Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  TIPS 1  የታጋቾች ዜና ለፖለቲካ ፍላጎታቸው ቅድሚያ በሰጡ ክፍሎች ሳቢያ እየተዛባ ነው፤ “በሰው ልጅ መቆመር ያብቃ”
TIPS 1

የታጋቾች ዜና ለፖለቲካ ፍላጎታቸው ቅድሚያ በሰጡ ክፍሎች ሳቢያ እየተዛባ ነው፤ “በሰው ልጅ መቆመር ያብቃ”

Ethioreview newsEthioreview news—July 11, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የተማሪዎችና የሰላማዊ ዜጎችን ዕገታ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ከሆነ ዓመታት አስቆጥሯል። ጉዳዩ ፖለቲካ መሆኑ ይፋ ቢሆንም አንድም አካል ሃላፊነት ወስዶ በይፋ እገታ ስለፈጸመበት ምክንያትም ሆነ ምን ለመደራደር እገታው እንደተፈጸመ አይገለጽም። ዜናውን የሚበትኑት አካላትና ሚዲያዎችም ይህ የሚያስጨንቃቸው አይመስልም። የእገታ ዜና በተሰማ ቁጥር ከየአቅጣጫው የሚወረወረው ዜና ከራስ የፖለቲካ ፍላጎትና መንግስትን ለመዝለፍ ፍጆታ ስለሚውል መረጃው የተዛባ እየሆን ዜጎችን እየረበሸ ነው። ሰሞኑን የሆነውም ይህ ነው።

ከአማራ ክልል ተነስተው ወደ አዲስ አበባ በሦስት በአውቶብሶች ሲጓዙ የነበሩ ከ160 የሚበልጡ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ሰኔ 25/2016 ዓ.ም. ኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ውስጥ በታጣቂዎች መታገታቸው ይታወሳል።

ታጋቾቹ አብዛኞቹ የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መሆናቸው የታወቀ ሲሆን፤ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገርበ ጉራቻ አካባቢ “ሸኔ” በተባሉ ታጣቂዎች መታገታቸውን ከእገታው ያመለጡ ተማሪዎች እና የታጋች ቤተሰቦች ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በታጣቂች ታግተው የተወሰዱት ከ160 በላይ ተማሪዎች ተለቀዋል ሲል የኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አስታውቋል፡፡ የክልሉ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ በትናንትናው እለት በይፋዊ ማህበራዊ ገጹ ያወጣው መረጃ የታገቱት ተማሪዎች መንግስት እና ህዝብ በወሰዱት የተቀናጀ ኦፕሬሽን እንደሆነ አመልክቷል። ይህንኑ መረጃ ጠቅሰው የተለያዩ ሚዲያዎችና ግለሰቦች ክልሉ መዋሸቱን እየጻፉና እያሰራጩ ነው።

More stories

ዘመነ ካሤ ቀድሞ ወደ ድርድር ?  ሰባት የፋኖ ቡድኖች ያሉበት ስብሰባ ቃለ ጉባኤ

July 22, 2024

በኦሮሚያ የሰላም ውይይት ፍንጭ ተሰማ፤ “ጃል መሮ እጅ ካልሰጡ ከጃል ሰኚና ከመንግስት አያመልጡም”

October 11, 2024

ኢምሬት ከፈረንሳይ ጋር ያሰረችውን የ 20 ቢሊዮን ጦር መሳሪያ ግዢ አቋረጠች

August 31, 2024

ኢትዮጵያ እንዲህ ተዘርፋለች፤ ” አሁንም ሌቦች አሉ የመንግስት ሌብነት ማለት ግን ይህ ነው”

July 7, 2024

“የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እና የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ባለፈው ሳምንት በታጣቂዎች የታገቱ አብዛኞቹ ተማሪዎች መለቀቃቸውን ቢገልጹም የታጋች ቤተሰቦች ግን ተማሪዎቹ አሁንም ታግተው እንዳሉ ተናገሩ” ይላል የቢቢሲ ዘገባ።

