Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  አዲስ አበባ ረክሳለች! – የሌቦች ውሎ
News

አዲስ አበባ ረክሳለች! – የሌቦች ውሎ

Ethioreview newsEthioreview news—December 25, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ትውልድ አምካኝ ቤቶችን፣ ትውልድ አምካኝ ደላሎችን፣ በህጻናት የወሲብ ንግድ ገንዘብ የሚሰበስቡትን፣ ማጥፋት ቀላል ነው። ግን ተጠቃሚዎቹ ህግ አስከባሪዎቹ፣ ህግ አወጪዎቹና ዋናዎቹ “የአገሪቱ ህዳሴ ባለቤቶች” የሚባሉት በመሆናቸው አይታሰብም። አንዳንድ ዝግ ቤቶች በሲቪል ጠባቂዎች የሚጠበቁ ናቸው። አንዳንዴ ቤተመንግስቱንና ሟቹን የቤተመንግስት ነዋሪ ይጠብቁ የነበሩት በፈረቃ ይታደሙባቸዋል።

ሃኪሞች፣ የህግ ባለሙያዎች፣ አገር የሚመሩት፣ ህግ የሚያስከብሩት፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ አውራ ባለስልጣናት፣ ህዝብ ፊት ቀርበው በልማት ስም የሚምሉት ሃብታም ተብዬዎች፣ የፖሊስ የበላይ አመራሮች፣ የስለላ አውራ ሰዎች፣ አጫፋሪዎች፣ የአቻ ፓርቲ አመራሮችና መካከል ጥቂት የማይባሉ ከዳር እስከዳር መመሸጊያቸው ዝግ ቤቶች ናቸው። አንዳንዴም ከዝግ ቤቶች ፍራሽ ላይ ሆነው የፖለቲካ መመሪያ የሚሰጥበት አጋጣሚ አለ። ይህን አስደንጋጭ እውነት “መርከስ” ነው። አዲስ አበባ ይፋ አደረገችው እንጂ በየክልሉ ከተሞች የሚደረገው ተመሳሳይ ነው።

የሺሻና የጫት በጀት የሚመድቡ ባለስልጣናት አሉ። አስቤዛ ሲደረግ “ሙአሰል” ከህጻናት ዳይፐርና የዱቄት ወተት እኩል የሚመድቡ አሉ። ህጻናትን በመመልመል ሳውና በማስገባት፣ በማሰልጠን፣ ዘመናዊ ልብስ በማልበስ ለገበያ የሚያቀርቡ ብዙ ናቸው። እገሌ ለሚባል አየር መንገድ አስተናጋጅ እንቀጥራለን በሚል ታዳጊዎችን እያንጋጉ በወሲብ የሚነዱና የሚያነዱ ይህን ተግባራቸውን የሚፈጽሙት ማስታወቂያ እያስነገሩ ነው።

ግብረሰዶም የሚያስፋፉ በየሆቴሉ ድሆችን በማደን ማበላሸት ከጀመሩ ቆይተዋል። አሁን አሁን በየጎዳናው ታዳጊዎችን በማታለል ህሊና የሚያስት ኬሚካልና እጽ በመጠቀም ህሊናቸውንና አካላቸውን መስበር ተለምዷል። ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው በዚህ የግብረሰዶም ወረራ ውስጥ ተጠቃሚ በመሆን ወንድሞቻቸውን የሚደልሉ መበራከታቸው ነው።

More stories

ተስፋ የተጣለባት ኢትዮጵያዊት አትሌት መጨረሻ ለምን እድሜ ልክ እስር ሆነ?

