Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  ኢሳት ቴሌቪዥን የመጨረሻ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጠው

ኢሳት ቴሌቪዥን የመጨረሻ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጠው

Ethioreview newsEthioreview news—April 13, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ባለስልጫኑ ለኢሳት በጻፈው በዚሁ ደብዳቤ ላይ፤ ቴሌቪዥን ጣቢያው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሚዛናዊነት የጎደላቸው፣ በመረጃ ያልተደገፉ/ያልተረጋገጡ የህዝቦች መተማመንና አንድነትን ሊሸረሽሩ የሚችሉ ዘገባዎችን በተደጋጋሚ በማቅረብ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ1238/2013 የጥላቻ ንግግርና የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣን አዋጅ 1185/2012 እና የጋዜጠኝነት ስነምግባርን በመጣስ ላይ ይገኛል ብሏል።

ባለስልጣኑ ለአብነት ብሎ በቴሌቪዥን ጣቢያው የተፈጸሙ ግድፈቶችን የጠቀሰ ሲሆን፤ ጣቢያው የካቲት 23/2015ዓ.ም በዕለቱ የኦሮሚያ ክልል ኢአ ዙሪያ ሸገር ከተማ የዜጎችን ቤት በማፍረስ ግፍ መፈጸሙን ድምጻዊ መብሬ መንግስቴ ተናገረ፡ ድምጻዊው በዜጎች ላይ የተፈጸመው በደል ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት መሆኑን ገልጿል…..” የሚል ዜና የቀረበ ሲሆን በዘገባው የተጠቀሱ አካላት ሃሳብና አስተያየት ሳይካተት ድምዳሜ ላይ የደረሰ በመረጃ ያልተደገፈና ሚዛናዊነት የጎደለው ዘገባ አስተላልፏል ሲል አስታውቋል፡፡

በተጨማርም ኢሳት፤ መጋቢት 6/2015ዓ.ም “የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ወደ ከተማው የሚገቡ ዜጎችን አስመልክቶ ያደረጉት ንግግር ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጭና የሰዎችን የመንቀሳቀስ መብት የሚጥስ መሆኑን የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ” የሚል መረጃ ያቀረበ ሲሆን፤ በዘገባው የጫካ ፕሮጀክት አንድ ሚሊየን የሚጠጋ በጣም አቅመ ደካሞች የሚባሉ ዜጎች አፈናቅሏል፤ የቤት ፈረሳውን የሚመራውን ግብረ ሀይል ቤቶቹን ከማፍረስ ባሻገር የንብረት ዘረፋ ውስጥ ተሰማርተዋል፤ የሚገድሉ፣ የሚዘርፉ እና የሚደበድቡ ሰዎች ናቸው እያስተዳደሩን ያለው” የሚሉ በሰነድ/በማስረጃ ያልተረጋገጡና የተቋማትን መልካም ስም የሚያጠፉ፤ ሚዛናዊነት የጎደላቸው ዘገባዎችን አሰራጨቷል ሲል ነው ባለስልጣኑ የገለጸው።

መጋቢት 12/2015ዓ.ም ደግሞ፤ “በኦሮሚያ ክልል መቂ ከተማ እድሜያቸው 18 አመት ያልሞላ ታዳጊዎች ለወታደራዊ ስልጠና እየተመለመሉ ነው ሲሉ ወላጆች ለኢሳት ገለጹ” በሚል አርዕስተ ዜና ስር በከተማዋ ከክልሉ ተወላጆች ውጪ ያለ አካል እንዳይኖር የማድረግ እቅድ አለ የሚል ዘገባ ቀርቧል ያለው ባለስልጣኑ፤ መረጃው ሚዛናዊነቱን ያልጠበቀ፤ የተዓማኒነት(የምንጭ) ችግር የተስተዋለበት ምንጮቻችን ነገሩን ከማለት ውጪ የድርጊቱን እውነትነት ሊያረጋግጡ በሚያስችሉ ማስረጃዎች ያልተመላከቱና በህብረተሰቡ ዘንድ ጥርጣሬና ስጋትን ሊፈጥር የሚችል ጥንቃቄ የጎደለው ዘገባ ነው ሲል አስታውቋል።

More stories

በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ በ6 ግለሰቦች ላይ የ15 ቀን ክስ የመመስረቻ ጊዜ ተፈቀደ

August 16, 2024

በ12 ዓመቱ ታዳጊ ላይ የግብረ-ሶዶም ጥቃት ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በ14 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል ።

August 4, 2021

ዜና ሌብነት – ደህንነትን የሌብነት ዜና ዳር ዳር እያለው ነው፤ በማይወራረድ ብር ዘረፋ መኖሩ ተሰምቷል

December 3, 2022

በወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መግለጫ

March 10, 2023

መጋቢት 13/2015 ዓ.ም ጣቢያው አዲሱ የሽገር ከተማ አስተዳደር ምስረታን ምክንያት በማድረግ በተጠና እና ማንነትን መሰረት ባደረገ መልኩ በክልሉ የሚኖሩ የኦሮሞ ብሄር ማንነት የሌላቸው ዜጎችን ቤት ለይቶ እያፈረሰ እንዲሁም ከክልሉ እያስወጣ ስለመሆኑ የሚያስረዳ ዘገባ ቀርቧል ሲልም ነው ባለስልጣኑ የጠቀሰው። ዘገባው የተነሳውን ርዕሰ ጉዳይ ትክክለኝነት ለማረጋገጥ ጥረት ያላደረገና በህዝቦች አብሮነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ሊያስከትል የሚችል ነውም ሲል ገልጿል።

መጋቢት 22/2015ዓ.ም ደግሞ “ከኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን የተመለመሉ የአማርኛ አስተማሪዎች አዲስ አበባ መግባታቸው ተሰማ” በሚል ዘገባ ጣቢያው ትምህርት ቢሮን ሆነ ሌሎች ተገቢ አካላትን ሳያካትት በህብረተሰቡ ዘንድ ብዥታን ሊፈጥር የሚችል ኢ-ሚዛናዊ ዘገባ አቅርቧልም ነው የተባለው።

ቴሌቪዥን ጣቢያው ከላይ የተጠቀሱትንና ሌሎች ከጋዜጠኝት ስነምግባርና መርህ ጋር የሚጣረሱ ማህበራዊና ተቋማዊ ሃላፊነትን ከመወጣት አኳያ ክፍተት ያለባቸውን ዘገባዎች በማሰራጨት የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ 1238/2013 አንቀጽ 68/1(ሀ)እና (ለ) ፕሮግራሞች ወይም ዜናዎችን የተለያዩ አመለካከቶችን በማንጸባረቅ አጠቃላይ ህብረተሰቡን እንዲያገለግሉ ሚዛናዊ እና ከአድሎ የጸዱ አድርጎ ማቅረብ፤ የሚሰራጨው ፕሮግራም ወይም ዜና ይዘትና ምንጭን እውነተኛና ትክክለኛ መሆናቸውን ለማረጋገጥ አሰራጩ ሪፖርቱ ላይ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ በሚል የተቀመጡ ህጎችን ያላከበረ መሆኑ በደብዳቤው ላይ ተገልጿል።

የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ 1238/2013 አንቀጽ 68/2(መ)(ሠ) የወንጀል ድርጊት እንዲፈጸም እና ሰላም እና ጸጥታ እንዲደፈርስ የሚቀሰቅስ መሆን የለበትም ያለው የባለስልጣኑ ደብዳቤ፤ በብሮድካስት አገልግሎት ለስርጭት የሚቀርብ ማንኛውም ፕሮግራም ወይም ዜና የማንኛውም ሰው ዘር ቋንቋ እና ብሄርን መሰረት በማድረግ እንዲጠላ ወይም እንዲገለል የሚቀስቅስ መሆን የለበትምየሚሉትን ድንጋጌዎችን የጣሰ ስለመሆኑ ተገልጿል።

በተጨማሪም የጥላቻ ንግግርና የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣ አዋጅ 1185/2012 አንቀጽ5 ማንኛውም ሰው የሀሰት መረጃን በአደባባይ፣ ስብሰባዎች በብሮድካስት፤ በህትመት ወይም በማህበራዊ ሚዲያ ወይም በሌላ ተመሳሳይ ዘዴዎች አማካኝነት በጽሁፍ፤ በምስል፣ በድምጽ ወይም በቪዲዮ ማሰራጨት የተከለከለ ተግባር እነደሆነ የጠቀሰው ደብዳቤው፤ የኢሳት ዘገባዎች እነዚህን ድንጋጌዎች የጣሱ መሆናቸው ተስተውለዋል ነው ያለው።

ጣቢያው ሚዛናዊነት የጎደላቸውን ሀሰተኛ fገባዎችን በማሰራጨት በህዝቦች አብሮነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚፈጥሩ መረጃዎችን ከማስተላለፍ እንዲቆጠብ የመጨረሻ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው መሆኑንም ባላስልጣኑ አስታውቋል።

ENA

law
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Obbo Ahimad Shiidee, dhaabbileen Ameerikaa Itiyoophiyaa keessatti hojii investimentiirratti akka hirmaatan waamicha dhiheessan.
ኦሮሚያ ልዩ ሃይሉን አክስሞ ሃላፊነቱን ለመከላከያ አስረከበ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2