Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ተስፋ የተጣለባት ኢትዮጵያዊት አትሌት መጨረሻ ለምን እድሜ ልክ እስር ሆነ?
News

ተስፋ የተጣለባት ኢትዮጵያዊት አትሌት መጨረሻ ለምን እድሜ ልክ እስር ሆነ?

Ethioreview newsEthioreview news—February 23, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አትሌት በሱ ሳዶ ከሁለት ወንድሞቿ እና ከሌሎች ሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በመሆን ባለቤቷን በመግደል ወንጀል ተከሳ፣ ድርጊቱን መፈጸሟ በመረጋገጡ የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባታል።

የመካከለኛ እና የረዥም ርቀት ሯጯ አትሌት በሱ ሳዶ፣ ከተባባሪዎቿ ጋር በመሆን ወንጀሉን የፈጸመችው ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ላይ መሆኑን ከሰጠችው የእምነት ክህደት ቃል መረዳት ይቻላል።

ሟችን እና አትሌት በሱን በቅርበት የሚያውቋቸው መሆናቸውን የሚናገሩት የአዳማ አትሌቲክስ ክለብ አሰልጣኝ ሐብታሙ ግርማ ስለ ግድያው ሲናገሩ “እኔ በጣም ነው ያዘንኩት፤ በእርሱ ሞትም በጣም አዝኛለሁ። የእርሷም እስር ከሞት የማይተናነስ በመሆኑ እና አገሪቱም እንዲህ ዓይነት ሰው በማጣቷ በጣም ነው ያዘንኩት” ብለዋል።

የአትሌት በሱ ሳዶ የቀድሞ አሰልጣኝ ስለ ሁኔታ ቢቢሲ ባናገራቸው ጊዜ የተፈጸመውን ወንጀል አምነው መቀበል እንዳዳገታቸው ሲናገሩ “እኔ አሁን ራሱ ይሄ ነገር እንዴት አንደተፈጠረ ሊገባኝ አልቻለም” ሲሉ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል።

More stories

ተስፋ የተጣለባት ኢትዮጵያዊት አትሌት መጨረሻ ለምን እድሜ ልክ እስር ሆነ?

February 23, 2023

የአሸባሪው ግፍ በአፋር …

February 19, 2022

የህብረት ስራ ኮሚሽን ገበያ የማረጋጋት ተልእኮውን በተገቢው እንዲወጣ ታዘዘ

April 5, 2023

በሳዑዲ አረብያ ኢትዮጵያዊያን ላይ የሚፈጸመው ግፍ እንዴት ማስቆም ይቻላል? የሚል ጭንቀት በርክቷል

February 9, 2022

የመካከለኛ እና የረዥም ርቀት ሯጯ አትሌት በሱ ሳዶ እንዲሁም አብሯት የነበረው ወንድሟ ከባለቤቷ ግድያ ጋር በተያያዘ ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው ፍርድ ቤት የእድሜ ልክ እስራት በይኖባቸዋል።

ነገር ግን ሌላ ወንድሟ እና ከሻሸመኔ በገንዘብ ገዝቶ ያመጣቸው ሌሎች ሁለት ተጠርጣሪዎች ወንጀሉ በተፈጸመበት ምሽት በማምለጣቸው እስካሁን በቁጥጥር ስር አልዋሉም።

የተከሰተው ምንድን ነው?

አትሌት በሱ እና የቀድሞ አትሌት ከነበረው ባለቤቷ ተሻለ ታምሩ ጋር ከስምንት ዓመት በላይ ለሚሆን ጊዜ አብረው በትዳር መቆየታቸውን የፖሊስ ሰነድ ያስረዳል።

ተሻለ ሩጫ ካቆመ በኋላ በሰንዳፋ ከተማ 01 ቀበሌ፣ ሶላር ፋብሪካ ወይንም ጎማጣ የሚባል ቦታ ከባለቤቱ ጋር ይኖር የነበረ ሲሆን፣ በስልጠናም ይረዳት ነበር።

የፖሊስ የምርመራ መዝገብ እንደሚያስረዳው ባለፈው ዓመት ነሐሴ 08/2014 ዓ.ም. ምሽት ላይ ተሻለ በመኖርያ ቤቱ ውስጥ ተገድሏል።

የሰንዳፋ በኬ ከተማ አስተዳደር ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አቶ አየለ ኢማሙ፣ በዚያን ቀን በግምት ከምሽቱ ሦስት ሰዓት እስከ ስድስት ሰዓት ድረስ የተፈፀመውን ነገር ለቢቢሲ አስረድተዋል።

