ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይፋ መሆን የጀመሩ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች ” እውን እስካሁን የት ነበርን” የሚያሰኝ እንደሆነ በየአቅጣጫው ቀና ልቡና ካላቸው ወገኖች የሚሰማ ድምጽ ነው። ሰላም ቢሰፍንና አገሪቱ ከሴራ ፖለቲካ ብትፈወስ ምን ሊታይ እንደሚችልም ምኞታቸውን የሚገልጹ ጥቂት አይደሉም። ” ምን ዋጋ አለው?” በሚል የሚያጣጥሉም አሉ።

መልካም ጉዳይን አበረታቶ የጎደለውን በመጠቆም፣ ክፉውን ተግባር የሚተች የተቃውሞ አውድ ወይም የተቃዋሚ ድርጅት ባለመኖሩ፣ በአብዛኛው ሚዲያዎችም ከሟርትና ከአስደንጋጭ ዜና አዙሪት ለመላቀቅ አለመፈለጋቸው፣ ቢፈልጉም ላይክና ሼር ስለሚጉዝደል ጉሮሮ ስለሚዘጋ፣ አብዛናው የማህበራዊ ሚዲያም ተሰበረ፣ ወደመ፣ ተደመሰሰ፣ ፈረሰ፣ ተገደለ፣ ተማረከ ወዘተ ከሚሉ ዜናዎች ውጭ ስሜት ስለማይሰጠው በኤትዮጵያ ነገሮች ሁሉ ግራ የሚያጋቡ እንደሆኑ በዚሁ ችግር ዙሪያ ጥናት ያካሄዱ፣ የታዘቡ ይገልጻሉ።

በተለያ በአብዛኛው ሊባል በሚችል ደረጃ የሚዲያ ዘርፉ ቁልቁል ሄዶ መከስከሱ፣ የፖለቲካ አጀንዳ አራጋቢ መሆኑና በተወሰኑ ሃይሎች የሚደጎም መሆኑ የኢትዮጵያን ፖለቲካ አታካች አድርጎታል። ዓላማው ህዝብ እንዲሰላችና ዘወትር ምሬት ውስጥ እንዲወድቅ በመሆኑ፣ ከመንግስት ድክመት ጋር ተዳምሮ ኢትዮጵያን እጅግ እየጎዳት ነው።
“የአባይ ግድብ ተሸጠ” በሚል “የውስጥ አዋቂዎች ነገሩኝ” የሚል ተከፋይ ሚዲያ፣ ግድቡ እንደተባለው አለመሸጡ፣ ይልቁንም ተጠናቆ ሙሉ በሙሉ ኤለኤክትሪክ ለማምረት ከጫፍ መድረሱ በውል እየታየ ይቅርታ አይጠይቅም። ይህንኑ ልዩ ተልዕኮ ያለው ዜና በጅምላ ያሰራጩ በተመሳሳይ እርምት አይወስዱም። ከሁሉም በላይ ትልልቅ የሚባሉትን ጨምሮ ተከፋዮቹ ሚዲያዎች ሆን ብለው በተደጋጋሚ ስህተት ሲያትሙና ሲያሰራጩ በውል እየታየ አንባቢ፣ ተከታይ፣ አከፋፋይ “ውሸታም” ብሎ ሲቃወምና ጥንቃቄ ሲወስድ አይታይም። የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክን ጭምሮ የጫካ ፕሮጀክትና መላው የገበታ ለአገር ፕሮጀክቶች ላይ የተረጨው የሃሰት ፕሮፓጋንዳ እንደሚለው ሳይሆን ውጤቱ ሌላ ነው።
የውድቀትና የክስረት ዜና ሲረጭበት የነበረው የጨበራ ጩርጩራ ፕሮጀክት ይህን ይመስላል
የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በኮንታና በዳውሮ ዞኖች መካከል የሚገኝ ሲሆን ካለው ዕምቅ ከተፈጥሮ ሀብት አንፃር በቀዳሚነት ስሙ ይነሳል፡፡
ብሔራዊ ፓርኩ በ1997 ዓ.ም በኮንታና በዳውሮ ህዝቦችና አስተዳደር አካላት ጥያቄና ተሳትፎ መሰረት በብሔራዊ ፓርክ ደረጃ የተቋቋመ ሲሆን ፓርኩ የሚያካልለው የቆዳ ስፋት 1410 ካሬ ኪሎ ሜትር ስኩዌር ሲሆን በመካከለኛው ኦሞ ሸለቆ ውስጥም ይገኛል፡፡
ብሔራዊ ፓርኩ ከመዲናችን አዲስ አበባ በ475 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።
ፓርኩ የግዙፉ የአፍሪካ ዝሆን መኖሪያ ሲሆን በውስጡ ከ800 በላይ የሚሆኑ ዝሆኖችና ከ 5 ሺሕ በላይ ጎሾች የሚገኙበት መሆኑ ፓርኩን ልዩ ያደርገዋል፡፡

