የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዝዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን አዲስ አበባ ሲገቡ ሚኒስትሮቻቸውን በሙሉ በመያዝ ነው። ኢትዮጵያ በሽግግር ወቅት ታንቃ የነበረችበትን የዕዳ ሸምቀቆና የትህነግ ወረራ ለመመክተ የመሳሪያ ድጋፍ ያደረግችው አገር መሪዎች ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ የተደረገው አቀባበልም ያንን የሚመጥን እንደሆነ ታይቷል።
ፕሬዝዳንቱ አዲስ አበባ ሲገቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና ካቢኒያቸው ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በጋለና ክብራቸውን በሚመጥን መልኩ አቀባበል የተደረገላቸው የተባበሩት አረብ ኢመሬቶች የንጉሳዊያን ቤተሰቦች ለኢትዮያ እጅግ ውለታ መስራታቸው ይህንኑ አቀባበል ተከትሎ ተነስቷል።
ትህነግ በህዝባዊ አመጽ ተገዶ ስልጣኑን ሲለቅ አገሪቱ በዕዳ ሸምቀቆ ታንቃ ነበር። ዕዳ መክፈል ባለመቻሏ ንብረቷን ልታጣ፣ ክብሯን ልክትገፈፍ ጫፍ ደርሳ ለነበረችው ኢትዮጵያ የሶስት ቢሊዮን ዶላር ስጦታ በመስጠት ውለታ የሰራች ብቸኛ አገር ኢመሬትስ በቀና አሳቢ ዜጎች ዘንዳ ክብር አላት።
መከላከያ በክህደት ታርዶ፣ መሳሪያው ሁሉ ተዘርፎ፣ ሎጂስቲኩ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ተወስዶ ባዶ ቀርቶ ወረራ በተፈጸመበት ወቅይ ኢመሬትስ ኢትዮጵያ እንደ አገር እንድትጸናና ወረራውን እንድትመክት ድሮን ጨምሮ ከፍተኛ የጦር መሳሪያ እገዛ ማድረጓን የሚረዱ አሁንም ለዚህች አገር ውለታ እውቅና ይሰጣሉ።
በርካታ በገሃድ የማይጻፉና የማይነገሩ ውለታዎችን የፈጸመችው ይህቺ ቱጃር አገር፣ ኢትዮጵያ በተጠና ዘመቻ አገራት፣ ዓለም ዓቀፍ ተቋማት፣ ሚዲያዎች፣ የታላላቆቹ አገራት መሪዎች ጫና አሳድረው ሊያፈርሷት በተረባረቡ ወቅት የተባበሩት ኢመሬትስ ልክ እንደ ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጎን በመቆም በተለያዩ ጊዜ ወደፊት በሚገልጻቸው አግባቦች ሁሉ ድጋፍ አድርገዋል።
ለዚህም ይመስላል ኢትዮጵያ አረንጓዴ ምንጣፏን ዘርግታ ” እንኳን ደህና” መጣችሁ ስትል በኢትዮጵያዊ ክብር እንግዶቿን የተቀበለችው። ከቦሌ ዓለም ዓቀፍ አየር ማረፊያ ጀምሮ በጎዳና ላይ በሚማርክ አጀብ እንግዶቿን አጅባ ወደ ታላቁ ቤተመንግስት በማስገባት በዚህችው አገር እርዳታ የተዋበውን ቅጥር አስጎብኝታለች።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው “እያደገ የመጣው የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በመከባበር እና ለጋራ እድገት የጋራ ራዕይ ላይ የተመሰረተ ነው” ሲሉ ቀድመው እንደገለጹት ከጉብኝቱና መስተንግዶው ጎን ለጎን አስራ ሰባት ስምምነቶች መደረጋቸው ጉዳዩ ከአቀባበሉ ድምቀት በዘለለ ሌላ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው አሳይቷል።
“ዘላቂ ልማትን ለማስቀጠል ትብብራችንን እንቀጥላለን” የገለጹት አብይ አሕመድ ከፕሬዝዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ያላቸው እጅግ የጠነከረ ወዳጅነትን ለማሳየት ” ወንድሜ” ሲሉ ደጋግመው ይጠራቸዋል። ይህ አጠራራቸውና ከፕሬዚዳንቱ ጋር ያላቸው የጠበቀ ግንኙነት ያልተመቻቸው ዘለፋ ሲሰነዝሩና ጉብኝቱን ሲያጣጥሉ ታይቷል።
የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዝዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን መላ ካቢኒያቸውን ይዘው መምጣታቸውና ከአስራ ሰባት በላይ ስምምነቶች መከናወናቸው ግርምት የፈጠረባቸው ደግሞ አድናቆትን ችረዋል።
በኢንደስትሪ፣ ግብርና፣ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስ፣ ንግድ፣ ኢንጂነሪንግ፣ ማህበራዊ ዘርፍ፣ የነጻ ንግድ፣ ወደብና ሎጂስቲክ፣ የንግድ ዘርፍ ተቁማት ስምምነት የሚጠቀሱ ሲሆኑ አገራቱ ሽብርተኛነትን በጋር ለመዋጋትና በደህንነት ጉዳይ አብረው ለመስራት መፈራረማቸው የሁለቱ አገራት ግንኙነት ወደ ላቀና ስትራቴጂካዊ አጋርነት መሸጋገሩን የሚያሳይ እንደሆነ ተመልክቷል።
ከፍተኛ ሃብት ከኢትዮጵያ ተዘርፎ ወደ ኢመሬትስ ባንኮች መዛወራቸው፣ የገንዘብ አጠባ ስራ የሚሰራው ባብዛኛው እዛ በሚገኙ ገንዘብ አዘዋዋሪዎች መሆኑንን ያስታወሱ ግልጽ ስምምነት ስለመደረጉ ባይናገሩም አገሪቱ በቀርቡ ህገወጥ ገንዘብ አዘዋዋሪዎች ላይ እየወሰደች ካለው እርምጃ ጋር ተያያዞ ዜና ሊኖር እንደሚችል በርካቶች ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ስለጫካው ፕሮጀክት ሲጠየቁና የገቡበትን ቆሻሻ የሞላው ቤተ መንግስት እንዴት እንዳደሱት ሲያብራሩ “ወንድሜ” የሚሏቸው ሼኽ መሐመድ ቢን ዛይድ ባበረከቱላቸው ድጋፍ አንድም የአገር ውስጥ በጀት ሳይነኩ እየሰሩ መሆናቸውን ማስታወቃቸው አይዘነጋም።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






