎችን ስም ስላልዘረዘሩ የኤርትራ ወታደሮች የያዙዋቸው አካባቢዎች አወዛጋቢዎቹን ስፍራዎች ይሁን ተጨማሪ ግልጽ አይደለም።

ኤርትራ በተደጋጋሚ እንዳስታወቀችው የአልጀርሱ ስምምነት ላይ በተጠቀሰው መሰረት ወደ ተግባር መሸጋገር እንጂ ሌላ ድርድርም ሆነ አማራጭ “ቀይ መስመር ነው” ብላለች።

አማራና ትግራይ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ ያሰመሩት ቀይ መስመር፣ ኤርትራና በማድመና አካባቢው ያሰመረችው ቀይ መስመር፣ እንዲሁም በአማራና በትህነግ መካከል የተፈጥረውና ምን አልባትም በቀላሉ ሊረሳ የማይችለው ቁስል አንድ ላይ ተዳምሮ የሰላሙን እሳቤ የዜሮ ድምር እያደረገው መሆኑ በስፋትና በግልጽ እየተነገረ ነው።

ይህ ሁሉ ቀይ መስመር ሲሰመር ከጦርነቱ በሁውላ በቁጥር እጅግ የበዛ ሃይል መገንባቱን፣ በጥራት፣ በቴክኖሎጂ፣ በየብስ፣ በውሃና በምድር ሃይሉን እንዳዘመነ መንግስት በይፋ በየቀኑ እያስታወቀ ነው። ቀደም ሲል ከነበረበት የመመጣጠን ችግር መላቀቁን ተረት እንዳደረገ የሚናገረው መንግስት በጦርነት ፈተና ይገጥመኛል የሚል ስጋት እንደሌለው እያስታወቀ የራሱ ቀይ መስመር አስምሯል። ይህም ቀይ መስመር ከማናቸውም አካባቢም ሆነ አካላት የሚሰነዘር ትንኮሳ ነው።

ሊስማሙ ይገባል የሚባሉት ሃይሎች በቀይ መስመር አቋማቸውን “ሕዝብ ብዥታ እንዳይፈጠርበት” በሚል ሲያስታውቁ አብሮ እየተሰማ ያለው የውጪው ጫናና ጉትጎታ መላላቱ ነው። በውጭ ሃይሎች ፍላጎትና ዝንባሌ ላይ የተንጠለጠለው የኢትዮጵያ የውስጥ ፖለቲካ ትኩሳት ዛሬ ላይ አዲስ ጥርጊያ ላይ እንዳለ ምልክት እየታየ ነው።

ፍሬን ይዞ የነበረው ዓለም ባንክ ፍሬኑንን በግማሽ ለቋል። የአውሮፓ አገራት በጋራ የያዙትን አቋም በማላዘብ ትብብር እያሳዩ ነው። ሲራገሙ የነበሩትና በሚዛን አልባነት የሚታወቁ የተባበሩት መንግስታት የተለያዩ ሃላፊዎች ምስጋና እያቀረቡ ነው። አውሮፓ ህብረት የፖለቲካና የድህንነት አምባሳደሮቹን ልኳል። ባህር አልባዋ ኢትዮጵያ በአውሮፓ ህብረት ሙሉ ወጪ በቀይ ባህር ላይ የተቋቋመውን ሀገወጥ ተግባራትና የመሳሪያ ዝውውር እንድቶጣጠር ሃላፊነት ወስዳለች። አብይ አሕመድ የባህር ሃይልን ዳግም ሲመሰርቱ “እብድ” ያሉዋቸው ነበሩ።