በተጨማሪም 40 ትላልቅና መካከለኛ አጥቢ እንዲሁም 18 ትናንሽ አጥቢ የዱር እንስሳት ዝሪያዎች በውስጡ ይገኛሉ።
በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ እንደ አጥቢዎቹ ሁሉ የበርካታ አዕዋፋት ዝርያዎች መኖሪያም ጭምር ነው፡፡ እስካሁን በተጠናው ጥናት 137 የአዕዋፍ ዝርያዎች የተለዩ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 6ቱ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ናቸው፡፡
ፓርኩ በብዙ መልኩ የተፈጥሮ ሀብቱ የተጠበቀ ፓርክ ነው ያስባለው የእጽዋት ስብጥሩ እና ደኑ ነው። 106 እንጨታማ የእጽዋት ዝሪያዎች የሚገኝበት ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ስድስቱ የእጽዋት ዝርያዎች በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ናቸው፤ በተጨማሪም በውስጡ ከሚገኙ የዱር ዕፅዋት ዝሪያዎች መካከል ዝንጅብል፣ ቡና፣ ኮረሪማ፣ እንሰት፣ እጣንና የጌሾ ዝርያዎች ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
በፓርኩ ውስጥ ብቻ 6 ሀይቆች የሚገኙ ሲሆን ባሄ፣ ቡሎ፣ ሺታ፣ ቆቃ፣ ከሪቤላና ጮፎሬ እጅግ አስደናቂና ሊጎበኙ የሚገቡ በብሔራዊ ፓርክ ውስጥ የሚገኙ ሐይቆች ናቸው፡፡
በብሔራዊ ፓርክ ውስጥ ከሚገኙ ሐይቆች በአንዱ ብርቅዬ ወርቃማ የዓሳ ዝርያ የተገኘ ሲሆን በዓለም ሊቃውንት እውቅና አግኝቶ በሳይንሳዊ ስሙ ጋራ ጨበራ በመባልም ይጠራል፡፡
ሌላኛው ከብሔራዊ ፓርኩ ገፀበረከቶች መካከል ለአብነት ፏፏቴዎች፣ ፍልውሃዎችና የማዕድን ውሃዎች የሚጠቀሱ ናቸው።
ብሔራዊ ፓርኩ በአሁኑ ሰዓት በገበታ ለሀገር ኮይሻ ፕሮጀክት እየለማ የሚገኝ ሲሆን ቱሪስቶች ብዙም ሳይጉላሉና ሳይለፉ በቀላሉ ጎብኝተው እንድመለሱ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠሩም ባለፈ ፓርኩን በተገቢው ሁኔታ ለማስተዳደርና የዱር እንስሳትን በቅርበት ለመከታተልና ለመጠበቅ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡
ይህ ብሔራዊ ፓርክ በኮንታ እና በዳውሮ ህዝብ ፊላጎት እንደተቋቋመ ሁሉ በጥበቃ ሂደት ላይም ህዝቡ ከፍተኛ ዋጋ በመክፈል ብሔራዊ ፓርኩን ከተለያዩ ጥፋቶች በመታደግ መልካም ዝና እንድኖረው አድርገውታል።
ምንጭ ፦ የክልሉ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
- አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱበዙፋን ኡርጋ ደራሲነት የተጻፈውን ሌንጮ ለታ ትግል ሕይወቱ መጽሐፍን አነበብኩት። መጽሐፉ በ471 ገጾች እና በሦስት ክፍሎች ተቀንብቧል። የመጀመሪያው ክፍል ከልጅነት እስከ… Read more: አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው







