Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ትህነግና ሻዕቢያ በዱባይ መገናኘታቸው ተሰማ፤ አሜሪካ የፕሪቶሪያው ስምምነት ላይ አተኩራለች
News

ትህነግና ሻዕቢያ በዱባይ መገናኘታቸው ተሰማ፤ አሜሪካ የፕሪቶሪያው ስምምነት ላይ አተኩራለች

Ethioreview newsEthioreview news—August 21, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አስተዳደር እንዳቋቋመው የሚነገርለት ቡድን አቶ ጌታቸውና ሌተናል ጻድቃን የሚመሩት ቡድን አካል ከሆነ የትህነግ አካላት ጋር በዱባይ ተገናኝተው መምከራቸው ተሰማ። አሜሪካ በኦሮሚያና በአማራ ክልል ሰላም እንዲወርድ በሚል ከአውሮፓ ህብረት ጋር መላ እንደምትፈልግ አስታወቀች። የፕሪቶሪያውን ስምምነት ትግበራ እንደሚገመግሙ አመልክተዋል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን “ያገኘነውን እንዳናጣ” ሲሉ እርጋታን የተማጸኑበት መልዕክታቸው አሁን ላይ ትርጉም እያገኘ ነው።

የኢትዮ12 መረጃ አቀባዮች እንዳሉት የኤርትራ ሃይሎችና የትህግራይ ነጻ አውጪ ግንባር አንድ ክፍል የተገናኙት አብረው ሊሰሩ የሚችሉበትን መንገድ ለማፈላለግ ነው። ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አገዛዝ ግንኙነት እንደሌላቸው ተደርጎ ሽፋን የሚሰጣቸውና በውጭ አገር የሚኖሩ የሻዕቢያ ወገኖች የተገናኙት ከጀነራል ጻድቃንና አቶ ጌታቸው ጋር ግንኙነት ካላቸው የትህነግ ሃይሎች ጋር መሆኑን ለመረዳት ተችሏል።

እነዚህ አካላት በንግግራቸው ኢትዮጵያ አፋር ድረስ ዘልቀው በመያዝ፣ በሰሜን ወልቃይትና ጠገዴን በማካተት ፣ ትግራይን ከኤርትራ ደጋማ አካባቢዎች ጋር በመዋሃድ አንድ ታላቅ አገር ለመገንባት ቀደም ሲል የተያዘውን ዕቅድ ተግባራዊ የሚደረግበትን አግባብ ተነጋግረዋል። ይህ አሳብ በፍጥነት እንዲከናወን የታሰበው ኢትዮጵያ እየገነባች ያለው ሰራዊት በኤርትራ ላይ ከፈጠረው ስጋት አንጻር ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ አማራ ክልል ውስጥ እንዲነሳ የተደረገው ጦርነት በተፈለገው መንገድ ካልተጠናቀቀ ኢትዮጵያ አሰብን ለመውሰድ በገሃድ ዘመቻና እርምጃዎችን ልትወስድ እንደምትችል ግምት ውስጥ በማስገባት ነው።

“የአሰብን ወደብ ለኤርትራ ሰጥተን በሁዋላ ጊዜው ሲደረስ ከኤርትራ ላይ ለመውሰድ ይቀላል” በሚል አቶ መለስ በወሰኑት መሰረት የአሰብን ወደብ ያለ አግባብ የውሰደችው ኤርትራ፣ ከውስጥም ሆነ ከውጭ በአገዛዙ ላይ የሚነሳው ቅሬታ በመበርከቱ ኢትዮጵያ ሃይል እንኳን ብትጠቀም የሚመክት ሃይል እንደማይኖር መረጃውን የነገሩን አመልክተዋል። ስለሆነም ኢትዮጵያ ሰላም እንዳትሆን ከሚሰራው ስራ ጎን ለጎን “ነጻ ነን፤ ከፐሬዚዳንት ኢሳያስ ጋር ግንኙነት የለንም” የሚሉ ሃይሎችና ትህነግ ምክር መጀመራቸው ተመልክቷል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ኢትዮጵያና ኤርትራ ስምምነት ፈጥረው ድንበር ሲከፈት በሶስት ወራ ውስጥ ብቻ አምስት መቶ ሺህ የሚጠጉ የኤርትራ ተወላጆች ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን፣ በአሁኑ ሰዓት አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ የኤርትራ ተወላጆች አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል በሰላም እየኖሩ መሆኑንን የሚገልጹት የዜናው ባለቤቶች፣ የትግራይ ሃይሎች መከላከያን ተቀላቅለው ወደ ኤርትራ ካቀኑ የኢሳያስ አገዛዝ እድሜው የቀናት ስለሚሆን ቅድሚያ ምን ማድረግ እንዳለባቸው በማሰብ ይህን ግንኙነት እንደጀመሩ አመልክተዋል።

