Skip to content
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
  • News
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    Western Pressure on Ethiopia Intended to See Weak Gov’t, Nation – Scholars

    July 10, 20210

    Journalist demands UNWFP to tell truth about missing trucks

    October 3, 20210

    ብርሃኑ ባይህ እና አዲስ ተድላ ምህረት ሊደረግላቸው ይችላል ተባለ

    December 19, 20200

    አብንና ባልደራስ ከተሸነፉ ” ውጤቱን አንቀበልም” ሊሉ የሚችሉ ፓርቲዎች እንደሚሆኑ ዲፕሎማቶች ገለጹ

    May 23, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1866
  • Design
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ሚስጥራዊ የቻይና ፖሊስ ጣቢያዎች በአሜሪካ ተገኙ

    December 19, 20240

    ሦስተኛው ዕድል እንዳይባክን … !

    May 21, 20220

    “Why I decided to extend my time at the club”

    May 24, 20230

    የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ዋና የጦሩ መሪ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለመንግስት እጁን ሰጠ

    February 24, 20220

    “Ethiopia’s success reflects a new alternative for Africa’s development”

    January 29, 20240
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • Video
    video

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለፓርላማ የሰጡት ማብራሪያ

    July 4, 2024
    video

    የህብታቸውን ምንጭ የሚያውቁ አይሰጉም! ማብራሪያ

    June 22, 2024
    video

    የሀገር አቀፍ የምክክር ሂደት ይፋዊ የማስጀመሪያ ሥነ ስርዓት

    June 4, 2024
    video

    የምክክር ሂደት ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር

    June 4, 2024
    Prev Next Showing 1 Of 5
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • News
  • Design
  • Video
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  ኤርትራን መንካት እንደማይታሰብ ኢትዮጵያ አስታወቀች፣ “ውለታን መርሳት ነውር ነው”
News

ኤርትራን መንካት እንደማይታሰብ ኢትዮጵያ አስታወቀች፣ “ውለታን መርሳት ነውር ነው”

Ethioreview newsEthioreview news—January 1, 20230
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

” ውለታን መርሳት ነውር ነው” በሚል የመንግስት ቁርጥ ያለ አቋም የተገለጸው “ተቃዋሚ” ፓርቲዎችን በመሰብሰብ “የኤርትራ ሰራዊት ከትግራይ ለምን አይወጡም በሚል ተደራራቢ ጥያቄ መልስ ሲሰጥ ነው። “በሦስተኛው ዙር አገሪቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለማፍረስ በተካሄደው ጦርነት” አሉ አቶ ሬድዋን፣ “የፌዴራል መንግሥት በቆቦ በኩል ባለው ዳገት ወደ ላይ መውጣት ስላዳገተው፣ ትህነግ ያለውን መልክዓ ምድራዊ ጠቀሜታ ተጠቅሞ ቆቦን ተቆጣጥሮ ነበር” ሲሉ ኤርትራን እንደ ጠላት በማየት ጥያቄ ላቀረቡት ምስላዊ ማብራሪያ ሰጡ።

  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

ይህ ሲሆን ወቅቱ ክረምት መሆኑ ችግሩን እንዳባባሰው ካስታወሱ በሁዋላ ” በዝናብ ምክንያት በምዕራብ በኩል ተከዜን የኢትዮጵያ ሰራዊት ማቋረጥ ባለመቻሉ፣ አቅጣጫ ቀይሮ ያለስጋት በዛላምበሳና በአዲግራት በኩል ተከዜን እንዲሻገር የኤርትራ መንግሥት በመፍቀዱ ጦርነቱ ሊቀለበስ ችሏል” ሲሉ ኤርትራ ክህደት ተፍጽሞበት የታረደውን የኢትዮጵያ አለኝታ ሰራዊት ተቀብላ ከማስተናገዷ በተጨማሪ ያበረከተችውን የማይረሳ አስተዋጾ ገለጹ።

ኤርትራ ባትተባበር ኖሮ ምን ሊፈጠር ይችል እንደነበር ሲገልጹ “ለአጭር ጊዜም ቢሆን በራቸውን ባይፈቅዱልን ኖሮ ይኼንን ጦርነት መቀልበስ አይቻልም ነበር፡፡ እንደ አገር ከባድ ፈተና ውስጥ እንወድቅ ነበር” በማለት “ውለታ መርሳት ነውር ነው” ያሉበትን አንድ ምክንያት ገልጸዋል። ይህንኑ አሳብ በወታደራዊ ቋንቋ ሌተና ጀነራል ባጫ ደበሌ ” በቆቦ በኩል ወደፊት የሚገፋ እብድ የለም። ከተፈጥሮ ጋር ውጊያ አይታሰብም። በሌላ አቅጣጫ እናስኬደዋለን” ማለታቸው ይታወሳል።

