በክልሉ እየታየ ያለው የሰላም እጦት በኢንቨስትመንቱ ላይ ቀጥተኛ የኾነ ተጽእኖ እያሳደረ እንደኾነ ነው የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ የገለጸው፡፡
እየታየ ያለው አለመረጋጋት ወደ ክልሉ እየገባ ያለውን እና ለመግባት በሂደት ላይ የነበረውን ኢንቨስትመንት እንደሚያስቀር ተገልጿል። ይህ ደግሞ በክልሉ ምጣኔ ሃብት ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ነው ቢሮው ያስገነዘበው።
የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ኀላፊ ይሄነው ዓለም እንዳሉት ሰላም የሌለው ክልል አልሚዎችን ሊስብ አይችልም፡፡ አልሚዎች ለዳግም ኢንቨስትመንት በተለይም አዳዲስ ማሽኖችን ለማስገባት ያላቸውን ፍላጎት እንደሚቀንስም አብራርተዋል፡፡
ሰላም ከሌለ ኢንቨስትመንቱ አትራፊ ስለማይኾን አዳዲስ የሥራ እድል መፍጠር እንደሚሳነው እና ምርትም ማምረት እንደማይቻል አስገንዝበዋል፡፡
አሁን ላይ ያለው አለመረጋጋት የጥሬ እቃ ዝውውርን እየገታ በመኾኑ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ማምረት እንዳልተቻለ የሚናገሩት የሕዝብ ግንኙነት ኀላፊው ጉዳዩ የውጭ ምንዛሬን ለማግኘት አስቸጋሪ ነው ብለዋል፡፡
አቶ ይሄነው በሰላም መደፍረሱ ምክንያት ተጨማሪ ምርት አምርቶ በገበያው ላይ የሚታየውን የዋጋ መናር ለመቀነስ አስቸጋሪ እንዳደረገውም ነው ያስገነዘቡት፡፡
እየተፈጠረ ባለው ችግር ዋነኞቹ ተጠቂዎች ፋብሪካዎች ኾነዋል ፤ ይህም በፋብሪካዎቹ የሚሠሩ ሠራተኞችን ከሥራ እያፈናቀለ ስለመኾኑ ነው ያብራሩት፡፡ ባለፈው ጊዜ በተከሰተው አለመረጋጋት ብቻ ከ3 ሺህ በላይ የፋብሪካ ሠራተኞች ከሥራ ገበታቸው ስለመፈናቀላቸው ነው የገለጹት፡፡
በተለይም እስከ 8 የሚጠጉ የእርሻ ኢንቨስትመንቶች ላይ ጉዳት በመድረሱም ክልሉ እየተጎዳ ስለመኾኑ ነው ያስገነዘቡት፡፡
ከዘጠኝ በላይ በሚኾኑ የአበባ ልማት ዘርፎች ላይ ጉዳት በመድረሱ በዓመት ከ9 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መታጣቱንም አብራርተዋል፡፡
የክልሉን ኢኮኖሚውን ለማሳደግ በክልሉ ያለውን ችግር ለመቅረፍ እና አሁን የተጀመረውን አንጻራዊ ሰላም ለማስቀጠል የሁሉንም የክልሉን ሕዝብ ለሰላም መረባረብን ይጠይቃል። (አሚኮ)
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