ቢቢሲ ኢሰማኮ የመንግስት ባለስልጣናትን ባገኘው መረጃ እንደነገረው ከሆነ 138 የሚሆኑት መለቀቃቸውን ዘግቧል። በዛው ዘገባ “አንድ የታጋች ቤተሰብ” እያለ መቶ የሚሆኑት ታጋቾች ሙሉ በመኡሉ እንዳልተለቀቁ በመጥቀስ የኦሮሚያ ባለስልጣናት የቅጥፈት ዜና መናገራቸውን አስፍሯል።

አሁን ላይ በጋዜጠኛነት ስራ እንደማይሰሩ የሚናገሩት አቶ ኤሊያስ መሰረት “በተደረገ ጥብቅ ኦፕሬሽን ከ167 ታጋች ተማሪዎች መካከል 160ዎቹ ተለቀዋል” ሲሉ የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ መናገራቸውን ጠቅሶ በኤክስ ገጻቸው ላይ የሚከተለውን አስፍረዋል።

“እውነት ይሆን? ብዬ የታጋቾች ቤተሰቦችን፣ የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ወንጌላዊያን ህብረትን እና የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንትን ማምሻውን ጠየቅኩ። ምላሹ ይህን ይመስላል” በለው የጥርጣሬያቸውን መነሻ ሳይዘረዝሩ ማጣራት ማካሄዳቸውን ይገልጻሉ።

“አሁንም ልጆቻችን በእገታ ስር ናቸው፣ የማስለቀቂያ ገንዘብ ከህዝብ እየለመንን ነው። በዚህ ግዜ እንዲህ አይነት መረጃ ማውጣት የጭካኔ ስራ ነው” የሚለውን የታጋቾች ቤተሰቦች እንደነገሯቸው ያመለክታሉ። የታጋቾች ቤተሰቦች ሲሉ ምን ያህሉን እንዳናገሩ፣ ታገቱ የተባሉት ተማሪዎች ቤተሰቦች ሲሉ የት የሚኖሩትን እንደሆነ አቶ ኤሊያስ አላስታወቁም።

“ታግተው ያሉ በርካታ ተማሪ አልተለቀቁም፣ ተለቀቁ ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ከየት እንደመጣ አናውቅም” የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ወንጌላዊያን ህብረት ምላሽ እንደሰጣቸው የጻፉት አቶ ኤሊያስ መሰረት ተማሪዎቹ ደባርቅን ለቀው ከወጡ ከደባርቅ ዩኒቨርስቲ እንዴት የተሟላ መረጃ ማግነት እንደሚቻል ሳይተቅሱ የዩኒቨስርስቲውን ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስማማው ዘገዬን አነጋግረዋል። “አንዴ መረጃ ሰጥቻለሁ፣ እኔ ጋር ለምን ትደውላላችሁ?” የሚል መልስ እንደሰጡዋቸው ጽፈዋል።

ቢቢሲም ሆነ አቶ ኤሊያስ ልጆች የታገተባቸውን ቤተሰቦች “እንድ” በሚል ሲገልጹ ለምን ስምና አድራሻን ማስታወቅ እንዳልፈለጉ ያሉት ነገር የለም። ተማሪዎቹ ዳባርቅ ዩኒቨርስቲ የሚማሩ የለኤላ አካባቢ ተወላጆች መሆናቸውን የሚጠቅሱ ሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ አንቂ ነን ባዮች ለሚሰራቸው ዜና እርምት እንዲሆን ያሉትን ጽፈው አሰራጭተዋል።

“የታገቱት ተማሪዎች ለእረፍት ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ ያሉ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንጂ የደባርቅ ነዋሪዎች አይደሉም” ይላል ናትናኤል መኮንን። ይቀጥልና “አንዳንዶች ሙሉ መረጃ በሌላቸው ጉዳዮችም ላይ የማይሆን ነገር መጻፋቸውን ታዚቢያለሁ። ህዝብን ለማደናገር” እንደሆነ ያመልክታል።

