Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  TIPS 1  በገለልተኝነት የሚታሙት የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ ተሸኙ፤
TIPS 1

በገለልተኝነት የሚታሙት የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ ተሸኙ፤

Ethioreview newsEthioreview news—July 5, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በገልተኛነትና የሌሎች ሃይሎችን ዓላማ ያራምዳሉ በሚል ይከሰሳሉ። በዚህ ጉዳይ በተደጋጋሚ ሲጠየቁ ክሱን ውድቅ የሚያደርጉት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) ዛሬ ተሸኝተዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሠ ጫፎ አሸኛኘት እንዳደረጉላቸው ተመልክቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በትናንትናው የፓርላማ ውሏቸው ” የሰብዓዊ መብት አዋጅ ፣ ተቋም፣ አሰራር ይፈተሽ ” በሚል ተናግረው ነበር።

ዳንኤል በቀለ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሆነው ሰኔ 25 ቀን 2011 ዓ.ም መሾማቸው ይታወሳል፡፡ ተቋሙ ከለወጡ በሁዋላ ከተገነቡት ሁሉ እጅግ አስፈላጊና ከመንግስት ተጽዕኖ ገለልተኛ እንደሆነ ራሳቸው ኮሚሽነሩ ምስክር ሰጥተዋል። ይሁንና የስራ ጊዜያቸው ሊጠናቀቅ ሁለትና ሶሶት ወራት ሲቀራቸው ማስፈራራትና ዛቻ በተቋሙ ሰራተኞችና አመራሮች ላይ እንደሚደረግ ተመልክቷል። ይህንኑ ዜናም ዓለም ዓቀፍ ተቋማትና የዜና አውታሮች በስፋት ሲያስተጋቡት ነበር።

ይህ በንዲህ እንዳለ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ” ሰብዓዊ መብት ደስ የሚል ቋንቋ ነው፣ ለሰዎች የሚደረግ መብት በግርድፉ ሲታይ ደስ የሚል ቋንቋ ነው ግን ይሄ ቋንቋ ከዋናው የትርጉም ግንዱ ወጥቶ የፖለቲካ መጠቀሚያ እየሆነ ነው ” ሲሉ ትናንት በፓርላማ ውሏቸው ተናግረዋል። በርካታ የአድፍሪካ አገራትም የሚታመሱት በዚህ (ሰብዓዊ መብት) ታርጋ እንደሆነ አመልክተዋል።

ስለ እሰረታዊ የሰብዓዊ ልጆች መብት አንስተው ለዚሁ የሰው ልጆች መብት ማሰብ ጠቃሚና ቀዳሚ መሆኑንን ተናግረዋል። የሰውን ልጆችን ማክበር ፣ የተሻለ ቤት፣ ጥሩ መማሪያ እንዲኖራቸው፣ እንዲመገቡ ማስቻል ዋናና ቀዳሚው የሰው ልጆች መብት መሆኑንን ያመልከቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ስለ ሰው ልጆች በልቶ ማደር ስለ መኖሪያ ቤታቸው ሳይጨነቁ በሚዲያና በዩትዩብ በመናገር ብቻ የሰው ልጆች መብት ተቆርቋሪ እንደማያሰኝ ገልጸዋል።

More stories

ዘመነ ካሤ ቀድሞ ወደ ድርድር ?  ሰባት የፋኖ ቡድኖች ያሉበት ስብሰባ ቃለ ጉባኤ

July 22, 2024

በኦሮሚያ የሰላም ውይይት ፍንጭ ተሰማ፤ “ጃል መሮ እጅ ካልሰጡ ከጃል ሰኚና ከመንግስት አያመልጡም”

October 11, 2024

ኢምሬት ከፈረንሳይ ጋር ያሰረችውን የ 20 ቢሊዮን ጦር መሳሪያ ግዢ አቋረጠች

August 31, 2024

ኢትዮጵያ እንዲህ ተዘርፋለች፤ ” አሁንም ሌቦች አሉ የመንግስት ሌብነት ማለት ግን ይህ ነው”

July 7, 2024

“የሰብዓዊ መብት አዋጅ፣ ተቋምና አሰራር መፈተሽ ያስፈልጋል ” ሲሉ ለተከበረው ምክር ቤት አሳባቸውን ያጋሩት አብይ አሕመድ፣ ” እኛ ደመወዝ የምንከፍለው፣ ሌሎች ኃይሎች የቀጠሩት፣ ለሌሎች ኃይሎች ሪፖርት የሚያደርግ ተቋም ኢትዮጵያ ውስጥ ከፈቀድን ምን ሊፈጠር እንደሚችል ለእናንተው መተው ነው ” ሲሉም አስጠንቅቀዋል።

