ጆንሰን በቴሌቪዥን ጣቢያው የፕሮግራም አቅራቢ፣ አዘጋጅና ተንታኝ ይሆናሉ። በቀጣይ ዓመት የአሜሪካና የዩኬ ምርጫ በመዘገብ “ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ” ተብሏል። “የእንግሊዝን ኃይል የሚያሳይ መሰናዶ” ያቀርባሉም ብሏል ጂኒ ኒውስ። በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዩች ምልከታቸውን ለማጋራት ቃል ገብተዋል።
በዴይሊ ሜይል ላይም አምደኛ የሆኑት ቦሪስ ጆንሰን ሥራቸውን በአውሮፓውያኑ አዲስ ዓመት ይጀምራሉ። ቦሪስ ጆንሰን በኤክስ ገጻቸው ላይ “ጂቢ ኒውስን እንደምቀላቀል ስነግራችሁ በደስታ ነው” ብለው ቪድዮ አጋርተዋል።
“በሩሲያ፣ ቻይና፣ ዩክሬንና ሌሎችም ጉዳዮች እውነተኛ ዕይታዬን አቀርባለሁ” ብለዋል። “እንግሊዝ በዓለም ስላላት ዕምቅ አቅምና ፈተናዎቻችንም እናገራለሁ” ሲሉ አክለዋል። ቦሪስ ከሥልጣን እንዲወርዱ ከፍተኛ ጫና መፈጠሩን ተከትሎ ነው አምና የወረዱት። በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት ያሳዩት አመራር አሁንም ምርመራ እየተደረገበት ነው።
በዩኬ የቀድሞ መሪዎች ሥልጣን በለቀቁ በሁለት ዓመታት ስለሚይዙት ሥራ የሚያማክሩት አገራዊ ኮሚቴ አለ። ይህ ኮሚቴ ቦሪስ ጆንሰን ጂቢ ኒውስ መግባታቸው ከመንግሥት መርህ ጋር የሚጻረር ስላልሆነ ፈቅዷል። ሥልጣን ላይ ሳሉ ያገኟቸውን መረጃዎች ያለአግባብ እንዳይጠቀሙ መርሆች ተቀምጠዋል። በተጨማሪም ጂቢ ኒውስን ወክለው መንግሥት ላይ ጫና እንዳያደርጉም ጥንቃቄ ይደረጋል።
ይህ የሚሆነው ሥልጣን ከለቀቁበት ጊዜ በኋላ ላሉት ሁለት ዓመታት ነው። ቦሪስ ከሥልጣን በለቀቁ በአምስት ወራት ውስጥ በተለያዩ መሰናዶዎች ንግግር በማድረግና የግል የሕይወት ታሪካቸውን ለመጻፍ በመስማማት አራት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ፓውንድ አግኝተዋል። ጂቢ ኒውስ ከዚህ በፊት ታዋቂው ኮሜድያን ጆን ክሊስን ቀጥሯል። ጣቢያው ቦሪስ ጆንሰንን ከቀጠረ በኋላ የተመልካቾቹ ቁጥር ከፍ እንደሚል ይጠበቃል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች







