Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News2  ሶማሊያ ከየትኛውም አገር የመጡ ወታደሮች ወደ ግዛቴ አልገቡም”ማለቷን ቢቢሲ ዘገበ
News2

ሶማሊያ ከየትኛውም አገር የመጡ ወታደሮች ወደ ግዛቴ አልገቡም”ማለቷን ቢቢሲ ዘገበ

Ethioreview newsEthioreview news—September 11, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የግብጽ ወታደሮች ወደ ሶማሊያ እየገቡ መሆኑ መዘገቡን ተከትሎ የሶማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር በአገራቸው የየትኛውም አገር መንግሥት ወታደሮች እንደሌሉ በመግለጽ አስተባበሉ።

የሶማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሐምዛ አብዲ ባሬ ማክሰኞ ጳጉሜ 5/2016 ዓ.ም. ሞቃዲሾ ውስጥ ባደረጉት ንግግር፤ የትኛውም አገር ወደ ሶማሊያ ወደታሮቹን እያስገባ እንዳልሆነ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ግንኙነት መሻከሩን ተከትሎ ሶማሊያ እና ግብጽ ወታደራዊ ትብብር ለማድረግ ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ግብጽ ወታደሮቿን ሶማሊያ ውስጥ እንደምታሰማራ በስፋት ሲዘገብ ቆይቷል።

ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ባለው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምክንያት ከኢትዮጵያ ጋር ለዓመታት ውዝግብ ውስጥ የቆየችው ግብጽ፣ በሁለቱ አገራት መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ተከትሎ ወታደሮቿን በሶማሊያ ልታሰማራ መሆኑ ከተነገረ በኋላ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ውጥረት ተባብሷል።

ከሳምንት በፊት የጦር መኮንኖችን እና ወታደራዊ አቅርቦቶችን የጫኑ ሁለት የግብጽ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ሞቃዲሾ ማረፋቸው በስፋት የተዘገበ ሲሆን፣ ይህም ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ከሶማሊያውን ጭምር ተቃውሞ ገጥሞት ነበር።

ይህንንም ተከትሎ ሶማሊያ የውጭ ኃይሎችን ወደ ግዛቷ እንዲገቡ መፍቀዷ የአካበቢውን ሰላም እንደሚያናጋ በመግለጽ እርምጃውን ኢትዮጵያ በይፋ ተቃውማለች።

በተጨማሪም የሶማሊያ የተለያዩ ግዛቶች ባለሥልጣናት እና የፌደራል መንግሥቱ ፓርላማ አባላትም መንግሥት የግብጽ ወታደሮች ወደ ሶማሊያ እንዲገቡ መፍቀዱን በይፋ ተቃውሞው ከፍተኛ ውዝግብ አስከትሏል።

የግብጽ ወታደሮች ወደ ሶማሊያ መግባት ከተነገረ እና በአገሪቱ ውስጥ እና ከውጪ ተቃውሞ መሰማት ከመጀመረ ከሳምንታት በኋላ የሶማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሐምዛ አብዲ ባሬ “የትኛውም አገር ወደ ሶማሊያ ወታደሮቹን እያስገባ አይደለም” በማለት አጥብቀው አስተባብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት “ወታደሮቹን ወደ ሶማሊያ የሚያመጣ መንግሥት የለም፤ የጠየቀንም መንግሥት የለም” በማለት ነገር ግን “ነጻ አገር እንደመሆናችን [ሶማሊያ] የፈለግነውን ለማድረግ መብቱ አለን” ብለዋል።

ጨምረውም “አረብ አገራትን እንዲረዱን ብንጠይቅ እና ጥያቄያችንን ቢቀበሉት፤ ይህ ማለት ሌላ አገርን ለማጥቃት ነው ማለት አይደለም” በማለት ሶማሊያም ሆነች ሌላ አገር ወታደሮቹን በአገሪቱ ውስጥ ለማስፈር ጥያቄ አለማቅረባቸውን አስረድተዋል።

ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የተፈራረመችውን ስምምነት ተከትሎ በሶማሊያ እና በኢትዮጵያ መካከል ፖለቲካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ውዝግብ ሲካሄድ የከረመ ሲሆን፣ በአፍሪካ ቀንድ ውጥረትን በማስከተል እስካሁን ድረስ ዘልቋል።

ከ15 ዓመታት በላይ ወታደሮቿን በሶማሊያ አሰማርታ የአገሪቱን መንግሥት ስትደግፍ የቆየችው ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያ ከግብጽ ጋር የደረሰቸውን ወታደራዊ ስምምነት ተከትሎ ወታደሮቿን ወደ ሶማሊያ ልታስገባ ነው መባሉ አስቆጥቷታል።

ነገር ግን ሶማሊያ ወታደራዊ ድጋፍን የምትፈልገው ከአረብ አገራት ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን ጨምሮ ፈቃደኛ ከሆኑ ከሌሎች አገራት ጭምር መሆኑን የሶማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ተናግረዋል።

“ድጋፍ ሊያደርጉልን ከሚችሉ አገራት ሁሉ እንፈልጋለን፤ ከእነሱ [ኢትዮጵያ] ጋርም ብዙ ሥራዎችን ሠርተናል፤ አሁንም ድጋፍ የሚሰጡን ከሆነ ለመቀበል ዝግጁ ነን” ብለዋል ሐምዛ አብዲ ባሬ።

የግብጽ ወታደሮች ረጅም ድንበር በምትጋራት ሶማሊያ ውስጥ መስፈሩ በኢትዮጵያ መንግሥት ተቃውሞ የገጠመው ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ በተለያዩ አጋጣሚዎች ላይ ጉዳዩን አንስተው አገራቸው ለሚከሰት ማንኛው ነገር ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።

በቅርቡ ሙሉ ለሙሉ እንደሚጠናቀቅ የተነገረለት እና ኃይል ማመንጨት የጀመረው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በግብጽ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለመግባባት ምንጭ ሆኖ ከአስር ዓመታት በላይ ቆይቷል።

ግብጽ ኢትዮጵያ የምትሳትፍበት የሶማሊያ ሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ ወታደሮቿን ለማሰማራት ፍላጎት እንዳላት ገልጻ ከሶማሊያ ጋር ወታደራዊ ስምምነትን ከተፈራረመች በኋላ በቅርቡ ወታደራዊ አውሮፕላኖችን ወደ ሞቃዲሾ ልካላች።

ይህ ከሆነ ከጥቂት ሳምንታት በኋላም የሕዳሴ ግድብ ከተገነባበት የአባይ ወንዝ የምታገኘውን የውሃ ጥምቅ ለማስከበር እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል ግብጽ ለተባበሩት መንግሥታት በጻፈችው ደብዳቤ የገለጸች ሲሆን፣ ኢትዮጵያም ይህንን በመቀዋም ለድርጅቱ ባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ ደብዳቤ ጽፋለች።

ግብጽ ወደ ሶማሊያ ሠራዊቷን ለማሰማራት የፈለገችው በሶማሊያ ውስጥ የሚንቀሳቀሰውን ታጣቂ ቡድን አልሻባብንን በመዋጋት ላይ ያለውን የሶማሊያን ጦር ለመደገፍ ብቻ ሳይሆን፣ በኢትዮጵያ ላይ ተጽእኖን ለማሳደር እንደሆነ በአንዳንድ ወገኖች ሲገለጽ ቆይቷል።

BBC

home
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
አብይ አሕመድ 2017 በታሪክ የሚጠቀስ ዘመን እናድርግ ሲሉ ጥሪ አቀረቡ
BRICS Confirms 159 Participants Will Adopt New Payment System
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News2

ብሔራዊ ጥቅምን አሳልፎ ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ባለድርሻ ሊሆኑ አይገባም – በለጠ ሞላ

March 8, 2026
News2

ለክቡር የኢፌዴሪ ማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኝና ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው የቀረበ ጥሪ

March 8, 2026
News2

ስምረት ፓርቲ የትግራይ ወጣት ለትህነግ ጀርባ መስጠቱን አስታወቀ

March 6, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2