Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የአየር ሃይል የኢትዮጵያን ታላቅነት በሚመጥን ደረጃ እየተገነባ ነው፤ በህር ሃይል በቅርቡ በአፍሪካ ቀዳሚ ይሆናል
News

የአየር ሃይል የኢትዮጵያን ታላቅነት በሚመጥን ደረጃ እየተገነባ ነው፤ በህር ሃይል በቅርቡ በአፍሪካ ቀዳሚ ይሆናል

Ethioreview newsEthioreview news—October 20, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በሁዋላ ዳግም ትንሳዔ የተነሳው የኢትዮጵያ አየር ሃይል የኢትዮጵያ በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን አስተማማኝና ዘመናዊ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በሻዕቢያና ትህነግ ስምምነት የፈረሰው ባህር ሃይልም ዳግም ተወልዶ ከአፍሪካ ግንባር ቀደም እንዲን ተደርጎ እየተገነባ መሆኑ ተመልክቷል። ዘመናዊ የጦር መርከቦችም ባለቤት ሆኗል።

ኢትዮጵያ በአየር ሃይል ታሪኳ ከአፍሪካ ቀዳሚና ዝናን ያተረፈ ሆኖ ሳለ ከ1983 በሁዋላ በሂደት ተመናምኖ ዳዋ በልቶት፣ ባለሙያዎቹም ተበትነው ነበር። ከአገር የወጡ በርክታ ባለሙያዎች እንደመሰከሩት በተቋሙ ላይ ታሪክ የማይረሳው ውድመት ተፈጽሞበታል። በህልውናው ጦርነት ወቅት አገራቸውን ለመታደግ ከውጭ የተመለሱ ኢትዮጵያዊ ባለሙያዎች እንዳሉት የኢትዮጵያ አየር ሃይል እንዲበተን ባይደረግ ኖሮ ዛሬ ላይ እጅግ ገናና ይሆን ነበር።

በቁጭት የቀደመውን ጥፋት ያወሱት ባለሙያዎች ከለውጡ በሁዋላ የተደረገውን ዝግጅትና ትኩረት እንዲሁም በአጭር ጊዜ ውስጥ የተሰራውን ሲመለከቱ መገረማቸውን በግልጽ ማስታወቃቸው አይዘነጋም። አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በሁዋላ በግንባር ቀደምትነት ትኩረት የሰጡት የኢትዮጵያ አየር ሃይል ዘመናዊ የጦር አውሮፕላንና የድሮን ባለቤት አድርገውታል። ሃላፊዎቹ እንዳስታወቁት በአዲስ ሪፎርም ተቋሙ አዋራ እየጠረገ ያነሳቸውን አውሮፕላኖች በማዘመን፣ አደርፈጃጀቱን በማሳደግና የሰው ሃይሉን በማብቃት ደረጃውን ከፍ አድርጓል። በተለይም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ አየር ኃይሉ በሁሉም ረገድ በመዘመንና ስኬታማ በመሆን ሀገር የምትኮራበት ታላቅ ተቋም መሆኑንም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ አየር ኃይል አሁን ላይ በውጊያ መሠረተ-ልማት፣ በሰው ኃይል ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራና አጠቃቀም በአጭር ጊዜ ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገቡን በተቋሙ የተለያዩ ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስተማማኝ የሀገር መከታ በመሆን ለየትኛውም ግዳጅ አፈጻጸም ብቁና ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ዘመናዊ ተቋም የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ሲሉ ለኢፕድ ባለሟዎቹ አረጋግጠዋል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

አየር ሃይል ዛሬ የውጊያ ሃይሉን ከማዝመኑና ዘመናዊ ትጥቅ ከመታጠቁ በተጨማሪ ራሱ የቴክኖሎጂ ፈጣሪ በመሆን አቅሙን ማሳደጉን ባለሙያዎቹ አመልክተዋል። አዛዡ ሌተናል ይልማ መርዳሳ ቀደም ሲል እንዳሉት የኢትዮጵያ አየር ሃይል ለኢትዮጵያዊያን ሁሉ አለኝታና ኩራት በሚሆንበት ደረጃ ዳግም እንዲደራጅ መደረጉ ለወገን ኩራት ሲሆን ለጠላት ስጋት እንዲሁን አስችሎታል።

ትናንት ኢዜአ ያነጋገራቸው ከፍተኛ መኮንኖች በአየር ኃይል አቪዬሽን ከባድ ጥገና ማዕከል የሮተሪ ዲፓርትመንት ዊንግ መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ኮሎኔል ኢንጂነር ሙሉቀን ደርሶ፤ አየር ኃይሉ የኢትዮጵያን ታላቅነት በሚመጥን መልኩ በሁሉም መስክ በዘመናዊ መልኩ እየተገነባ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በአየር ኃይሉ ለውጊያ፣ መለማመጃና ለትራንስፖርት አገልግሎት የሚውሉ አውሮፕላኖችን አስተማማኝ እድሳትና ጥገና በማድረግ ላይ ስለመሆኑም አንስተዋል። በአየር ኃይሉ ቀደም ሲል የነበሩ አውሮፕላኖችን ከአናሎግ ወደ ዲጂታል የማሻሻያ ሥራ በማከናወን የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ እየተደረገ መሆኑንም አብራርተዋል።

የአየር ኃይል የከባድ ጥገና ማዕከል የምርምር እና ልማት ክፍል ኃላፊ ሌተናል ኮሎኔል ወንድማገኝ አርዓያ፤ በቴክኖሎጂ አጠቃቀምና በማሻሻያ ሥራዎች ስኬታማ መሆኑን ገልፀዋል።

በከባድ የጥገና ማዕከል አውሮፕላኖችን የማዘመን፣ የዕይታና ዒላማ አቅማቸውን የማጎልበት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በዚህም አየር ኃይሉ ያወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት መቻሉን ገልጸው፤ በቀጣይም ተጨማሪ ገቢዎችን ለማስገኘት እንሰራለን ብለዋል፡፡

በአየር ኃይል የአቪዬሽን ጥገና ማዕከል መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ደረጄ አስታጥቄ፤ አየር ኃይል የውጊያ መሠረተ-ልማቶችን በመገንባት ያከናወናቸው ተግባራት ግዳጆችን በአስተማማኝ ብቃት መወጣት የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

በአየር ኃይሉ የትራንስፖርት ሄሊኮፕተር ጥገና ስኳድሮን ኃላፊ ሻለቃ አንድነት ብርሃኑ በበኩላቸው፤ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በአየር ኃይሉ በርካታ አመርቂ ሥራዎች ስለመከናወናቸው አብራርተዋል።

በአየር ኃይሉ የሄሊኮፕተር አብራሪዎቹ ሌተናል ኮሎኔል አየለ ዳዊት እና ሻለቃ ፀጋዬ አሰፋ ፤ አየር ኃይሉ አሁን ላይ በቴክኖሎጂ አጠቃቀምም ይሁን በግዳጅ አፈጻጸም አስተማማኝ ቁመና ላይ ይገኛል ብለዋል። በአስቸኳይ ተልዕኮና ግዳጅ በቀንም ይሁን በሌሊት በመብረር ያሰብነውን ማሳካት የሚያስችል ቁመና ላይ እንገኛለንም ነው ያሉት።

በተመሳሳይ ዜና “ባህር ሳይኖር ለመን ይቋቋማል” በሚል መንግስትን ሲተችበት የቆየው የኢትዮጵያ ባህር ሃይል ብቅርቡ በአፍሪካ ታላቅ ሊሆን በሚያስችል ደረጃ እየተደራጀና አቅሙን በውጭና አገር ውስጥ እያበቃ መሆኑ ተሰምቷል። በባህር ሃይል ቲክኖሎጂና አቅም ከፊት ደረጃ ከሚቅመጡት መካከል ፈረንሳይና ሩሲያ የተማሩትን ጨምሮ በአገር ውስጥ በዩኒቨርስቲ ደረጃ የሰው ሃይሉን እያበቃ እንደሆነ የተነገረለት የኢትዮጵያ ባህር ሃይል ዘመናዊ የጦር መርከብ ባለቤት መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ይናገራሉ።

አሁን ላይ መንግስት የባህር በርን አስፈላጊነት በይፋ ሲያውጅ “ዝግጅት እንዴት ይጠላል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ከዚህ ቀደም ሲሰነዘር ለነበረው ትችት ምላሽ ሰጥተዋል። በክህደት ተመቶ ዳግም እንዲፈርስ ሙከራ የተደረበትና በደምና አጥንቱ አገግሞ ዛሬ ግዙፍ ጦር የሆነው የአገር መከላከያ ሰራዊት በሃይል ከአየር ሃይልና ባህር ሃይሉ ጭምር ታላቅ እንደሆነ በውጭ ሃይሎች እየተመሰከረለት ነው።

“ከ፴ ዓመት ውርደት በኋላ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል የውሃ አካል ላይ ግዳጅ ለመወጣት ዝግጁ ነው” ተብሎ የተነገረለት የኢትዮጵያ ባህር ሃይል ባህርተኞችን በቅርቡ ሲያስመርቅ ” ሠራዊታችን እንደጠላት ፍላጎት ቢሆን ኖሮ ሀገራችን እና የህዝባችን ደህንነት አደጋ ላይ ይወደቅ ነበር ። ሠራዊታችን አላፊ አግዳሚ ሽፍታ የሚደመስሰው ሳይሆን በፕሮፌሽን የተገነባ የሀገራችን አለኝታ ሠራዊት ነው” ሲሉ ኢታማዦር ሹሙ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ መናገራቸው ይታወሳል።

ሰሞኑን ኢትዮጵያ የባህር በር በቀይ ባህር ላይ እንደምትሻ፣ ይህም ፍላጎት የህልውና እንደሆነ ማስታወቋን ተከትሎ አማራጭ የባህር በር ዜናዎች በይሁንታና አሉታዊ ጎኑ እየተሰማ ነው። ኢትዮጵያ ፋልጎቷን መግለጿን ተከትሎ ኤርትራ “በዚህ ጉዳይ መስሚያዬ ጥጥ ነው” ስትል ጁቡቲም ” በወደብ ኪራይ እያለብኳችሁ እኖራለሁ” በሚል ተመሳሳይ አሉታዊ ዜና አሰምታለች። ሶማሌም እንደዛው።

ከታማኝ ምንጮች እንደሚሰማው ከሆነ ኢትዮጵያ የባህር በር ባልቤት የመሆኗ ጉዳይ አልቆለታል። ኢትዮጵያ በቀጥታ ጥይቄ ሳታቀርብላቸው ምላሽ የሚሰጡት አገሮች ምን አልባትም ከጥቅምና ዋጋ ቢስ እንሆናለን ከሚል ስጋት የተነሳ እንደሆነ እየተገለጸ ነው። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አሕመድ በቻይና ታላቁን ወደብ ሰፊ ጊዜ ወስደው መጎብኘታቸውና የባህር ሃይል ድምጹን አጥፍቶ ባለሙያዎችና ትጥቅ ማዘጋጀቱ የአንድ ማለዳ ሰበር ዜና ሊሆን እንደሚችል ምልክት መሆኑንን እነዚሁ ክፍሎች ይናገራሉ።


  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
    ቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በሰሜን ሸዋ ከፍተኛ ገንዘብ ከፍለው ከእገታ የተለቀቁት አባት የቀናት ሰቆቃና ምስክርነት፤ “ነጻ ልናውጣችሁ ነው” አጋቾች
Call for consolidated efforts to ensure media literacy, peace building
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2