Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  TIPS 1  በኦሮሚያ የሰላም ውይይት ፍንጭ ተሰማ፤ “ጃል መሮ እጅ ካልሰጡ ከጃል ሰኚና ከመንግስት አያመልጡም”
TIPS 1

በኦሮሚያ የሰላም ውይይት ፍንጭ ተሰማ፤ “ጃል መሮ እጅ ካልሰጡ ከጃል ሰኚና ከመንግስት አያመልጡም”

Ethioreview newsEthioreview news—October 11, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በኦሮሚያ ሁለት አብይት ዜናዎች ውስጥ ውስጡን እየጦዙ ነው። አንደኛው በኦሮሚያ ክልል የሰላም ስምምነት ውይይት መጀመሩ ሲሆን ሁለተኛው የተከፈለው የኦሮሞ ነጻ አውጪ ጦር አንዱ ሌላውን ለጠቀላይ የመግጠሙ ጉዳይ ነው። በዚህ መካከል አቶ ሽመልስ የሰላም ንግግር ስለመኖሩ ፍንጭ መስጠታቸው የጠቅላዩን ጨዋታ መቃረብ የሚያሳይ እንደሆነ ተደርጎ እየተወሰደ ነው።

የማዕከላዊ ዞን የቀድሞ አዛዥና የድርጅቱ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ጃል ሰኚ ነጋሳን በግልጽ ጃል መሮን ጠቅሰው ድርጅቱ ህግ፣ ድንብና ተጠያቂነት የሌለው መሆኑን አስታውቀው መለያታቸውን በገሃድ ሲያስታውቁ ለሰላም ውይይት ዝግጁ መሆናቸውን ጠቅሰው ጥሪ አቅርበው እንደነበር ይታወሳል።

ራሱን የኦሮሞ ነጻ አውጪ ሰራዊት በሚል ስያሜ የሚጠራውና ጠብ መንጃ አንስቶ ጫካ የገባው ይህ አማጺ ኃይል በይፋ ባይወጣም በውስጡ የመከፍል ችግር እንዳለበት በተደጋጋሚ መረጃ ሲወጣ ነበር። መረጃውን ራሳቸው ነበር የሚያሰራጩት።

የሁለቱም ወገኖች አመራሮች በስልክ ያካሄዷቸውን መልዕክቶች ጨምሮ በጠብመንጃ ገጥመው መገዳደላቸው ሲዘገብ ነበር። በርካታ በውጭና በውስጥ ያሉ ደጋፊዊቻቸው ሳይቀር በሰሙት ዜና ተሰላችተው እየተለዩዋቸው፣ ጀርባቸውን እየሰጧቸው መሆኑ ለኦሮሚያ ብልጽግና መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ተደርጎም አስተያየት ሲሰጥ ከርሟል።

More stories

ዘመነ ካሤ ቀድሞ ወደ ድርድር ?  ሰባት የፋኖ ቡድኖች ያሉበት ስብሰባ ቃለ ጉባኤ

July 22, 2024

በኦሮሚያ የሰላም ውይይት ፍንጭ ተሰማ፤ “ጃል መሮ እጅ ካልሰጡ ከጃል ሰኚና ከመንግስት አያመልጡም”

October 11, 2024

ኢምሬት ከፈረንሳይ ጋር ያሰረችውን የ 20 ቢሊዮን ጦር መሳሪያ ግዢ አቋረጠች

August 31, 2024

ኢትዮጵያ እንዲህ ተዘርፋለች፤ ” አሁንም ሌቦች አሉ የመንግስት ሌብነት ማለት ግን ይህ ነው”

July 7, 2024

የቀድሞ ኦነግ መስራችና አንጋፋ አመራሮች “አሁን ላይ ኦሮሞ ጠብመንጃ ለኩሶ የሚጠይቀው ጥያቄና የሚያገኘው ልዩ ነገር የለም። ቀሪው ጨዋ የፖለቲካ ትግል ነው” በማለት በግልጽ ጠብ መንጃ አንስተው የሚተኩሱትን ወገኖች ባጋኙት አጋጣሚዎች ሁሉ ሲተቹ ቆይተዋል። በተለይም በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚደረግ ግድያ፣ ማፈናቀል፣ እገታና ዝርፊያ መበራከቱ ህዝብ ሳይቀር ምሬት ውስጥ እንዲገባ አድርጓል። ምሬቱም ህዝብ ባካሄዳቸው ስብሰባዎች በግልጽ የቀረበ ሲሆን በአንዳንድ ቦታዎች አዛውንትና ህጻናት ሞፈርና ቀንበር ተሸክመው “የሰላም ያለህ” በሚል ተማጽኖ እንዲያሰሙ አድርጓቸዋል። እገታ፣ ግድያና ማፈናቀልን ዋና ህዝብን የማነሳሻ መንገድ አድርገው የሚጠቀሙበት እንዳሉ ሆነው ማለት ነው።

ይህ በሆነበትና ህዝብ ቆዳ ለብሶ፣ ልጆቹን ሞፈርና ቀበር አሸክሞ አደባባይ በወጣ ማግስት ነው ጃል ሰኚ አደባባይ ወጥተው ድርጅቱ የድርጅት ቁመና የሌለው፣ በህግና ድንብ የማይመራ፣ አላማ ቢስና ተጠያቂነት የሚባል ወግ የማያውቀው መሆኑን የተናገሩት። ለመለየት ምክንያት የሆናቸውም ይህ የመርህ ጉዳይ እንደሆነ ያስታወቁት።

ጃል መሮ ልዩነት መኖሩ በስፋት ይሰማ በነበረበት ወቅት፣ ጦራቸው ወደ መካከል ኦሮሚያ መነቃነቁን፣ የወለጋንና አካባቢውን መልቀቃቸውን ያስታወቁት በጃል ሰኚ በኩል ያለው ቡድን በተለያዩ የግጭት አውዶች ያሳደረባቸውብ ተጽዕኖና የበላይነት መቋቋም ስላቃታቸው እንደሆነ ስለ ግጭቱ የሚያውቁ ይናገራሉ።

አሁን ላይ እንደሚሰማውና ዝግጅት ክፍላችን ባሰባሰበው መረጃ ኦሮሚያ ውስጥ የሚነቀሳቀሰው የጃል መሮ ኃይል በጃል ሰኚ ኃይል አማካይነት የሚጸዳበት አግባብ ሰፊ ነው። ጃል መሮ ጋር የቀሩት ኃይሎችም ቢሆኑ በየዕለቱ አንድም ለመግስት፣ አንድም ወደ ለጃል ሰኚ ወገኖች በመቀላቀል ላይ ናቸው። የተቀሩትም እየተበታተኑ ነው። ለዚህ ይመስላል የኦሮሚያ የጸጥታ ኃልፊ በኦሮሚያ የሚነቀሳቀሱ ነፍጥ ያነገቡ ኃይሎች ቢበዛ በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ እንደሚጸዱ አፋቸውን ሞልተው የተናገሩት።

የጃል ሰኚ ኃይል ምን ያህል ከመንግስት ኃይላትና መዋቅር ጋር እንደሚናበብ ባይታወቅም፣ ጃል ሰኚ ለጊዜው በምግስ በኩል በበጎ የሚታዩ ለመሆናቸው አቶ ሽመልስ በቂ ምስክር ናቸው።

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሺመልስ አብዲሳ ኦክቶበር 9 በኦሮሚኛ ባሰራጩት ጽሁፍ በጃል ሸኚ የሚመራው ቡድን ለሰላም ውይይት ዝግጁ መሆኑን ማስታወቁን ” መልካምና የሚበረታታ እርምጃ ” ሲሉ ስም ጠርተው ነው ያደነቁት።

“ቃል በገባነው መሰረት” አሉ አቶ ሽመስል ” ቡድኑ በሚታመን ደረጃ፣ በቀናነት በተግባር ለዕርቅ ከተዘጋጀ መንግስታችን ለሰላም እጁን ዘርግቶ ለውይይት ይቀመጣል” ሲሉ አስታውቀዋል።

ይህ ብቻ ሳይሆን በበርካታ መረጃዎች የጃል መሮ ኃይል እንዳክተመለት የሚናገሩ በዝተዋል። ከውጭም ቢሆን ድጋፉ ቀንሷል። በዛንዚባር በተደረገው የሰላም ውይይት ላይ ተስማምቶ ሲያበቃ ባለቀ ሰዓት አሳቡን የቀየረው ጃል መሮ፣ ከዚያን ቀን ጀምሮ በርካታ እድሎች ከእጁ እንደወጡ እየተሰማ ነው። ጃል ስኚ ቀደም ሲል የሰላም ስምምነቱ ተግባራዊ እንደሚሆን ይጠብቀ እንደነበር መግለጹ በራሱ አንዱ የልዩነቱ መካረሪያ ነጥብ ስለመሆኑ ማሳይ ነው።

ጃል መሮ የሰላም ስምምነቱን ከጠንቀቀ በሁዋላ ባለቀ ሰዓት የገለበጠው ከአገር ቤትና ዋና ድጋፍ ከሚያደርጉ ክፍሎች ሆነ ተብሎ በስልክ የሰላም ሂደቱን የሽግግር መንግስት እስካልተቋቋመ ድረስ እንዳይቀበል በሚል ግፊት ተደርጎበት ስለመሆኑ በወቅቱ ተሰምቷል።