ወንጀሉ በተፈጸመበት ምሽት ተጠርጣሪዋ አትሌት በገንዘብ ገዝታ አምጥታቸዋለች የተባሉ ግለሰቦችን የመኝታ ክፍል ውስጥ እንዲደበቁ ማድረጓን ይናገራሉ።

“ባል ተሻለ ውጪ ቆይቶ ሁለት ሰዓት አካባቢ ቤት ከገባ በኋላ፣ ሳሎን ተቀምጦ የእጅ ስልኩን በሚነካካበት ወቅት እነዚህ በገንዘብ የተገዙ ሰዎች ከተደበቁበት ወጥተው በብረት መትተው እና በስለት ወግተው ግድያውን ፈፀሙ።”

በዚህም የተነሳ ሟች ወድያውኑ ሕይወቱ ያለፈ ሲሆን፣ ከዚያም ግድያውን በመተባባር የፈጸሙት ግለሰቦች የሟችን አስከሬን አውጥተው መንገድ ላይ እንደጣሉት ዐቃቤ ሕጉ ተናግረዋል።

“ሚስት ደግሞ ከእርሷ ጋር ከሚኖር ወንድሟ ጋር እንዲሁም ከቤት ሠራተኛዋ ጋር በመተባበር ቤት ውስጥ የፈሰሰውን ደም አፀዱ፤ የሶፋውን ጨርቅ አውጥተው አጥበው፣ የሟችን ልብስ እና ደም የነካውን ምንጣፍ ሰብስበው. . .” መደበቃቸውን የአትሌት በሱን የእምነት ክህደት ቃል በመጥቀስ ያስረዳሉ።

በግድያ ወንጀሉ ውስጥ በሱ እና ከእርሷ ጋር የሚኖረው ወንድሟ፣ እንዲሁም ከሻሸመኔ ሁለት ተጠርጣሪዎችን ያመጣው ሌላ ወንድሟን ጨምሮ በአጠቃላይ አምሰት ሰዎች መሳተፋቸውንም አክለው ገልጸዋል።

ባል ከተገደለ በኋላ ከሻሸመኔ የመጡት ተጠርጣሪዎች እና አንድ ወንድሟ የዚያኑ ዕለት ምሽት አምልጠው መጥፋታቸውን ዐቃቤ ሕጉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ከዚያ በኋላም ቀድሞ አብሯት የሚኖረው ወንድሟ እና እርሷ ቤት ውስጥ ቆይተው ሟች “ወደ ቤት እንዳልገባ ለወዳጆቻቸው እየደወሉ ሲናገሩ ነበር።”

መንገድ ላይ የሟች አስከሬን ተጥሎ ከተገኘ በኋላ መረጃ የደረሰው ፖሊስ ምርመራውን ከባለቤቱ አትሌት በሱ ነበር ጀመረው።

ዐቃቤ ሕግ “ሟች በማኅበረሰቡ ዘንድ ተወዳጅ ስለነበር በግድያው ማኅበረሰቡ በጣም ተከፋ፤ የፀጥታ ሰዎች ቀድመው ባይደርሱ ኖሮ ባለቤቱ ላይ ጉዳት ሊደርስ ይችል ነበር” ሲሉ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ያስረዳሉ።

ከምርመራ በኋላ “እርሷም ከተባባሪዎቿ ጋር በመሆን ባሏን ያስገደለችው መሆኗን አምናለች” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በሱ በለንደን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ በተሳተፈችበት ጊዜ
የምስሉ መግለጫ,በሱ በለንደን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ በተሳተፈችበት ጊዜ

የግድያው ምክንያት ምንድን ነው?

አትሌት በሱ እና ባለቤቷ መካከል ይህ ችግር ከመከሰቱ በፊት ወደ ሕግ ቀርቦ ቅሬታ ወይንም ስጋቱን የገለጸ አካል የለም። ነገር ግን በጥንዶቹ መካከል ግጭት እንደነበር ዐቃቤ ሕጉ ጠቅሰዋል።

በሱ ባለቤቷ “እንዳይሳካልን በቤተሰቤ፣ በእናቴ፣ በወንድሞቼ እና በእኔ ላይ ያስጠነቁላል” በሚል ይህንን ወንጀል እንደፈጸመች ቃሏን በሰጠችበት ወቅት መናገሯን ተናግረዋል።

በጥንዶቹ መካከልም ከገንዘብ ጋር በተያያዘ አለመግባባት እንደነበር ተከሳሿ በሰጠችው የእምነት የክህደት ቃል ላይ መስፈሩን ተገልጿል።