የጠቅላይ ሚንስትር አብይ የደህንነት አማካሪ አቶ ሬድዋን መንግስት ኤርትራ ላይ የያዘውን አቋምና የአቋሙን አግባብነት የሚያሳይ ማብራሪያ ከሰጡ በሁዋላ፣”የኤርትራ ሠራዊት ከኢትዮጵያ ይውጣ የሚሉት አካላት ለኢትዮጵያ አዝነው አይደለም” ሲሉ ወቅሰዋል። ወቀሳቸውን ሲያጠናክሩ “ኤርትራ ትውጣ የሚሉ አካላት ሱዳን 50 ኪሎ ሜትር አልፎ ድንበር ወሮ በነበረበት ወቅት አፋቸውን ዘግተው ነበር” ሲሉ ስለ ብሄራዊ ጥቅምና አገር መውደድ የሚገለባበጠውን የአንዳንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አቋም ለማሳየት ሞክረዋል።

More stories

በመተከልና ሌሎች አካባቢዎች ተፈጥረው በነበሩ ግጭቶች የሱዳንና የግብፅ እጅ እንዳለበት ተገለጸ

March 5, 2021

የመከላከያን ጨምሮ የአሜሪካንን ሚስጢር “ለትውልድ አገሩ አቀብሏል” የተባለው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ” ብሄራዊ ጀግና” እየተባለ ነው

October 1, 2023

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ወይም ሞት እያለ ነው

March 22, 2022

“የኢትዮጵያ አምላክ እንደ ወትሮው ከእኛ ጋር ነበር ” ዐቢይ አህመድ ወደ ቢሮ መመለሳቸውን ገለጹ

December 8, 2021

ከሃምሳ በላይ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች በተገኙበት ስለ ሰላም አተገባበርና አካሄድ መረጃ ለመስጠት በተካሄደ ውይይት ላይ “ኤርትራ ትውጣ” በሚል ለተነሳው ጥያቄ አቶ ሬድዋን መልሳቸው ከላይ በተገለጸው ምክንያት ብቻ አላቆሙም። ግብጽን አንስተው የትርምስ ገመዱንና እቅዱን በማሳየት ” ይህ ሁሉ ሲሆን የት ነበራችሁ?” ሲሉ ሞግተዋቸዋል።

ተጨማሪ ይህን ያንብቡ

ራስ – በኢትዮጵያዊያን በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች IA መጠቀም የሚያስችለው መተግበሪያ

ራስ – በኢትዮጵያዊያን በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች IA መጠቀም የሚያስችለው መተግበሪያ

እንደ ቻት ጂፒቲ ( ChatGPT)ያሉ በሰውሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረቱ ዲጅታል መድረኮች በአብዛኛው በእንግሊዝኛ የሚሰሩ በመሆናቸው ለኢትዮጵያውያን ተጠቃሚዎች ምቹ…

በግብፅ የቀብር ስፍራዎች 3ሺህ ዓመት ያስቆጠረ ማር ተገኘ

በግብፅ የቀብር ስፍራዎች 3ሺህ ዓመት ያስቆጠረ ማር ተገኘ

አዲስ ሪፖርተር – ማሩ አሁንም ጣፋጭነቱ የሚያስደምም ነው ተብሎለታል። የንብ ማር ልዩ ባህሪያት በድጋሚ በአስደናቂ ሁኔታ ተረጋግጧል የተባለ ሲሆን…

ፍቅረ ማርቆስ ደስታ – ኢትኖግራፈሩ ደራሲ

ፍቅረ ማርቆስ ደስታ – ኢትኖግራፈሩ ደራሲ

የኢትዮጵያ የልብ-ወለድ ድርሰት (creative writing) ከሚታዩበት ድክመቶች አንዱ እንደ ሌሎች ሀገራት ድርሰት ፈርጀ ብዙ አለመሆኑ ነው። ደራሲዎቹ በአብዛኛው የሚያተኩሩት…

Something went wrong. Please refresh the page and/or try again.