ናትናኤል እንደሚለው የታገቱት ተማሪዎች በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኘው ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ የኦሮሚያና የሌሎች ክልሎች ተወላጆች ናቸው። ይህን ካለ በሁዋላ “መረጃ አለኝ የምትሉ ሰዎች ወይም ጉዳዩን እውንታ ማጣራት የምትፈልጉ ጋዜጠኞች ወደ ኦሮሚያ ክልል በተለይ አብዛኛዎቹ ተማሪዎች የወለጋ ልጆች ስለሆኑ ወደ ወለጋ ደውላችሁ እውነቱን ለህዝብ አድርሱ” ሲል ይመክራል። ሲያጠቃልልም መረጃ ለመውሰድ ደባርቅ ዩኒቨርስቲ ሳይሆን ወለጋ ወይም ኦሮሚያና ሌሎች ክልሎችን ማግኘት እግባብነት እንዳለው ያመልክታል። እንደ ጥቆማው ከሆነ ልጆቹ ከአማራ ክልል ደባርቅ ስለወጡ ትክክለኛ መረጃ የሚገኘው አሁን ላይ ደባርቅ ሊሆን የማይችልበትን አመክንዮ ያሳያል።

አቶ ኤሊያ መሰረት@EliasMeseret ባሰራጩት ዜና ስር ” ልጄ ታገተ ብሎ መናገር ለምን ያስፈራል? ምንስ ችግር አለው?” የሚል ጥያቄ ቀርቧል። በአብዛኛው ተለቀዋል የሚለውን ዜና ሳይሆን ” አልተለቀቁም፣ መንግት ላይ ተስፋ ቆርተዋል፣ መንግስትን አይምኑም ወዘተ” በሚሉ ተቀጽላዎች የታጀበው የዕገታ ሪፖርት በርካቶችን ግራ ያጋባውም በዚህና በበርካታ ምክንያቶች ነው።

ሲጀመር በተለያዩ ጊዜያት እገታ ሲፈጸሙ የቆዩ በስም የሚታወቁና የማይታወቁ አካላት ለድርጊታቸው ሃላፊነት አይወስዱም። ምን እንዲፈጸምላቸው አስበው እገታ እንደሚፈጽሙ አያስታውቁም። በመቶ የሚቆተር ተማሪዎች ታግተው ሲነዱ የሚመከቱ ለህግ አካላት ወዲያውኑ ሪፖርት አይደርጉም። በመቶ የሚቆጠሩ ታጋቾች በቀያቸውና ደጃቸው፣ በማሳቸው በታጣቂዎች ሲነዱ ነዋሪዎች ፈጥነው መረጃ የማይሰጡ ከሆነ አጋቾቹ ከሩቅ መጡ ለማለት እንደሚቸገሩ በርካቶች ይናገራሉ።

በዚህ መነሻ እገታው ዓላማና ከጀርባው ፖለቲካዊ ጥያቄ ከሌለው በየመንደሩ የተደራጁ ቡድኖች የሚፈጽሙት ተግባር ከመሆን አያልፍም። ለዚህ ነው የእገታ ዜና ሲሰማ፣ ዜናውን የሚያቀጥጥሉት ወገኖች ጉዳይም አብሮ የሚነሳው። አብርሃም ሃይሌ የተባሉ አስተያየት ሰጪ ” እገታ ኢትዮጵያ ውስጥ ሴራ ተኮር ድራማ ነው። ዜናውን የሚያጨሱት ወገኖች በአብዛኛው በሰብአዊነት ሳይሆን ከራሳቸው፣ ወይም ከተቀጠሩለት ዓላማቸው አንጻር የሚቃኙት ጉዳይ ነው” በሚል አዘኔታቸውን ጠቅሰው መናገራቸው ይታወሳል። ሳትታገት ታገተች የተባለውችውንና ሰፊ የሚዲያ ሽፋን አግኝታ የነበረችውን እንስት አንስተው ግርምታቸውን ገልሰው ነበር እኚሁ አስተያየት ሰጪ የቋጩት።

ዜናውን መጀመሪያ የሰራው ቲክቫህ ኢትዮጵያ አንድ ያመለተ ልጅ እንደነገረው ጠቅሶ ዜናውን ሲያሰራጭ እንዳለው ሰኞ ዕለት ከደባርቅ ዩኒቨርስቲ በአውቶብስ ተሳፍረው ወደ ቤተሰብ እየተጓዙ የነበሩ ተማሪዎች ገብረ ጉራቻ ከተማ ሲደርሱ በታጣቂዎች መታገታቸውን አንድ ያመለጠ ተማሪ አረጋግጦ ነበር። ቲክቫህ ያነጋገረው ይህ ተማሪ “ሁለት አውቶብስ ተማሪዎች በታጣቂዎች ታግተዋል” ነበር ያለው።

ከቀን በሁዋላ በተሰማ ዜና በርካታዎቹ ያለምንም ክፍያ ተለቀዋል። የተረፉት እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር እየተጠየቁ ነው። እገታው እንደተፈጸመ “ መከላከያ አብዛኛዎቹን ልጆች አስመልሶ መከላከያ ካምፕ ውስጥ ያደሩ ልጆች እንዳሉ፣ የተወሰኑ ደግሞ በሌላ መኪና ተሳፍረው አዲስ አበባ መግባታቸውን የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት አስታወቀዋል” ሲል ቲክቫህ በዘገባው አካቷል። እንግዲህ ኦሮሚያ ይህንኑ ዜና ሲደግመው አቶ ኤሊያስ መሰረትን ጥርጣሬ ውስጥ የከተታቸው ዋና ቁልፍ ጉዳይ ምን ይሆን? የሚለው ጥያቄ እንዲነሳ ምክንያት ሆኗል።

ከ2ኛ እስከ 4ኛ ዓመት ተማሪዎች መታገታቸውን የዓይን እማኞች፣ የታጋች ቤተሰብና ዩኒቨርሲቲው አረጋጠው መስክረው ተጨማሪ ማረጋገጫ ሰጥተዋል። እንደተባለው ከሆነ ሁለት አውቶብሶች ከደባርቅ፣ አንድ ደግሞ ከባህር ዳር ሰው ሞልተው ሲጓዙ የነበሩት አውቶቡሶች ውስጥ የነበሩ ተማሪዎች የታገቱት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገብረ ጉራቻ አካባቢ ነው። አጋቾቹም የሸኔ ታጣቂዎች እንደሆኑ ተመልክቷል። ከእገታው የተወሰኑ ተማሪዎች ሲያመልጡ ዛሬ ደግሞ የተወሰኑት 150 የሚደርሱ መለቀቃቸውን ቲክቫክ ቤተሰቦቻቸውን ጠቅሶ ዘግቧል። በሚል መዘገባችን ይታወሳል።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“በጸጥታ እና ተያያዥ ችግሮች ፈተና መውሰድ ያልቻሉ ተማሪዎችን የማካካሻ ትምህርት በመስጠት ፈተናውን እንዲወስዱ ይደረጋል”
ቡና ላኪዎች ለአቅራቢዎች በወቅቱ ክፍያ አለክፈላቸው ማዘግየታቸው አምራቾችን ለጉዳት እየዳረገ ነው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
TIPS 1

WFP Country Director Says Ethiopia Registered Significant Economic Transformation by Focusing on Rural Dev’t, Poverty Reduction

July 28, 2025
TIPS 1

Almost a third of people in Gaza not eating for days, UN food programme warns

July 26, 2025
TIPS 1

Israeli spy chief visits US amid bid to move Palestinians out of Gaza – Axios

July 20, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2