Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  “በወልቃይት ምንም ጦርነት የለም፤ ከመከላከያ ጋር አብረን እየሰራን ነው” ኮሎኔል ደመቀ
News

“በወልቃይት ምንም ጦርነት የለም፤ ከመከላከያ ጋር አብረን እየሰራን ነው” ኮሎኔል ደመቀ

Ethioreview newsEthioreview news—July 24, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አቶ ዮሃንስ ቧ ያለው መከለላከያን አጠልሽተው ክልሉን ለቆ እንዲወጣ በጠየቁ ማግስት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የሰላምና የፀጥታ መምርያ ኃላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በአካባቢው ምንም ዓይነት ጦርነት አለመኖሩን፣ ከመከላከያ ጋርም አብረው በስምምነት እየሰሩ መሆናቸውን አመለከቱ።

በክልሉ መደበኛ ጉባኤ መከላከያ የትህነግ ሃይል አማራ ክልል ላይ የፈጸመውን ወረራ ከህዝብ ልጆች ጋር ሆኖ እንዴት እንደመከተና ምን ያህል መስዋዕትነት እንደከፈለ በመዘንጋት ” ወራሪ፣ አተራማሽ” በሚል አቶ ዮሐንስ ያጠለሹትን የአገር መከላከያ ሰራዊት፣ ኮሎኔል ደመቀ ‹‹የአገር መከላከያ ሠራዊት የወልቃይት አካባቢን እየተከላከለና እየጠበቀ እንዳለ ነው የምናውቀው፤በአካባቢው ከመከላከያ ጋር ምንም ዓይነት ጦርነት የለም፣ ተባብረን ነው እየሠራን ነው፡፡ አካባቢው ሰላማዊ በመሆኑ ፋኖ በሚል ምክንያት ምንም ዓይነት ግጭትም ሆነ ጦርነት የለም፤›› ሲሉ በተለይ ለሪፖርተር አስታውቀዋል።  

አቶ ዮሐንስ ቧያለው ወልቃይት ጠገዴ ጠለምትን ጨምሮ የማንነትና የድንበር ጥያቄ ያለባቸውን አካባቢዎች በተመለከተ ” ሕዝብ እንዲወስን ይደረጋል፣ በህጋዊ መንገድ ይቋጫል” የሚል ዝርዝር የሌለውና የቦታን ስም ያልጠቀሰ አቅጣጫ እንደተያዘ ፍንጭ መሰጠቱን ተከትሎ ” ህዝብ እንዲወስን የሚደረገው አማራ ጋር ሲደርስ ነው ወይ?” በሚል በምክር ቤት ተቃውሞ አሰምተዋል ህዝብ ካልወሰነ ማን እንደሚወስን ፍላጎት እንዳላቸው አላብራሩም።

በደቡብ ክልል የተለያዩ ውሳኔዎችን መወሰናቸውን በዋቢነት አንስተው ይህ መብት ለአማራ መነፈጉን ገልጸዋል። በደቡብ ክልል የክልልነትና የዞንነት ጥያቄዎች ምላሽ ያገኙት በህዝብ ውሳኔ እንደሆነ የሚታወቅ ቢሆንም፣ ምርጫ ቦርድ ሪፖርት ማቅረቡም ግልጽ ሆኖ ሳለ የአቶ ዮሐንስ ማነጻጸሪያ ምን ይዘት እንዳለው ለበርካቶች ግራ አጋብቷል። በተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በተሰራጨው የምክር ቤት ንግግራቸው ” የእን አምባቸው አጥንት ይወጋናል” ሲሉ መማጸናቸው ደግሞ አቶ ዮሐንስ እነ ዶክተር አምባቸውን ማን እንደገደላቸው ለሚያውቁ መነጋገሪያ ሆኗል። ብዙ ጉዳዮችን በወቀሳና በጉድለት ያስነሱት አቶ ዮሐንስ እግረ መንገዳቸውን እንኳን በአማራ ክልል አመራሮችና የጸጥታ ሃሎች ላይ የሚፈጸመውን ግድያ አላነሱም።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ይህ ንግግራቸው በተሰራጨ በማግስቱ ብረት አንስተው ሰሜን ሸዋ ከሚገኝ ክፍል አመራር ጋር ውይይት ማድረጋቸውን የሚያሳይ የድምጽ ቅጂያቸው አደባባይ ወጥቷል። አቶ ዮሐንስ ባገኙት ስልክ እንደሚጠቀሙና ቋሚ ስልክ እንደሌላቸው ጠቅሰው ከጉዳቸው ጋር ሲነጋገሩ የተሰማው የታጣቂውን ሃይል አቋም ሪፖርት ሲሰሙና እሳቸውም በምክር ቤት ስለተደረገው ስብሰባ ሲያስረዱ ነው።