“… ግብፅ በሚሊዮን በሚቆጠር ገንዘብ መድባ ለጋምቤላ፣ ለኦነግ ሸኔና ለትህነግ ጭምር በአየርና መሬት ወደ ኢትዮጵያ መሳሪያ እያስገባች ስታስታጥቅ፣ ተቃዋሚዎቹ ፓርቲዎች ምንም አላላችሁም” ሲሉ ፈትነዋቸዋል። አክለውም “ይህ [የተቃዋሚዎች አቋም]የሚያሳየው እንቅስቃሴው መንግሥትን የሚያዳክም ሲሆን ዝምታ፣ መንግሥትን የሚያግዝ ሲሆን ደግሞ ጩኸት ማብዛት የሚወዱ በመኖራቸው ነው” ሲሉ የሁከቱና የመንግስት መዳከምን መሰረት አድርገው እንደሚንቀሳቀሱ ነግረዋቸዋል።

ሬድዋን “ኤርትራ እኛን አስቸገረን ካላልን ምን አሳሰባቸው?” ሲሉ ጠይቀው፣ “ኤርትራ ባስቸገረን ጊዜ እኛ ራሳችን በቃን እንላለን፡፡ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ካሳሰባችሁ ሱዳን ትውጣ ብላችሁ መግለጫ አውጡ” ሲሉ መንግስትና ኤርትራ ተናበው እንደሚሰሩ፣ ይህ የማይናወጥ አብሮነት እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። ፍትሃዊ አቋም ማራመድ ሲጀመሩ “ኤርትራ ትውጣ ብትሉ እኛ መረዳት እችላለን” ሲሉ ጉዳዩ ላይ ያለው መንሸዋረር እንዲጠራ አሳስበዋል። መክረዋል።

ግልጥ ያለውን የመንግስትን አቋም ሲያስታውቁ “በእኛ [ኢትዮጵያን] አስታኮ የኤርትራ መንግሥትን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም፡፡ ቢያንስ ከተፈጠረው የሰላም ስምምነት አንፃር እኛ እንዳንፈርስ አግዘውናል” ብለዋል። ከዚህ ቀደም ትህነግ መንግስትንና ኤርትራን ለማጣላት ሂሳብ እያሰላ የመንቀሳቀስ ስልት እንደሚከተል ገልጸን መዘገባችን የሚታወስ ነው። የኤርትራ መንግስት ደግሞ “ትህነግ ስጋት እስከሆነ ድረስ ለደህንነታቸው ሲሉ ከገቡበት ለቀው እንደማይወጡ ሲያስታውቁ መቆየታቸው የሚታወስ ነው።


” … አብይ አሕመድ በብርሃን ፍጥነት ኤርትራ የዘለቁትና አገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ዓለምን ጉድ ያሰኘ የፖለቲካ እርቅ በማካሄድ የመቻላቸው ሚስጢር ቁልፍ ዛሬ ላይ የሆነውን በማየትም የማይገባቸው ካሉ ችግር ነው። እሳቸው ኢትዮጵያን ሲረከበቡ ምን ምን አስቀድመው እንደሚፈጽሙ ተረድተው ስለጀመሩ ነው ብዙ ጊዜ ‘ልንሰራ ያሰብነውን ከማንም በላይ የሚረዱት ጠላቶቻችን ናቸው የሚሉት። ሰሞኑንንም ‘ ለማድረግ አስበን የተነሳነውን ሌሎች የአፍሪካ አገራት ይከተሉታል በሚል መከራችን የሚበዛው ጉዟችን ወዴት እንደሆነ ስለተረዱት ነው’ ብለው ሰፊ መግለጫ ሰጥተዋል። ኤርትራ ሲገቡም ለምን እንደገቡ ከነ ሙሉ አስፈላጊነቱ፣ ወዳጅነቱንም ከነ ሙሉ እመነቱ ያደረገጉት ለዚህ ነው” ከማህበራዊ ገጽ ግርጌ የተወሰደ