ከዚያን ጊዜ በሁዋላ በውስጥ በህዝብ፣ በድርጅት እንዲሁም በደጋፊዎች በካከል ድጋፍ እያጣ የሂደው የጃል መሮ ቡድን አሁን ለደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ ግድ ሆኗል። አስተየት የሚሰጡ እንደሚሉት ጃል መሮ ከወደ ሰሜን ድጋፍ የሚያደርጉላቸውን አካላት በሙሉ ትተው ለኦሮሞ ህዝብ ሲሉ በይቅርታ ለመንግስትይ እጃቸውን መስጠት ይበጃቸዋል። ምክንያቱም ወደ ኡጋንዳና ደቡብ ሱዳን መሄድ አይችሉም። ወደ ኬንያም ካመሩ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ተላልፈው የሚሰጡበት ዕድል ሰፊ ነው። ይህን ካላደረጉ ከጃል ሰኚ እጅ አያመልጡም። ካመለጡም ከመንግስት ዓይን ሊሸሸጉ አይችሉም።

“መዋቅር ሲፈርስ መዋቅር ፈረሰ ነው” የሚሉ ብዙ ዝርዝር መናገር ባይፈልጉም ጃል ሰኚ ሁሉም መዋቅር እጁ ላይ ስላለ ከመንግስት ጋር ከመሰጠረ ምን ሊመጣ እንደሚችል ጃል መሮ ብቻ ሳይሆን ሁሉም ስለሚረዳ፣ ህዝብም ነፍጥ ስለሰለቸው በዚህ እንዲያበቃ ባይ ናቸው።

በሌላ በኩል ኦሮሚያ ህዝቡ ለተቃዋሚ ድርጅቶች ቀደ ሲል የነበረው ስሜት አሁን ላይ የለም። በውጭ አገር በሚጠሩ ውይይቶች ላይ እንደቀድሞ መቀነት የሚፈቱ፣ ኪሳቸውን እየነሸጣቸው የሚገለብጡና በሰዓታት ሚሊዮን የሚሰበስቡ አይታዩም። በአሜሪካና በካናዳ የተለያዩ ስቴቶች ከደጋፊዎችቻቸው ጋር ለመነጋገር ወደ አሜሪካ ያመሩት ፕሮፌሰር መረራ ከኤድመንቶን በስተቀር ይህ ነው የሚባል ህዝብ ለስብሰባ እንዳልወጣ ካናዳ ሆነው የሰጡት ቃለ ምልልስ ያስረዳል።

ከኤርትራ በረሃና የአስመራ የግዞት ህይወት ወደ በአዲስ አበባ በክብር የገባው ኦነግ ” ትግል ማለት በሄዱበትና በገቡበት ሁሉ መነጣጠቅ ነው” ብሎ ያመነ ይመስል ሁለት ቦታ ተከፍሎ በመኖርና አለመኖር መካከል ከህዝብ ተነጥሎ ብቻውን እየተንፏቀቀ መሆኑን የሚናገሩ ” ማፈሪያዎች” ይሉዋቸዋል። “ሙክት ካኮላሸው” እንዲሉ ከሻዕቢያና ወያኔ ቁርበት ላይ መነሳት አቅቶት እዛው የሚንከባለለው ኦነግ፣ ዘመናዊ አሳብ ያላቸው፣ ወቅቱን የሚመጥኑ፣ በሰለጠነ ፖለቲካ የወደፊቱን ዓይተው የሚራመዱ አዳዲስ መሪዎች ማፍራት አቅቶት ” ለኦነግ ማኒፌስቶና መተዳደሪያ ደንብ ምን ያደርገለታል” በሚሉ ያረጡ ፖለቲከኞች መመራቱን አብዝተው ይኮንናል።

የኦሮሞን ምርጦች እነ ነዲ ገመዳን ከበሉ አካላት ጋር እየመሰጠሩ በሴራ ፖለቲካ የወለጋን ህዝብ ያስራቡ፣ በታሪኩ አይቶት የማያውቀውን የስንዴ እርዳታ ተቀባይ ያደረጉ፣ ፖለቲከኞች እውን ኦሮሞን ይመጥናሉ? በሚል የሚጠይቁ፣ ኦሮሚያ የነቁ ልጆች እንጂ ያረጀ እሳቤ ያላቸውን እንደማትፈልግ ይገልጻሉ። ገዢውን አካል የአሳብ የሚበልጡ ትንታግ ፖለቲከኞችን የሚመኙት እነዚህ ክፍሎች፣ በኦሮሚያ በተቃዋሚ ወገን ያሉ አዛውንት አመራሮች “በቃን” በማለት ለመንግስትም፣ ለትውልድም ምሳሌ ሊሆኑ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ሙሉውን አስተያየት በቀጣይ ይዘን እንቀርባለን።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Sudan’s RSF accuses Egypt of involvement in air strikes on its forces
“የአስዋን ግድብን እንመታለን” ሲሉ የሱዳን ፈጣን ኃይሎች RSF ግብፅን አስጠነቀቁ፤ ግብጽ ቁጣዋን እያሰማች ነው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
TIPS 1

WFP Country Director Says Ethiopia Registered Significant Economic Transformation by Focusing on Rural Dev’t, Poverty Reduction

July 28, 2025
TIPS 1

Almost a third of people in Gaza not eating for days, UN food programme warns

July 26, 2025
TIPS 1

Israeli spy chief visits US amid bid to move Palestinians out of Gaza – Axios

July 20, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2