ዋናዋ የጠብ አጋፋሪ ስትባል የነበረችው አሜሪካ ከዩክሬንና ሩሲያ ጦርነት በሁዋላ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ አፍሪካን ላለማጣት ኢትዮጵያ ላይ ያሳየችውን መገልበጥ ተከትሎ ከላይ የተዘረዘሩት አገራትና ተቋማት ያሳዩትን ወደ ቀልብ የመመለስ ውሳኔ ተከትሎ አውሮፓ ህብረትም በይፋ የአቋም መለሳለሱን ይፋ ለማድረግ ከጫፍ መድረሱ እየተሰማ ነው። በቅርቡ የህብረቱ የፖለቲካና የደህነት አምባሳደሮችም አዲስ አበባ መግባታቸው፣ እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት ዓለም በሙሉ የአፍሪካ ህብረት ወኪል ኦባ ሳንጆ እያከናወኑት ላለው ተግባር ሙሉ ደጋፍ እንዲሰጥ መጠየቁ … አሁን ላይ እየታዩ ያሉ አበይት ጉዳዮች ናቸው።

የአውሮፓ አገራት በተናጠል ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግንኙነትና ትብብር እያሻሻሉ ባለበት ወቅት፣ አውሮፓ ህብረትም አቋሙን በተቋም ደረጃ ሊያሻሽል ዳር በደረሰበት፣ መንግስት ለሰብአዊ እርዳታ ሲባል የወሰደው አቋም በሁሉም ወገኖች አሜሪካን ጨምሮ በበጎ በሚነሳበት፣ የአፍሪካ አገራት ሩሲያን መደገፋቸው አሜሪካ ( አፍሪካን አልከስርም) ስትል የያዘችውን አቋም በይፋ እንድትቀይር መገደዷ፣ መንግስት የመከላከያ አቅሙን ማዘመኑና የመሳሰሉት ጉዳዮች ተዳምረው የዲፕሎማሲ አውዱ መሻሻል ማሳየቱ በይፋ እየታየ ዶክተር ደብረጽዮን ” ጦርነት ሞክረናቸው ነበር” ሲሉ መንግስት ተንቦቅቡቆ እርዳታ እንዲገባ መፍቀዱን ተናግረዋል።

መንግስት ትህነግ እንዳይቀጠቅጠው ፈርቶ እርዳታ እንዲገባ የፈቀደ በመሆኑ ወደ ውጊያ መግባቱ ብዙም ጥቅም አለው ብለው እንደማያስቡ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ለዚህ አባባል ቃል በቃል መልስ ባይሰጥም ” ዛሬ ላይ ምንም ሃይል ኢትዮጵያን መተንኮስ እማያስበበት፣ ካሰበም ምነው ባላደረኩት እሰከ ሚልበት ደረጃ የሚዘልቅ ምላሽ ይሰጠዋል” ሲል በጥቅሉ አስታውቋል። ይህን ያስታወቁት የኮሙኒኬሽን ሃላፊው ሲያጠቃልሉ ” የኢትዮጵያ ሕዝብ አሳብ አይግባህ” ነበር ያሉት።

መንግስት ይፋ ያደረገውና ቢበዛ በሁለት ሳምንት ውስጥ ጥናቱን የሚያቀርበው ኮሚቴ ከሚያካትታቸው አንድ ዋና ጉዳይ በትግራይ ህገመንግስቱ ከሚፈቅደው ውጪ ያደራጀውን ሃይልና የታጠቀውን ትጥቅ መፍታትን አስመልክቶ የመንግስት ቀይ መስመር እንደሆነ ተሰምቷል። መንግስት፣ ክልሎችና ኤርትራ ሁሉም የራሳቸውን ቀይ መስመር ያሰመሩባት የሰሜኑ ጉዳይ እንዴት ወደ ሰላም ያምራ? ለሚለው ጥያቄ ይህ ነው የሚል የመግባቢያ አሳብ የሚያቀርብ የለም። የትግራይ ክልል በዚህ መልኩ መቀጠል ስለማይችል ጦርነቱ አይቀሬ መሆኑንን በርካቶች ያምናሉ። እንደውም ትህነግ ለምን እስካሁን ዝም አለ? በሚል የትህነግን ሃይል የድል ዜና በጉጉት የሚጠብቁ በርካታ ናቸው። ህዝብ ግን ሰላም ይፈልጋል።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Ethiopia, World Bank Agree $405mln Grant for Water Development, Anti-COVID Campaign
አብን የከፍተኛ አመራሮቹን የሥራ መልቀቂያ ውድቅ አደረገ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2