ትግራይ ክልል ገብተው የነበሩ የአማራ ግዛቶችን አስመልክቶ በውይይቱ ላይ ዝርዝር አቋም ባይያዛም፣ የትግራይ ሃይሎች ከኤርትራ ወገን የቀረበላቸውን የአብሮነት ቅድመ ሁኔታ ከተቀበሉ በኤርትራ በኩል አስፈላጊው ድጋፍ ሊደረግ እንደሚችል ቃል መገባቱ ታውቋል። ስማቸውን ሳይጠቅሱ መረጃውን ያቀበሉን ሚስጢር አዋቂዎች፣ አሁን ላይ ባለው ወደብ የማግኘት አቋም፣ ሻዕቢያ እያሰለጠነ በአማራ በኩል የሚልከው ሃይል ከኢትዮጵያ በኩል በፈጠረው ብስጭት ፣ በጦርነቱ ሳቢያ የያዘውን የኢትዮጵያን መሬት ሙሉ በሙሉ ለቆ እንዲወጣ መጠየቁ አንድ ላይ ተዳምሮ ሻዕቢያ “ሳልቀድም ልቅደም” በሚል ከትህነግ ፍላጎት ጋር ለመግባባት የማይችል ንግግር ተጀምሯል። ከኢርትራ በኩል ያሉት ክፍሎች የሻእቢያ የውጭ ክንፍ እንደሆኑ መረጃ እንዳለም አመልክተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የአሜሪካ የምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሀመር ከነሐሴ 13 ጀምሮ እስከ 19/2015 ድረስ ወደ አውሮፓ እንደሚያቀኑ፣ በጉዟቸውም ከአውሮፓ ሕብረ አገራት ጋር በኢትዮጵያ ወቅትዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚመክሩ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ይፋ አድርጓል።

ማይክ ሀመር በስዊድን ስቶኮልም እና በቤልጂየም ብራስልስ በሚኖራቸው ቆይታ፤ በአውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ እና ሱዳን ተዎካዮች ጋር ተገናኝተው እንደሚነጋገሩ መረጃው አመልክቷል። በስቶኮም ዓለም አቀፍ የውሃ ተቋም በተዘጋጀው የዓለም የውሃ ሳምንት መድረክ ላይ ሲሳተፉ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ እንደሚመክሩ በመረጃው ተጠቁሟል። የአባይ ጉዳይ አስመልክቶ ዝርዝር የተባለ ነገር የለም።

በቤልጂየም ብራስልስ በሚኖራቸዉ ቆይታ፤ ከአውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ ተዎካዮች ጋር ተገናኝተው ኅብረቱ እና አሜሪካ በኢትዮጵያ በአማራ እና በኦሮምያ ክልል የተፈጠረውን ቀውስ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በሚቻልበትና ሰላማዊ ሰዎችን በመጠበቅ ዙሪያ ይወያያሉ ተብሏል።

ከዚህም በተጨማሪ በተጨማሪም በፕሪቶሪያ የተፈረመዉ የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ በሚደረግበት ሁኔታ ከህብረቱ አገራት ጋር እንደሞነጋገሩ መረጃው አመልክቷል። ይሁን እንጂ ዝርዝር አጀንዳዎችን አልጠቀሰም። በተደጋጋሚ አሜሪካ የፕሪቶሪያው ስምምነት አፈጻጸም አስታካ የምታነሳው ሁሉም ነገር ከጦርነቱ በፊት ወደነበረበት የሚል እንደሆነ ይታወቃል። የትግራይ አዲሱ መሪ አቶ ጌታቸውም ይህንኑ በተደጋጋሚ ሲናገሩ ይሰማል። አሁን ላይ በአማራ ክልል የተነሳው ጦርነትና ” መከላከያ ከክልሉ ይውጣ” የሚለው መፈክር ” የያዝነውን እንዳያሳጣን” ሲሉ እርጋታ የጠየቁትን የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ንግግር የሚያስታውስ ሆኗል። ከዚህ ጎን ለጎን ፍትሕ እና ተጠያቂነትን በማስፈን ዙሪያም ከኢትዮጵያ አመራሮች ጋር እንደሚወያዩ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በመግለጫው ገልጿል። መንግስት የፍትህ ሚኒስቴር ያዘጋጀውን ሰነድ በማዘጋጀት ለተጠያቂነቱና ፍትህን የማስፈኑንን ስራ መጀመሩን ማስታወቁ አይዘነጋም።

አሜሪካ የአማራ ሃይሎች እያለች ከትግራይ ምዕራባዊ ግዛት እንዲወጡ በተደጋጋሚ ስትጠይቅ መቆየቷ ይታወሳል። አሁን ላይ ሃመር ከመንግስት ሃይሎች ጋር ይህንኑ አስመልክተው እንደሚወያዩ ከመገለጹ ውጪ ዝርዝር የተባለ ነገር የለም።

በሌላ ዜና የኢትዮጵያ ብሄራዊ የንግግር ኮሚሽንን ጨምሮ ለጊዜው ስማቸው ይፋ ያልሆኑ አካላት በአማራ ክልል የተነሳውን ጦርነት በሰላማዊ መንገድ ለመቋጨት እንዲቻል መንቀስቀሳቸው ሰሞኑንን ተሰምቷል። ከታጣቂዎቹም መካከል የተወሰኑት እርቅ አድርገው መግባት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል። የክልሉ መንግስትም ሆነ የፌደራሉ ይህ ነው ብለው በግልጽ ዝርዝር ጉዳይ ባያስቀምጡም ለሰላምና ድርድር በራቸው ክፍት መሆኑን ሲያስታውቁ ነበር። በመንግስትና መሳሪያ ባነገቡት ሃይሎች መካከል እርቅ እንዲወርድ ህዝብም ፍላጎቱ እንደሆነ በተደጋጋሚ ሲገልጽ ተሰምቷል።


Via addismaleda

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የሳዑዲ ድንበር ጠባቂዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን መግደላቸውን ሪፖርት ጠቆመ
የአክሲዮን ማኀበር እና የኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ልዩነት
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2