የትዳር አጋሮቹ በቆይታቸው ልጅ ባይኖራቸውም የተለያየ ንብረት አፍርተዋል።

ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፊንፊኔ ዙርያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት (አሁን የሸገር ከተማ የተባለው) በጥር 09/2015 ዓ.ም. የእድሜ ልክ እስራት ውሳኔውን በእርሷ እና በወንድሟ ላይ አስተላልፏል።

ሁለቱ የቅጣት ውሳኔ የተላለፈባቸው ተከሳሾች በቀጥታ ግድያው ላይ ባይሳተፉም “አብረው በማሴር ግድያ የፈጸሙ ተጠርጣሪዎችን ጠርተዋል። ግድያው ከተፈጸመ በኋላ ደግሞ ሟች እንደጠፋባቸው በማስመሰል ለሰዎች ሲያወሩ ነበር” ሲሉ ዐቃቤ ሕጉ ለቢቢሲ ገልፀዋል።

በተጨማሪም የቤት ሠራተኛዋ ይህንን ጥፋት እንዳትናገር ገንዘብ እንደሚሰጧት በመናገር ለመደለል መሞከራቸውን ለፖሊስ ቃሏን ሰጥታለች።

ሦስቱ ተጠርጣሪዎች ግን የዚያኑ ዕለት ሌሊት ስለጠፉ እስካሁን ድረስ ያሉበት እንዳልታወቀ እና በፖሊስ እየተፈለጉ መሆናቸውን ጨምረው አስረድተዋል።

ከዚህ ግድያ በፊት ይህች አትሌት ሟችን እንደምታስገድለው ትዝትበት እንደነበር ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ወቅት እንደ ደረሰበት ለቢቢሲ ተናግረዋል።

አትሌት በሱ ሳዶ ማን ናት?

የ27 ዓመቷ አትሌት በሱ ሳዶ እና ባለቤቷ ተሻለ ታምሩ የአዳማ አትሌቲክስ ክለብ አባል ነበሩ። የክለቡ ረዥም ርቀት አሰልጣኝ ሐብታሙ ግርማ ሁለቱን አትሌቶች ማሰልጠናቸውን ይናገራሉ።

“እኔ ለሁለቱም እንደ አባት ነኝ” የሚሉት አሰልጣን ሐብታሙ፣ አትሌቷ በጠባይዋ ምስጉን እንደሆነች “በሱ ሳዶ እንዲህ ዓይነት ነገር ትፈጽማለች ብዬ አስቤም አላውቅም” ሲሉ የሆነውን ማመን እንደከበዳቸው ይገልጻሉ።

አትሌት በሱ በዓለም መድረክ ላይ ተስፋ እንደነበራት ሲናገሩም “የገጠማት ጉዳት ትንሽ ያስቸገራት እንጂ ማራቶን ላይ ውጤታማ ልትሆን ትችላለች ብዬ አስብ ነበር” ይላሉ።

የአትሌቷ መረጃዎች እንደሚያሳዩት አትሌት በሱ አገርን ወክላ ኦሊምፒክ ላይ ጭምር ተሳትፋለች።

በብራዚል ሪዮ ኦሊምፒክ፣ በለንደን እና በቤይጂንግ በተካሄዱ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናዎች ላይ በ1500 ርቀት አገርን ወክላ ተሳትፋለች።

ባለፈው የፈረንጆች ዓመትም ሜክሲኮ ላይ በተደረገ ግማሽ ማራቶን ስታሸንፍ፣ ፓሪስ ላይ በተደረገ የማራቶን ውድድር ላይ ተሳትፋ በሦስተኝነት ጨርሳለች።

በሌላ በኩል ደግሞ በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ላይ እንዲሁም ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ የብር ሜዳሊያ ባለቤት ናት።

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ደግሞ በ1500 ሜትር ለሦስት ዓመታት ሻምፒዮና ሆናለች።

ባለፈው ዓመት በ2014 ዓ.ም በተካሄደው የኦሮሚያ የክለቦች መመዘኛ ላይ ክለቧን ወክላ ሮጣ በ10ሺህ ሜትር አሸንፋለች።

SOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የትውልደ ኤርትራዊው ራፐር ኒፕሲ ሃስል ገዳይ 60 ዓመት ተፈረደበት
ባለቀይ መለዮ- በቁርጠኝነትና ታማኝነት የታወቀ የውጊያ የማርሽ ቀያሪ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2