አቶ ሬድዋን ይህንኑ የኤርትራን አቋም ግንዛቤ ውስጥ በመክተት፣ ከዛም በላይ በመናበብ እንደሚሰሩ ግልጽ በማድረግ ዲፕሎማሲያዊ ሃረግ አክለዋል። “የጋራ ጠላት የነበረን ቢሆንም” አሉ የደህንነት አማካሪው፣ “ትጥቁን የፈታ የትህነግ ታጣቂ ግን ኢትዮጵያዊ ነው”ሲሉ ትህነግ ካልታጠቀ ስጋት እንደማይሆን አስታውቀዋል። ትጥቅ መፍታቱ ኤርትራናም ሆነ በትግራይ ዙሪያ ያሉትን ወገኖች ሰላም እንደሚሰጥ ከስምምነቱ በሁዋላ በተደጋጋሚ ሲገለጽ ነበር። በዚሁ ማዕቀፍ ውስጥ ሆነው “… ስለዚህ አቅማችን ባለበት እስኪጠናከር ትህነግ መጀመሪያ ትጥቁን መፍታት ይጀምርና እንደማንወጋ ስናረጋግጥ፣ ከጀርባችን ያለው አካል ማንም ይሁን ማን ይውጣልን ማለት እንችላለን” ሲሉ አመክንዮ የተሞላው ምላሽ ሰጥተዋል። ኢትዮጵያና ኤርትራ የደንነትና ወታደራዊ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።

ወልቃይትን አስመልክቶ ከግራና ቀኝ በተዘዋዋሪ መንገድ ለሚነሳው ጥያቄ ምላሽ እንዲሆን ባስበ መልኩ ይመስላል አቶ ሬድዋን የተናገሩት። ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ የሱዳን መውጪያ በርም ልክ እንደ አሰብ ሁሉ እንዳይወሰድ በሚል ስጋታቸውን ጨምረው ላነሱት “ከጅምሩ የጦርነቱ ዓላማ ወልቃይትን ማስመለስና ትህነግን ማጥፋት አልነበረም” ሲሉ ነው አቶ ሬድዋን ያስታወቁት። የጦርነቱ ዋና ዓላማ የአገሪቱን ሉዓላዊነት ማስከበርና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ማስፈን እንደነበር አሳስበው፣ “ትህነግን እንደ ፖለቲካ ኃይል የማጥፋት ዓላማ ያለው ሰው ይኖራል፣ ነገር ግን የፌዴራል መንግሥቱ ዓላማ አይደለም” ሲሉ ትህነግን ማቀፍም ሆነ መግፋት የትግራይ ህዝብ ውሳኔ እንጂ የሌሎች አካላት እንዳልሆነ አመላካሽ ምላሽ ሰጥተዋል። ከላይ እንደገለጹት ትጥቅ የፈታ ትህነግ ኢትዮጵያዊ ነውና።

ወልቃይት በአማራና በትግራይ ክልሎች መካከል ያለ ፀብ በመሆኑ በሁለት ክልሎች መካከል ያለው ፀብ ደግሞ የሚፈታው የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሚመራው ሥርዓት በህግና ህግ ብቻ እንደሆነ አመልክተዋል። የፌደራል መንግስት ባለው የህግ አግባብ የህግ ጨዋታውን ገለልተኛ ሆኖ ማስፈጸም እንጂ ሌላ ተልዕኮ ሊኖረው እንደማይችል ባለሙያዎችም ሲናገሩ ነበር።

“የፌዴራል መንግሥትን አቅም ተራ በተራ ጡንቻ እየተፈታተን አንዳችን ሌላችንን ማንበርከክ ይቁም” ሲሉ ጉልበት መፍትሄ እንደማያመጣና አንዱ ሲደክም ሌላው ሲበረታ፣ የሚገኝ ድል አስተማማኝ እንደማይሆን ገልጸዋል።

“ወልቃይትን ከዚህ ቀደም ትህነግ ጡንቻ ስለነበረው በጉልበት ወስዷል” ሲሉ ያለፈውን አካሄድ ፍትሃዊ እንዳልነበር ያወሱት አቶ ሬድዋን፣ ዛሬ ትህነግ ሸብረክ ሲል ጡንቻ ያለው አካል ይውሰድ ካልን መጪው ትውልድ 20 ዓመት ጠብቆ ድንገት ጡንቻ ካገኘ ዳግም ይወስደዋል። ስለዚህ ዘላቂው መፍትሔ ጡንቻ ሳይሆን ሕግና ሥርዓት ነው” ሲሉ ጉዳዩ በህግ አግባብ መፍትሄ ሊበጅለት እንደሚገባ የመንግስታቸውን አቋም ይፋ አድርገዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኤርትራ ወታደሮች ከሽሬና አክሱም ለቀው ወደ ራሳቸው ድንበር መጠጋታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል። ሮይተርስ እንዳሻው የሚያገኛቸውን አቶ ጌታቸው ለማረጋግጫ ፈልጎ እንዳላገኘ በዜናው ጠቅሷል። የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረ መስቀል ተጠይቀው ማረጋገጫም ሆነ ማስተማመኛ እንዳልሰጡት፣ ነገር ግን ዕርዳታ ሰራተኞች እንደነገሩት ገልጾ ሮይተርስ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ይህ የትህነግ ወዳጅ ለሆኑንና “ኤርትራ ሰራዊቷን ታስወጣ” ለሚሉ ሁሉ ከቢድ ዜና በመሆኑ ትህነግ እውቅና ሊሰጠው እንደማይፍለግ እምነታቸው የሚገልጹ አሉ።

