አርብ ኤምሬትስ የአሜሪካ ሁለተኛዋ ”ዋነኛ የመከላከያ አጋር” መሆኗን አሜሪካ አስታወቀች። ሁለቱ አገራት ወታደራዊ ስምምነት ያደረጉት በዋናነት “በመካከለኛው ምስራቅ፣ ምስራቅ አፍሪካ እና ህንድ ውቅያኖስ ክልል ወታደራዊ ትብብርን ይበልጥ የሚያጎለብት ነው” ሲል ዋይትሃውስ አጋርነቱን አጉልቶ በመግለጫው አመልክቷል። ዜናው ለኢትዮጵያ መልካም ብስራት እንደሆነ ጉዳዩን የሚከታተሉ ገልጸዋል።
The US announced the UAE as a ‘major defence partner’ – a status accorded so far only to India – in a joint statement issued on Monday
ይህን የላቀ የተባለ ስምምነት ለማከናወን በአሜሪካ የመጀመሪያውን ይፋዊ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት የአረብ ኤምሬትስ ፕሬዝዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ በነጩ ቤተመንግስት ከፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ጋር በአንድነት መክረዋል።
ከዚሁ ምክክር በሁዋላ ከነጩ ቤተመንግስት የወጣው መግለጫ ሁለቱም አገራት በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር ለመስራትና ያላቸውንም ህብረት ለማጠናከር እንደተስማሙ ይፋ አድርጓል።
መግለጫው አሜሪካ የኤምሬትስን ደህንነትና የግዛት አንድነት አደጋ ላይ የሚጥሉ የውጭ ስጋቶችን ለመከላከል የቴክኖሎጂና ሌሎች ድጋፎችን እንደምታደርግ አመልክቷል።
የኢትዮጵያ የቅርብ ወዳጅ የሆነችው ኤምሬትስ ለአሜሪካ ያሰራቸው ውል “በመካከለኛው ምስራቅ፣ ምስራቅ አፍሪካ እና ህንድ ውቅያኖስ ክልል ወታደራዊ ትብብርን ይበልጥ የሚያጎለብት ነው” መሆኑ አሁን ላይ ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ያደረገችውን የባህር በር ስምምነትና የጦር ቤዝ ግንባታ አይቀሬነት የሚያረጋግጥ ስለመሆኑ ነው “ዜናውን ለኢትዮጵያ በጎ ብስራት” ሲሉ የገለጹ ክፍሎች የሚናገሩት።
የኢትዮጵያን ቀይ ባህር ላይ መመለስና የጦር ቤዝ መገንባት የምትደግፈው እስራኤል ከኤምሬትስ ጋር የጠበቀ የንግድ ትብብር እንዳላቸው ይታወቃል። ኤምሬትስ ከምስራቅ አፍሪቃ እሰክ ህንድ ውቅያኖስ ወታደራዊ ስምምነት ከአሜሪካ ጋር ማድረጓ በቀጥታ ኢትዮጵያ በባብኤልመንደብ የምትገነባውን የጦር ቤዝ አስፈላጊነት የሚያሳይ እንደሆነ እነዚሁ ወገኖች አብራርተዋል።
አሜሪካ እና ኤምሬትስ ግጭትን ለመከላከልና ለማብረድ የጋራ አቋም ይዘው የደህንነት ትብብራቸውን ማጠናከራቸውን በማንሳትም የፕሬዝዳንት ባይደን አስተዳደር አቡ ዳቢን ሁለተኛዋ “ዋነኛ የመከላከያ አጋር” አድርጎ እውቅና እንደሰጣት አብራርቷል። አሜሪካ በ2021 ህንድን “ዋነኛ የመከላከያ አጋር” አድርጋ መሰየሟ የሚታወስ ነው።
በዚሁ ስምምነት መሰረት ኤምሬትስ ከአሜሪካ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ ለማድረግና የደህንነት ትብብሯን ይበልጥ ለማሳደግ እድል ታገኛለች ማለት ነው። ይህ ሙሉ ወታደራዊ የአጋርነት ስምምነት ዘርፈ ብዙ በመሆኑ ኢትዮጵያን እንደሚጠቅም በስፋት እየተገለጸ ነው።
መሪዎቹ ከወታደራዊ ስምምነታቸው በተጨማሪ፣በንግድና ኢንቨስትመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ህዋ ምርምርና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት በሚያሳድጉ ጉዳዮች ላይም እንደመከሩ ተገልጿል።
ኢምሬትስ የኢትዮጵያ የልብ ወዳጅ መሆኗን ለሚረዱ፣ በሶማሊላንድ የበርበራ ወደብን 42 ሚሊዮን ዶላር በማውጣት ማዘመኗን ለሰሙ፣ አሁን ላይ ወደቡን የምታስተዳድረው እሷ እንደሆነች ለሚያውቁ ትናት ይፋ የሆነው የአሜሪካና ዋንኛ የመከላከያ አጋርነት ስምምነት ኢትዮጵጵያ በቀይ ባህር የመመለሷን ጉዳይ ያከተመለት ጉዳይ እንደሆነ የሚያሳይ ተደርጎ ተወስዷል።
ኢትዮጵያና ሶምሊላንድ የፊታችን ቅዳሜ ስምምነታቸውን በይፋ የፊርማ ስነስርዓት እንደሚያጸድቁ በሚጠበቅበት በአሁኑ ሰዓት፣ ኤምሬትስ በምስራቅ አፍሪቃ ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ አጋር ለመሆን ስምምነት ላይ መድረሳቸው አካሄዱ መናበብ ያለበት እንደሆነ ታዛቢዎች እየገለጹ ነው።
እስራኤል ግብጽን በሶማሌ የምታደርገውን ደፋ ቀና ማውገዟን ተከትሎ የተሰማው ይህ ዜና፣ ኢትዮጵያ ከበባውን እንደምትበጣጥስ የሚያሳይ ስለመሆኑም በበርካታ ማስረጃዎች “ዜናው ለኢትዮጵያ ብስራት ነው” ያሉት ወገኖች ገልጸዋል።