February 23, 2023

የአሸባሪው ግፍ በአፋር …

February 19, 2022

የህብረት ስራ ኮሚሽን ገበያ የማረጋጋት ተልእኮውን በተገቢው እንዲወጣ ታዘዘ

April 5, 2023

በሳዑዲ አረብያ ኢትዮጵያዊያን ላይ የሚፈጸመው ግፍ እንዴት ማስቆም ይቻላል? የሚል ጭንቀት በርክቷል

February 9, 2022

ህጻናትን ለወሲብ የሚያቀርቡ ነፍሰ በላዎች ኢኮኖሚያቸው አድጎ ባለ ዘመናዊ መኪናና ህንጻ መሆናቸው ነው። አዲስ አበባ ባሉ ዝግ ቤቶች ወሲብንና ግብረ ሰዶምን የሚያሻቅጡ ህሊና ቢሶች ጉዳይ ያሳሰበው ቀጭኑ ዘ-ቄራ የሚባለው የአዲስ አበባው አምደኛችን ከወራት በፊት “የሚዘጋባቸው ህጻናት” በሚል ርዕስ የጉዳዩን አሳሳቢነት ጠቁሞ ነበር። (ዕድሜ ለኢንሳና አፈናው ብዕሩ ማዕቀብ ተደርጎበት በተከታታይ ጽሁፎችን ሳያስነብብ ቢቆይም እንዲሁ እንደጠፋ ግን አይቀርም፡፡)

የከበረውን ትዳራቸውንና ያብራካቸውን ፍሬዎች ቤት ጥለው፤ ባይወልዷቸውም ልጆቻቸው ከሚሆኑት ጋር የሚዳሩትና፣ የውሽሞች ቀን እያከበሩ አረቄ የሚራጩት ሃብታሞች ጠለቅ ያለ ምርመራ ቢደረግባቸው እስከ ዱባይ የዘለቀው የግፍ ገመናቸው ይገለጥ ነበር። ዳሩ የወንጀሉ ዋና ተባባሪዎች ተቆጣጣሪዎቹና ህግ አስከባሪዎቹ በመሆናቸው አስቀድሞ እንደተባለው አይታሰብም።

አዲስ አበባ መርከሷን ጥር 11 ቀን 2013 በአዲስ አበባ አስተዳደር ይፋ የተደረገው ጥናት፤ የቀንና የማታ ጭፈራ ቤቶችን፣ የእርቃን ዳንስ ቤቶችን፣ የማሳጅ፣ የቪዲዮ፣ የአደንዛዥ ዕጽ መጠቀሚያ፣ የግብረሰዶማውያን ማዘውተሪያ ቤቶችንና የመኪና ላይ ወሲብ መፈፀሚያና ጫት መቃሚያ ቦታዎችን በሚገባ በመቃኘት ተሰብስቦ በተሰራው ጥናት መረጋገጡን መረጃውን ይፋ ባደረገው አዲስ አድማስ ጋዜጣ በኩል ሰምተናል። ዘገባው ትኩረት የሚያሻውና በሚሊዮን በሚቆጠሩት ታዳጊዎች ህይወት ላይ ያነጣጠረ ስለሆነ እንዳለ አትመነዋል።


አዲስ አበባ በህገወጥ ልማዶችና የወሲብ ድርጊቶች እየተናጠች ነው

ግብረሰዶም ከሚገመተው በላይ በከፍተኛ መጠን እየተስፋፋ ነው፣ አብዛኞቹ የከተማዋ ማሳጅ ቤቶች የወሲብ ንግድ እንደሚያጧጡፉ ታውቋል፣ ከ3600 በላይ ህገወጥ ልማዶችና የወሲብ ድርጊቶች የሚፈፀምባቸው ቤቶች አሉ፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ፖሊሶችና ነጋዴዎች የአነቃቂ እፆች ተጠቃሚ ናቸው፣ በእርቃን ጭፈራ ቤቶች ደጃፍ ከሚቆሙ መኪኖች አብዛኛዎቹ የመንግስትና የንግድ ታርጋ የለጠፉ ናቸው፡፡

በአዲስ አበባ ህገወጥ ተግባራት የሚከናወኑባቸው ቤቶች በከፍተኛ መጠን እየጨመሩ መምጣታቸውንና ከተማዋ አደጋ ላይ እንደሆነች ሰሞኑን ይፋ የተደረገ ጥናት አረጋገጠ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በትናንትናው ዕለት ይፋ የተደረገው ጥናት “መጤ ባህሎችና ልማዳዊ ድርጊቶች በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በተለይም በወጣቶችና ሴቶች ላይ እያስከተሉት ያለው አሉታዊ ተጽእኖ” በሚል ርዕስ የተካሄደ ሲሆን ከ3600 በላይ ህገወጥ የወሲብ ድርጊት የሚፈፀምባቸው ቤቶች እንዳሉ ጠቁሟል፡፡