“ትልቁ ሰው” ያሉት ማንን እንደሆነ በግልጽ ባይታወቅም የሰላም ኮሚቴ መቋቋሙ፣ ከታች መዋቅር ጀምሮ ህዝብን የማነጋገር ስራ እንደሚጀመር አመልክተው “ጊዜ ይወስዳል። ለጊዜው ጥሩ ነው። ለመደረጃት ይጠቅመናል… የመደራደሪያ ሃሳቡን አዘጋጅቼ እንዲደርሳችሁ አደርጋለሁ” ሲሉ በስልክ ድምጻቸው ተሰምቷል። አቶ ዮሐንስ ቧያለው የኢትዮጵያን ደህንነት ዋጋ የሌለው እንደሆነ በተናገሩ ሰዓታት ውስጥ ድምጻቸውን መቅዳት ችሏል። ይህ እስከተጻፈ ድረስ አቶ ዮሐንስ “ድምጹ የእኔ አይደለም” የሚል ማስተባበያ አላቀረቡም። ከዚህ ቀደም የአቶ ግርማ የሺ ጥላን ግድያ አስመልክቶ የተደረገ የስልክ ምልልስ ይፋ መሆኑንን ተከትሎ “ፌክ” እንደሆነ ቢገለጽም፣ ድምጹን አጣርቶ “የተሰራ ነው” ያለው ድርጅት የተባለውን ማረጋገጫ አለመስጠቱን፣ ሰጠ በተባለው ማስረጃ ላይ ያለው የስልክ ቁጥር አገልግሎት ላይ ያለዋለና የማይሰራ እንደሆነ ማረጋገጥ ተችሏል። ይህን በተመለከተ ሙሉ መረጃ በቀናት ውስጥ እናስነብባለን።

“የአማራና የትግራይ ክልሎች የሚዋሰኑባቸውንን የወልቃይት፣ የጠለምትና የራያ አካባቢዎች ይገባኛል ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ላቀረቡት ጥያቄ የሚሰጠውን ውሳኔ እየጠበቅን ነው” ሲሉ የጉዳዩ ባለቤት ኮሎኔል ደመቀ አስታውቀዋል። ኮሎኔል ደመቀ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ በቅርቡ የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸም ለፓርላማ ባቀረቡበት ወቅት ሁለቱ ክልሎች የሚዋሰኑባቸውን አካባቢዎች “በሕዝብ ውሳኔና በሕጋዊ መንገድ መፍታት አለባቸው” ያሉትን እንዴት ተቀበላችሁ በማለት ለምክትል አስተዳዳሪው ሪፖርተር ጥያቄ አቅርቦላቸው ነው መልስ የሰጡት።

ጥያቄውን በማስተካከል መልስ የሰጡት ኮሎኔል ደመቀ ‹‹በወልቃይት ጉዳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውሳኔ እናደርጋለን ሲሉ በግልጽ አልሰማንም” ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩን “በህግ ይቋጫል” ንግግር ነቅሰው ወደ ፈለጉበት መንገድ ሲጎትቱ ለነበሩ መልስ የሚሆን አስተያየት ሰጥተዋል። “ነገር ግን” አሉ ኮሎኔሉ ” በሕጋዊ መንገድ ቢፈታ ይሻላል የሚለውን ምክር አዘል ነገር ለፓርላማው ሲናገሩ ሰምተናል፡፡ ግን በዚህኛው ቀጣና በዚህኛው ዞን ብለው ሲያነሱ እኔም በግል አልሰማሁም፣ እኛም የምናውቀው ነገርም የለም፤›› በማለት እንደ ጉዳዩ ባለቤት “ሰማሁ” ያሉትን ጠቅሰዋል። አይይዘውም ‹‹ነገር ግን የወልቃይት ጉዳይ በየትኛው መንገድ ነው ሊፈታ የሚገባው የሚለውን ቀደም ሲል በተደጋጋሚ ተናግረናል፡፡ ሊፈታ በሚገባው መንገድ እንዲፈታ ለመንግሥት አመልክተናል፤›› ሲሉም አስረድተዋል፡፡

