Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  የሃይማኖት ተቋማት የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርት እንዲያቀርቡ የሚያስገድድ አዋጅ ተዘጋጀ
lawNewsTIPS 1

የሃይማኖት ተቋማት የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርት እንዲያቀርቡ የሚያስገድድ አዋጅ ተዘጋጀ

የሰላም ሚኒስቴር የደረሰውን የኦዲት ሪፖርት አመቺ በሆነ መንገድ ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል

Ethioreview newsEthioreview news—May 23, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በከፍተኛ የፋይናንስ ብክነትና ህግ ያልተከተለ አሰራር ለከፍተኛ የሃብት ዘረፋ መጋለጣቸው በተደጋጋሚ የሚነሳባቸውን የሃይማኖት ተቋማት የፋይናንስ አሰራር ደንብ እንዲሁም የኦዲት ሪፖርታቸውን እንዲያቀርቡ የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገለጸ። ሪፖርቱ እንደ አስፈላጊነቱ ለህዝብ በአመቺ መንገድ ይገለጻል። ረቂቅ አዋጁ ከመጽደቁ በፊት በስፋት ውይይትና ምክክር የሚደረግበት መሆኑም ተሰምቷል።

“የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ” በሚል ስያሜ የሚጠራው ረቂቅ ህግ በግርድፍ ያወጣው ሪፖርተር ጋዜጣ እንዳለው ረቂቁ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርቱን ለሰላም ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚኖርበት፣ ከውጭ አገር የሚመጣ የገንዘብ ዕርዳታ በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት ይደነግጋል።

የሃይማኖት ተቋማቱ ተቀባይነት ያለው የሒሳብ አያያዝና የኦዲት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚኖርባቸው፣ የኦዲት ሪፖርታቸውንም ለሰላም ሚኒስቴር ማቀረብ እንዳለባቸው በረቂቅ አዋጁ ተካቷል።

የሃይማኖት ተቋማቱ የሚጠቀሙት የሒሳብ አያያዝ ሥርዓት የገቢ፣ የወጪና አጠቃላይ የንብረት ዝርዝር የያዘ መሆን እንደሚኖርበትና የገቢ አሰባሰብና የወጪ አስተዳደር በሕጋዊ መንገድ ማከናወን እንዳለባቸው ያስረዳል፡፡ አንድ የሃይማኖት ተቋም በራሱ የገቢ ማስገኛ ሥራዎችን በሚያከናውንበት ጊዜ፣ ለዚሁ ሥራ የተለየ የባንክ ሒሳብ መክፈትና የተለየ መዝገብ መያዝ እንዳለበት ደንግጓል፡፡

More stories

ለሸኔ የሽብር ቡድን ሊላክ የነበረ የጦር መሳሪያ ተያዘ

August 21, 2021

የስንዴ አብዮት!! ኦባሳንጆ [ ኢትዮጵያ ልማት ላይ ነች] ሲሉ መመስከራቸው ብስጭት ፈጠረ

June 2, 2022

“የባንክ ሥራ ረቂቅ አዋጁ የውጭ ባንኮች በፋይናንስ ዘርፉ እንዲሠማሩ የወጣውን ፖሊሲ ወደ ተግባር የሚያሸጋግር ነው”

November 13, 2024

In Ethiopia, the Tigray People’s Liberation Front is using child soldiers as human shields

September 10, 2021

በተጨማሪም ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ አገር የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት አስቀምጧል፡፡ ሲያሳውቅም የለጋሹን ድርጅት ወይም ግለሰብ ስምና አድራሻ፣ የተለገሰው የገንዘብ፣ ስጦታ ዓይነትና መጠን፣ እንዲሁም ስጦታው ወይም ድጋፉ የተሰጠበት ልዩ ዓላማ መካተት እንዳለበት ተገልጿል፡፡

ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የበጀት ዓመቱ በተጠናቀቀ በሦስት ወራት ውስጥ የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በገለልተኛ ኦዲተር ማስመርመር እንዳለበትና የኦዲተሩን አቋምና የውሳኔ ሐሳብ መያዝ እንዳለበት በረቂቁ ተመላክቷል፡፡ የሰላም ሚኒስቴር የደረሰውን የኦዲት ሪፖርት አመቺ በሆነ መንገድ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ እንዳለበትም ተደንግጓል፡፡ 

የአምልኮ ወይም የመቃብር ቦታ አሰጣጥን በተመለከተም ለሃይማኖት ተቋማቱ የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት እንደሚወሰን ተገልጿል፡፡ ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ ዓላማ የተሰጠ ቦታ አለመኖሩ ወይም ተጨማሪ ቦታ መስጠት አስፈላጊ መሆኑ መረጋገጥ እንዳለበት፣ እንዲሁም በተለያዩ ቤተ እምነቶች መካከል የሚኖረው ርቀት ቢያንስ 500 ሜትር መሆን እንዳለበት ተደንግጓል፡፡