ወደ 3 ሚሊዮን ከሚጠጋው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ህዝብ ውስጥ 52.4 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ሲሆኑ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ደግሞ ወጣቶች እንደሆኑ ያመለከተው ጥናቱ፣ አብዛኞቹ ሴቶችና ወጣቶች ላልተገቡ መጤ ባህሎችና ልማዳዊ ድርጊቶች እየተጋለጡ እንደሆነ ጠቁሟል፡፡ የከተማዋ ሴቶችና ወጣቶች ለሱስ አስያዥ እፆችና ለአልኮል መጠጦች እንዲሁም ለመጤ ባህል ወረርሽኞች ተጋላጭ ሆነዋልም ብሏል፡፡

ለዚህ እንደዋና ምክንያትነት የቀረበው በከተማዋ የቀንና የሌሊት ጭፈራ ቤቶች፣ የራቁት ዳንስ ቤቶች፣ የግብረሰዶም ወሲብ መፈፀሚያ ቦታዎች፣ የሺሻና የጫት ቤቶች፣ የቁማር ቤትና ህገወጥ የቪዲዮ ቤቶች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እያደገ መምጣቱ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡

(ምስል: አዲስ አድማስ)

በአሥሩም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ የፖሊስ መምሪያዎች የተሰበሰበ መረጃ እንዳመለከተው፣ 3691 ቤቶች ለእነዚሁ ተግባራት ተከፍተው በከተማዋ ውስጥ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

በእነዚህ ቤቶች መበራከትና በስፋት መሰራጨት ሳቢያም በርካታ ወጣቶች ለወንጀል ተግባራት፣ ለአደገኛ እፆች ሱሰኝነት፣ ለዝርፊያ፣ ለስደት ለጐዳና ተዳዳሪነት፣ ለኤችአይቪና ተያያዥ በሽታዎች እንዲሁም ላልተፈለገ እርግዝና ተዳርገዋል፡፡

ትናንት ይፋ የተደረገው ጥናት፤ የቀንና የማታ ጭፈራ ቤቶችን፣ የእርቃን ዳንስ ቤቶችን፣ የማሳጅ፣ የቪዲዮ፣ የአደንዛዥ ዕጽ መጠቀሚያ፣ የግብረሰዶማውያን ማዘውተሪያ ቤቶችንና የመኪና ላይ ወሲብ መፈፀሚያና ጫት መቃሚያ ቦታዎችን በሚገባ በመቃኘት በተሰበሰበ መረጃ የተሰራ መሆኑም ተገልጿል፡፡

የጥናቱ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ የተመሳሳይ ፆታ የወሲብ ግንኙነት ማንኛውም የከተማዋ ነዋሪ ከሚገምተውና ከሚያስበው እጅግ በበለጠ መልኩ ተስፋፍቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት ድርጊቱ እየተስፋፋ በማህበረሰቡ ላይ የስነልቡና፣ የማህበራዊ ግንኙነት፣ የትምህርት ማቋረጥና፣ የጤና ችግር እያስከተለ ነው ተብሏል፡፡

ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት፣ የ2ኛ ደረጃና የከፍተኛ ተቋማት ተማሪዎች፣ በወሲብ ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች፣ እንዲሁም በማረሚያ ቤት የሚገኙ የህግ ታራሚዎች የችግሩ ከፍተኛ ተጠቂዎች እንደሆኑ ጥናቱ አመልክቷል፡፡ ከተመሳሳይ ፆታ ጋር በመሄድ በወሲብ ንግድ ሥራ የሚተዳደሩ ሰዎች ቁጥርም እየተበራከተ መሆኑንና ድርጊቱ በሚያስደነግጥ ፍጥነት እየተስፋፋ እንደሆነ ታውቋል፡፡