“እኔ የሰብዓዊ መብት የሚባሉ ሃሳቦችና ተቋማት በየትም ቦታ ያሉ የማያቸው ልክ እንደመርፌ ነው ፤ መርፌ የራሱን ቀዳዳ መስፋት አይችልም። እነሱም የራሳቸውን ድክመት ማየት አይችሉም። ይሄ ጥሩ አይደለም ሀገር ያፈርሳል ጥቅም የለውም፤ ተቋሞቻችንን ጸዳ ማድረግ አለብን ” ሲሉ አፈርጥመው ተናግረዋል።

ሁለት ነገሮች ሊሰመርባቸው እንደሚገባ ያስታወቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰብአዊ መበት ተሟጋች ድርጅቶች ላይ መንግስት ጫና ማድረግ እንደሌለበት፣ ይህም አግባብ እንዳልሆነ ጠቅሰው በተቃራኒው ደግሞ ተቋማቱ የሌሎች አገራትና ሃይሎች መጠቀሚያ እንዲሆኑ መፈቀድ እንደሌለበት ተናግረዋል። “የሰብዓዊ መብት ተቋማት ከኢትዮጵያ መንግሥት እና ከሌላ ሀገራትና ፍላጎቶች ነጻ መሆን አለባቸው” በማለት አሳስበዋል።

“አሁን ላይ ያሉት ግን” አሉ አብይ አህመድ ” አሁን ያሉት ግን ከኢትዮጵያ መንግሥት ነጻ ቢሆኑም ከሌሎች ኃይሎች ነጻ አይደሉም” ሲሉ የተጠራቀመውን የመንግስትን ብሶት ይፋ አድርገዋል። ከዚህ ቀደም ፊልድ ማርሻል ብረሃኑ ጁላ በተመሳሳይ ተቋሙ ፍጹም ገለልተኛ እንዳልሆነ አምለክተው ነበር።

ዶ/ር ዳንዔል የሚመሩት ኢሰመኮ በአማራና አፋር ክልል ወረራ በተፈጸመት ወቅት፣ በማይካድራ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ በገሃድ ያላጋለጡ እንዲያውም፣ ለመሸፋፈን የሚከረ ሪፖርት በማቅረባቸው የተነሳ የተቋሙ ታማኝነት ማክተሙን በወቅቱ በርካታ ዜጎች አደባባይ ወጥተው ሲናገሩ እንደነበር ይታወሳል።

ብዙ ዝርዝር ጉዳዮችን ያላነሱት አብይ አህመድ የተቋሙን ችግር በድፈናው ሲገልጹ፣ በሀገሪቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የለም ማለት እንዳለሆነ ግልጽ አድርገዋል። በመብት ጥሰት ጉዳይ ስህተቶችን መገምገም ኃላፊነትም መውሰድ እንደሚገባ አልሸሸጉም።

መከላከያ እና ፌዴራል ፖሊስ ጥፋት የፈጸሙ አባሎቻቸው ላይ እርምጃ መውሰዳቸውን ጠቅሰው ካመሰገኑ በሁዋላ “የሀገር መከላከያ በወታደራዊ ፍርድ ቤት በሺዎች የሚቆጠሩ አባላቱን ከ code of conduct ውጭ ኦፕሬሽን ሰርተዋል በሚል ምክንያት እስር ቤት ከቷል” ብለዋል።

የአብን አባሉ አቶ አበባው ደሳለው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ባቀረቡት ጥያቄ ባለፉት 10 ወራት በአስቸኳይ አዋጅ ሰበብ በአማራ ክልል ፦የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ሰፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደፈጸሙ፤ በበርካታ የአማራ ከተሞች ያልታጠቁ ሰላማዊ ሰዎች በጅምላ እንደተገደሉ (ለምሳሌ ፦ በመርዓዊ ፣ በጅጋ ፣ በደብረ ኤልያስ ፣ በፍትኖተ ሰላም፣ ደብረሲና አካባቢ ፣ ጎንደር እና ወሎ) የጅምላ እስር አማራን መሰረት አድርጎ እንደሚፈጸም የምክር ቤት አባላት ሳይቀር በፖለቲካዊ አመለካከታቸው እስር ቤት እየማቀቁ እንዳለ ይህንን ጉዳይም የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማት መዘገባቸውን አንስተው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄ አቅርበው ነበር።

—–

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በአርባ ምንጭ ግዙፍና ዘመናዊ የህክምና ቴክኖሎጂ የተሟላላት ሆስፒታል ተገነባ
Ethiopian Rights Commission Chief “completes tenure”
Related posts
  • Related posts
  • More from author
TIPS 1

WFP Country Director Says Ethiopia Registered Significant Economic Transformation by Focusing on Rural Dev’t, Poverty Reduction

July 28, 2025
TIPS 1

Almost a third of people in Gaza not eating for days, UN food programme warns

July 26, 2025
TIPS 1

Israeli spy chief visits US amid bid to move Palestinians out of Gaza – Axios

July 20, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2