ራያም፣ ጠለምትም፣ ወልቃይትም ስላሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለየትኛው እንደተናሩ ግልጽ እንዳልሆነላቸው ገልጸው በግምት መልስ ለመስጠት ያስቸግራል ብለዋል፡፡ ‹‹ብዙ ሰው መላምት ሊኖረው ይችላል፡፡ ነገር ግን የወልቃይት ጉዳይ ሊፈታ የሚገባበትን መንገድ ጠቅሰን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ስላቀረብን ውሳኔውን እየጠበቅን ነው፤›› ሲሉ መናገራቸውን ሪፖርተር አመልክቷል።

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅትም ሆነ አሁን ከማኅበረሰቡ ጋር እንዳሉ ገልጸው፣ ‹‹የአገር መከላከያ ሠራዊት የወልቃይት አካባቢን እየተከላከለና እየጠበቀ እንዳለ ነው የምናውቀው፤›› ያሉት ኮሎኔል ደመቀ፣ ‹‹በአካባቢው ከመከላከያ ጋር ምንም ዓይነት ጦርነት የለም፣ ተባብረን ነው እየሠራን ነው፡፡ አካባቢው ሰላማዊ በመሆኑ ፋኖ በሚል ምክንያት ምንም ዓይነት ግጭትም ሆነ ጦርነት የለም፤›› ሲሉ አክለዋል፡፡   

ትህነግ የሚመራው ኢህአዴ ዒትዮጵያን ሲቆጣጠር ወደ ራሱ ክልል ያካተታቸውን አካባቢዎች ከወረራው በሁዋል በመነጠቁ ከሰላም ስምምነቱ በሁዋላ “አካባቢዎቹ ይሰጡኝ” ሲል ጥያቄ ማንሳቱ ይታወሳል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳዳር የክልሉ አስተዳደራዊ ወሰን ከጦርነቱ በፊት ወደ ነበረበት እንዲመለስ፣ በጦርነቱ ምክንያት ከምዕራብ ትግራይና ከሌሎች የአማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የተፈናቀሉ የክልሉ ነዋሪዎቸ በአፋጣኝ ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ አሁንም ጥያቄ እያቀረበ ነው።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር አባል ክንደያ ገብረ ሕይወት (ፕሮፌሰር) ከጥቂት ሳምንት በፊት በጉዳዩ ላይ ሪፖርተር ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹የወሰን ጥያቄ ለምን ይነሳል አንልም፡፡ ነገር ግን ጥያቄው በሕገ መንግሥቱ መርህ ይፈታል ብለን ነው የምናምነው። የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነትም የሚያስቀምጠውም ይህንኑ ነው፤›› ማለታቸው ሪፖርተር አስታውሷል። ጦርነት አማራጭ ባለመሆኑ ችግሩ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ክልላቸው እንደሚፈልግ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች በቅርቡ በባህር ዳር ያደረጉት ጉብኝትም ችግሩን በንግግር ለመፍታት በር የከፈተ እንደሆነ መግለጻቸውንም አመልክቷል።

ቀደም ሲል ኮሎኔል ደመቀ የአማራ ማንነት ከተከበረ፣ አካባቢው የአማራ መሆኑና በጉልበት በፖለቲካ ውሳኔ እንደተወሰደ ግልጽ ሆኖ በህግ ከተቋጨ እንኳን ቀደም ሲል ሲኖሩ የነበሩ ማንም ኢትዮጵያዊ ሊመጣና ሊኖር እንደሚችል ማስታወቃቸው አይዘነጋም።

በወልቃይት ጠገዴ ጸለምት ይኖሩ የነበሩ የአማራ ተወላጆች በአማርኛ መዝፈን፣ የኢትዮጵያን ባንዲራ መያዝ፣ በአማርኛ መማርን የመርሳሰሉ ሰብአዊ መብታቸው ተገፎ፣ በርካቶች ከመኖሪያቸው ተፈናቀልውና በግፍ ተገድለው፣ ታስረው ወዘተ በስቃይ ሃያ ሰባት ዓመታትን ማሳለፋቸውን ምስክረነት መስጠታቸው ይታወሳል።

ይህንን ማስፈንጠሪያ ethio12news ተጭነው በቴሌግራም ገጻችን ይከተሉን

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በሼፍ ሳሙኤልሰን ማርኩስ ስም ሃያት ሪኤጀንሲ ሆቴል የሚከፍተው ሬስቶራንት ስልጠና አወዛገበ “የደንበኞችን ጾታ መጥራት አትችሉም”
ከአርባ ሚሊዮን ብር በላይ ለ217 ፍሬ አልባሳት፤ አመራሩ ሰራተኞቹና አቅራቢዎቹ በሌብነት ክስ ተመሰረተባቸው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2