አዲስ አበባ የጭፈራ ቤቶችና የራቁት ዳንስ ቤቶች ከቀን ወደቀን እየጨመረ የሚሄድባት ከተማ መሆኗን የጠቆመው ጥናቱ፤ በተለይ ከማህበረሰቡ ወግና የአኗኗር ዘይቤ የወጡ፣ ግለሰባዊ ክብርን የሚፈታተኑ፤ የኢትዮጵያዊነት እሴቶችን የሚያጠፉ የእርቃን ጭፈራ ቤቶች እየተስፋፉ መምጣታቸውን አመልክቷል፡፡

በእነዚህ የእርቃን ዳንስ ቤቶች በራፍ ላይ ከሚቆሙ መኪናዎች ውስጥ አብዛኛዎቹ የመንግስት ታርጋ የለጠፉ መሆናቸውን ይፋ ያደረገው ጥናቱ፤ የግልና የንግድ ታርጋዎችን የለጠፉ መኪኖች በብዛት እንደሚታዩና የተወሰኑ የዲፕሎማትና የእርዳታ ድርጅቶች መኪኖችም እንደሚገኙበት ጠቁሟል፡፡

ከእርቃን ዳንስ ቤቶች ጠባቂዎችና ከእርቃን ደናሾቹ ጋር በተደረገ ኢ-መደባዊ ውይይት በቦታው መጥተው የሚገለገሉም ሆነ በየቤታቸው በግል በማስጠራት አገልግሎት ከሚያገኙት ደንበኞች መካከል የተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የመንግስት ሠራተኞች፣ የውጭ ዲፕሎማቶችና በንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች እንደሚገኙበት የጥናቱ መረጃ ይፋ አድርጓል፡፡

የእርቃን ደናሾቹ ወርሃዊ ገቢ የተለያዩ ጥቅማጥቅሞችን ሳይጨምር ከ3ሺ-14ሺ ብር እንደሚደርስ የሚጠቁመው ጥናቱ፤ ለዚህ ሥራ የሚመለመሉት ወጣት ሴቶች የኢኮኖሚ አቅማቸው ዝቅ ያለ፤ መልካም የሰውነት አቋም ያላቸው፤ የኮሌጅና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ከሞዴሊንግ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚመረቁ ወጣቶች እንደሆኑም ያመለክታል፡፡

በአሁኑ ወቅት ወሲብና ወሲብ ነክ ጉዳዮች የሚፈፀሙባቸው ማሳጅ (መታሻ) ቤቶችን መጠቀም እየተለመደ መምጣቱን ይፋ ያደረገው መረጃው፤ ከመታሻ ቤቶቹ አብዛኛዎቹ ደረጃቸውን በጠበቁ ትላልቅ የመኖሪያ ቤቶችና በትላልቅ የንግድ ህንፃዎች ላይ እንደሚገኙና የ24 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጡ እንደሆኑ ጠቁሟል፡፡ በእነዚህ ቤቶች በሚሰጠው የመታሸት አገልግሎት ሥር በተለየ ሁኔታ ለምርጫ የሚቀርቡት ድርጊቶች ህብረተሰቡን ከባህልና ሥነምግባር ውጪ ለሆነ ባህርያት እየዳረጉት እንደሆነና የማሳጅ አገልግሎት መስጫ ቤቶቹም ከቀን ወደ ቀን ቁጥራቸው እየጨመረ መሄዱ በጥናቱ ላይ ተጠቁሟል፡፡

የጥናቱ አዲስ ግኝት ሆኖ የተገለፀው ሌላው ጉዳይ በመኪና ውስጥ የሚፈፀሙ ጫት የመቃምና የወሲብ ድርጊቶች መስፋፋት ነው፡፡ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም በቦሌ በሚገኙ ትላልቅ ህንፃዎች፣ ባሮችና ሬስቶራንቶች ሥር፣ በመንገዶች ግራና ቀኝ እንዲሁም በመኪና ማቆሚያ ቦታዎች ላይ በመኪና ውስጥ በተናጥል እና በጥንድ በመሆን ጫት መቃም፣ ወሲብ መፈፀምና ሌሎች ያልተገቡ ተግባራትን መከወን በስፋት እየታየ መሆኑን ጥናቱ ያመለክታል፡፡