የትህነግ ታጣቂዎች መሳሪያቸውን ባስረከቡ መጠንና ለማናቸውም የአገሪቱም ይሁን የጎረቤት መንደሮች ስጋት መሆናቸው በተመናመነ ቁጥር ኤርትራ ወታደሮቿን እንድትስብ ከመንግስት ጋር በስምምነት እንደሚሰራ ገልጸን መዘገባችን ይታወሳል። በዚህ ዜናችን የኤርትራና ኢትዮጵያ ወታደሮች ሰላምታ በመቀያየር ምሽግ መረካከባቸውን ነበር የገለጽነው።

“የእኛ ወገን የምንላቸው የትህነግ ሰዎች ለሰላሳ ዓመታት ታገልኩለት ያሉትን ሕዝብ ለሰላሳ ዓመታት እየቀለበ፣ እየጠበቀ፣ አብሮ እየሠራና እያረሰላቸው የኖረውን ሠራዊት ከጀርባው አርደው ሜዳ ላይ ሲጥሉት የታደጉት እነዚህ [ኤርትራን ማለታቸው ነው] ሰዎች ናቸው፡፡ ለአጭር ጊዜም ቢሆን ውለታን መርሳት ነውር ነው” ሲሉ አቶ ሬድዋን ኤርትራ ላይ እጃቸውን ለሚቀስሩ ማሳረጊያ ሰጥተዋል።

ከሰላም ስምምነቱ ዜና ደስታና ፈንጠዝያ ጎን ለጎን “መላከላከያን ያረዱ፣ ያሳረዱና የተባበሩ ላይ ፍትህ ሊበየን ይገባል” የሚሉ ድምጾች የተሰሙትም ለዚሁ ነው። ከዚህም በተጨማሪ በትግራይ፣ በአፋርና አማራ እንዲሁም በተዘዋዋሪ በሌሎች አካባቢዎች በንጹሃን ላይ ጭፍጨፋ የፈጸሙና ያስፈጸሙ፣ የህዝብ ንብረትና ማህበራዊ መገልገያዎችን ያወደሙ፣ የጅምላ ግድያ ያስፈጸሙ ወዘተ ላይ ብሄር፣ ሰፈር፣ ቋንቋና ማንነት ሳይለይ ህግ እንዲጸናባቸው ፍትህ ወዳድ ዜጎች እየጠየቁ ነው።

ድንገት ወደ መቀለ ባመራው የመንግስት ልዑክ አካላት ውስጥ የፍትህ ሚኒስትሩና የእርቅ ኮሚሽን አባላት መካከታታቸው በህግ ተጠያቂነት አግባብ ከትህነግ አመራሮች ጋር ለመነጋገር እንደሆነ ውስጥ አዋቂዎች እየገለጹ ነው። ይህን ለማድረግ ቅሬታ ቢኖር እንኳን ” ወንጀለኞች በህግ አይጠየቁ” የሚል መከራከሪያ በማንሳት ዓለም አቀፍ ጫና ሊነሳ እንደማይችል የህግ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። በሰላም ውሉም ላይ ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል ይህ ፍትህ አንዱ ነው።

በዜናው የተጠቀሱት አቶ ሬድዋን ያተናገሩት ከሪፖርተር ዜና ላይ ቃል በቃልና የተወሰደና በዝጅት ክፍሉ አባሪ መረጃዎ እንደገና የተጻፈ ዜና ትንታኔ ነው ።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

Ethioreview news

A journalist

የኑዛዜ አይነቶችና የኑዛዜ ማረጋገጫ
የትግራይ ሕዝብ ከትህነግ ምን አተርፈ? መላሹ የትግራይ ሕዝብ ብቻ ነው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 20260
Load more
Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 20260
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 20260
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 20260
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedbusinesshotarchivetips
    © Copyright 2026, All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2
    • Home Demo news