ትምህርትና የሃይማኖት ተግባራትን በሚመለከትም በረቂቁ ላይ ዝርዝር ጉዳዮች ተቀምጠዋል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ መደበኛ ትምህርት በሚሰጡ የመንግሥት ወይም የግል ተቋማት የሚሰጠው ትምህርት ሃይማኖታዊ ይዘት የሌለው መሆን እንደሚኖርበት ተመልክቷል፤ በእነዚሁ የመንግስትና የሃይማኖት ተቋማት ንብረት ባልሆኑ የግል የትምህርት ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ ሃይማኖታዊ ትምህርትን ማስተማር ወይም በቡድን ማምለክ የተከለከለ ነው የሚል አሳብም አለበት።

በተጨማሪም ማንነትን ለመለየት የሚያስችሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን ጥቅም ላይ ሊውሉ እንደማይገባ ተደንግጓል፡፡ ይህን የረቂቁን ክፍል አስመልክቶ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሃይማኖታዊ ምልክቶችን እንደ ቤተ እምነቱ አስገዳጅ ሕግጋቶች ልዩ ሁኔታዎች እንደሚኖሩ መደንገግ ሲገባው፣ ሙሉ ለሙሉ ከትምህርትና ሥራ ገበታ የሚያስገድዱ ድንጋጌዎችን መያዙ አግባብ አለመሆኑን በመግለጽ ለሰላም ሚኒስቴር በላከው አስተያየት፣ ቅሬታና የመፍትሔ ሐሳብ መግለጹ ይታወሳል፡፡

በሌላ በኩል የመንግሥት ኃላፊዎች መንግሥትን ወክለው በሃይማኖት በዓላት አከባበር ላይ መገኘት እንደማይችሉ በረቂቁ ተመልክቷል፡፡ በተጨማሪም በትምህርት ቤት፣ በመኖሪያ ቤትና በሕክምና ማዕከላት አካባቢ የሚደረግ አምልኮ በአካባቢ ጥበቃ ሕግ የተቀመጠውን የድምፅ መጠን ያከበረ መሆን እንደሚኖርበት፣ ካልተፈቀደ በስተቀር ማስተማርን ጨምሮ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎች መፈጸም እንደማይችል ረቂቁ ይደነግጋል፡፡

የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በበኩሉ ይህ የረቂቅ አዋጁ ክፍል በልዩ ሁኔታ በወንጌል አማኞች ላይ ጫና የሚፈጥርና ሕገ መንግሥታዊ መሠረት የሌለው መሆኑን በመግለጽ፣ ሊስተካከል ይገባል በማለት ለሚኒስቴሩ በላከው ደብዳቤ ማስታወቁን ሪፖርተር አስታውሷል።

ዜናው በሃይማኖት ተቋማት ዙሪያ ጫጫታ መፍጠሩ እያተሰማ ነው። በአብዛኛው የእምነት ተቋማት የሚሰማው ግጭትና አለመግባባት የዚሁ የሃብት ቅርምት ጉዳይ እንደሆነ ከራሳቸው መሰማቱ አይዘነጋም። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይም ይህን ሲሰሙ በነበረበት ውይይት ላይ ህግ እንደሚዘጋጅና የሚመለከታቸው መክረውበት እንደሚጸድቅ መናገራቸው አይዘነጋም።

ኢህአዴግ በግምት ከዛሬ አስራ አምስት በፊት አገልጋዮች ላይ ያተኮረ የሃብት ምርመራ አካሂዶ በሚታወቁ ፓስተሮች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ አስተዳዳሪዎችና ወዘተ ስም በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እንዳከማቹ አረጋግጦ ነበር። በሃይማኖት ተቋማት የሚካሄደው ህግን ያልጠከተለ የፋይናንስ አካሄድ ለዝረፋ አመቺ በመሆኑ አዋጁ ከፍተኛ ተግዳሮት ሊገጥመው አንደሚችል ይገመታል።

አስተያየት የሚሰጡ እንደሚሉት እነዚህ አካላት ሃብት ስላላቸው የአዋጁን አቅጣጫና አላማ በማጣመም ምዕመኑን ለማነሳሳት ሊጠቀሙበት ስለሚችሉ፣ በግርድፍ የሚወጡ መረጃዎችን ፍትህ ሚኒስቴር በሚቻለው የሚዲያ አውድ ሁሉ ለህዝብ በመደጋገም ሊያሳውቅ ይገባል ብለዋል። አያይዘውም ከሃይምኖት ተቋማቱ ጋር የሚደረገው ውይይት ህዝብ እንዲሰማው ክፍት ሊሆን እንደሚገባው አሳስበዋል።

lawNEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽን ግብይት ሳይኖር ደረሰኝ ሲሸጡ የነበሩ በቁጥጥር ስር ዋሉ
መቐለ- የወርቅ መስቀሎችን የሰረቁ  ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2