ይሄም ተግባር ከተማዋን እጅግ አደገኛ ወደሆነ አደጋ ውስጥ እየከተታት እንደሆነ የጠቆመው ጥናቱ፤ በአገሪቱ የሬዲዮ ፕሮግራሞች በቀጥታ የሚተላለፉ ፕሮግራሞች ለእንዲህ ያሉት ድርጊቶች ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ገልጿል፡፡

በሬዲዮ የሚቀርቡና በወሲብ ዙሪያ የሚያጠነጥኑ የቀጥታ ውይይት ስርጭቶች ከአስተማሪነታቸው ይልቅ ወጣቶችንና ህፃናትን ለወሲብ ተግባር የሚገፋፉና ያዳመጡትን በተግባር ላይ ለማዋል ከቤት ወይም ከጐረቤት ጀምረው ወደሴተኛ አዳሪዎች እስከመሄድ እያደረሳቸው እንደሆነ የጥናቱ ውጤት ይፋ አድርጓል፡፡

ሱስ አስያዥ እፆችን መጠቀም፣ ሀሺሽ፣ ሺሻ፣ ሄሮይን እና የአልኮል መጠጦች ለዚህ ተግባር ሰፊ ድርሻ እንዳላቸው የጠቆመው መረጃው፤ ዕድሜያቸው ከ25-30 አልፎ አልፎም በአስራዎቹ ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ህፃናት የማሪዋና ወይንም የካናቢስ ተጠቃሚዎች እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጿል፡፡

በመረጃው መሠረት፤ በተለያየ የመንግስት ኃላፊነት ላይ የሚገኙ ግለሰቦች፣ በማህበረሰቡ ውስጥ ከፍተኛ ማህበራዊ ደረጃ የሚሰጣቸው ግለሰቦችና በኢኮኖሚው ዘርፍ ትልቅ አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ የሚችሉ ባለሙያዎችና የንግድ ሰዎች በዚህ መጤና ያልተገባ ልማድ በከፍተኛ ሁኔታ ተጠቂ ሆነዋል፡፡

የእነዚህ ግለሰቦች በዚህ ያልተገባ ተግባር መጠመድ አርአያ ሊሆኑለት ለሚገባው ህብረተሰብ የሚያስተላልፈው አፍራሽ መልዕክት ከፍተኛ ነው ያለው ጥናቱ፤ በአገሪቱ እድገትና የልማት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ የዝቅጠት አደጋ እያደረሰ መሆኑን አመልክቷል፡፡

ለህገወጥ ተግባራቱ መስፋፋት በአገሪቱ ያለው ህግ እርስ በርሱ የሚጣረስ መሆኑን ጥናቱ እንደምክንያት አቅርቧል፡፡ “መንግስት በአንድ በኩል ለቪዲዮ ቤቶች ፍቃድ ይሰጣል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ጐጂነቱን ያወራል፤ በየጊዜው ሺሻ ቤቶችን የማጥፋት ዘመቻ ያካሂዳል፣ ሺሻ ማጨሻውን እየሰበሰበ ያቃጥላል፤ ነገር ግን ይህንን ሥራ የሚከለክልና የሚቀጣ ህግ ስለሌለ ዕቃውን መልሰው በመግዛት ሥራውን ይጀምራሉ፡፡” ያለው የጥናቱ ሪፖርት፤ ከዚህ በተጨማሪም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ፈቃድ ባገኙበት የሥራ ዘርፍ ስለመሰማራታቸው የሚከታተልና ከመስመር ሲወጡም የሚቀጣ የህግ አግባብ አለመኖሩ ለህገወጥ ተግባራቱ መስፋፋት ምክንያት ሆኗል ተብሏል፡፡

SOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
መንግስት ሌብነትን”ውቀጥ” አለ፤ ሚዲያውስ ጤነኛ ነው?
የሚዘጋባቸው ህጻናት – ዝግ ቤቶች
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2