Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News2  “እገሌ ሊደራደር ነው የሚለውን ጉዳይ የፋኖ ኃይሎች  መበሻሸቂያ አድርገውታል”
News2

“እገሌ ሊደራደር ነው የሚለውን ጉዳይ የፋኖ ኃይሎች  መበሻሸቂያ አድርገውታል”

Ethioreview newsEthioreview news—September 15, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

… ይህንን መናገር አያስፈልግም፣ ምክንያቱም አንዳንዶች ነገሩን እገሌ ሊደራደር ነው በማለት መበሻሸቂያ አድርገውታል፡፡ በመሆኑም ከየትኛው የፋኖ አመራር ጋር እንደተወያየን መግለጽ ጠቃሚ አይደለም፤›

በአማራ ክልል በሚፋለሙት የፌዴራል መንግሥትና የፋኖ ኃይሎች መካከል ያለው ሥር የሰደደ አለመተማመን ሰላም ለማውረድ የሚያደረገው ጥረት ፈተና እንደሆነበት፣ የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል አስታወቀ፡፡

የካውንስሉ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ እያቸው ተሻለ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ በሁለቱ ተፋላሚ ኃይሎች መካከል መተማመንን ለመፍጠር የዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ዕገዛ ለማግኘት በቅርቡ ወይይት ተደርጓል።

የፌዴራል መንግሥት አመራሮችን ለማግኘት የካውንስሉ ጥረት አለመሳካቱን፣ እስካሁን ከፌዴራል መንግሥት በኩል ተገናኝቶ መወያየት የቻለው ከሰላም ሚኒስቴር ጋር ብቻ እንደሆነ፣ የሰላም ሚኒስቴርም ካውንስሉ የሚያቀርበውን ጥሪ እንደሚቀበል ማሳወቁን ገልጸዋል።

‹‹ከተለያዩ የፋኖ ኃይሎች ጋር ተነጋግረናል፣ ወደ ድርድር መግባትን በመርህ ደረጃ ይቀበሉታል፡፡ ነገር ግን በመንግሥት ላይ እምነት የላቸውም። ጊዜ መግዣ ነው ብለው ያምናሉ፣ እኛንም የፈተነን ይኸው ያለመተማመን ችግር ነው፤›› ብለዋል።

‹‹ከፌዴራል መንግሥት በኩል ተጨማሪ ሥራዎች ይጠብቁናል፤›› ያሉት አቶ እያቸው፣ ‹‹የፌዴራል መንግሥት ለሰላም ዝግጁ መሆኑን መናገር ብቻ ሳይሆን ምቹ ሁኔታን መፍጠር አለበት፤›› ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።

በሁለቱ ተፋላሚ ኃይሎች መካከል መተማመንን ለመፍጠር ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዕገዛ ለማግኘት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር፣ ከኢጋድና ከአፍሪካ ኅብረት አመራሮች ጋር በቅርቡ መወያየታቸውን አስረድተዋል።


‹‹ከአሜሪካ ኤምባሲ ጋር ተነጋግረናል፣ ለማገዝም ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸውልናል፡፡ በእኛ በኩል ደግሞ እየደረሰ ካለው ጉዳት አንፃር የአማራ ክልል ሁኔታን ችላ ብላችሁታል ብለናቸዋል፤›› ሲሉ አስረድተዋል።

የአሜሪካ አምባሳደርን ጨምሮ ከስድስት ዲፕሎማቶች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን፣ በውይይቱም የክልሉን የሰላም ዕጦት ችላ ማለታቸውን በመጠቆም ዲፕሎማሲያዊ ተፅዕኖ ማሳደር እንደሚገባቸው ካውንስሉ ማሳሰቡን ጠቁመዋል፡፡

የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ባለቀበት መንገድ የአማራ ክልል ጉዳይንም በዚያው መንገድ ማጠናቀቅ እንደሚገባ ማስረዳታቸውን፣ ካውንስሉ የገጠመውን የቅቡልነት ችግርና በሁለቱ ተፈላሚ ኃይሎት መካከል ሥር የሰደደ አለመተማን መኖሩን ማስረዳታቸውን ተናግረዋል፡፡

ዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ ካውንስሉ የሚያደርገውን ጥረትም ሆነ ድርድሩ እንዲሳካ ለማገዝ ፈቃደኛ መሆኑን፣ ነገር ግን በፋኖ አደረጃጀት ላይ ጥያቄ ማቅረቡን ገልጸዋል፡፡

ከየትኛው የፋኖ አደረጃጀት ጋር ተገናኝተው እንደተወያዩ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹ይህንን መናገር አያስፈልግም፣ ምክንያቱም አንዳንዶች ነገሩን እገሌ ሊደራደር ነው በማለት መበሻሸቂያ አድርገውታል፡፡ በመሆኑም ከየትኛው የፋኖ አመራር ጋር እንደተወያየን መግለጽ ጠቃሚ አይደለም፤›› ብለዋል።

‹‹እገሌ ሊደራደር ነው የሚለውን ጉዳይ የፋኖ ኃይሎች እንደ መበሻሸቂያ እየተጠቀሙበት ስለሆነ፣ ካውንስሉ የተደራጀ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ በፋኖ በኩል እገሌ እንዲህ ብሏል ከማለት እንቆጠባለን፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡

በፋኖ ኃይሎች በኩል ከሚነሱ ጥያቄዎች መካከል ዋነኛው የፌዴራል መንግሥት ድርድሩን ‹‹እንደ ጊዜ መግዣነት ሊጠቀምበት ነው›› የሚል ጥርጣሬ መሆኑን የገለጹት አቶ እያቸው፣ ከዚህ በተጨማሪም ካውንስሉ ሀቀኛ ድርድር ለማድረግ ሳይሆን ለማምታታት ነው የሚል ሐሳብ እንዳላቸው፣ ይሁንና አለመተማመኑን ለመቅረፍ የሁሉንም አካላት ቅንነት ካውንስሉ እንደሚፈልግ ተናግረዋል፡፡

ካውንስሉ ከፌዴራል መንግሥት በኩል እስካሁን መወያየት የቻለው ከሰላም ሚኒስቴር ጋር ብቻ መሆኑን አቶ እያቸው አስታውሰው፣ ይሁንና መንግሥት የድርድር ጥሪውን እንደሚቀበል መናገሩ ብቻ በቂ ስላልሆነ፣ ለሰላም የሚያስፈልጉ ምቹ ሁኔታዎችን ከመፍጠር ጀምሮ ተጨማሪ ዕርምጃዎችን መውሰድ እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል፡፡

ከአሜሪካ ኤምባሲ በተጨማሪ ከኢጋድ የፀጥታ ዳይሬክተር ጋር መወያየታቸውንና የአውሮፓ ኅብረት፣ የአፍሪካ ኅብረትና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማትን ለማግኘት ቀጠሮ መያዛቸውን አስረድተዋል፡፡

በአገር ውስጥ ከሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጋር መወያየታቸውን፣ ከጉባዔው ጋር በነበራቸው ውይይት እንደሚያግዟቸው ቃል መግባታቸውን ኃላፊው አክለዋል

ዜናው የሪፖርተር ነዉ

home
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ሻዕቢያ የኢትዮጵያን ቀይ መስመር እየጣሰ ነው፤ ለግብጽ አጋርነቷን በድጋሚ አረጋገጠች፤ ሶማሊያ ንሸራተተች
Ankara mediation talks between Somalia, Ethiopia postponed
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News2

ብሔራዊ ጥቅምን አሳልፎ ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ባለድርሻ ሊሆኑ አይገባም – በለጠ ሞላ

March 8, 2026
News2

ለክቡር የኢፌዴሪ ማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኝና ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው የቀረበ ጥሪ

March 8, 2026
News2

ስምረት ፓርቲ የትግራይ ወጣት ለትህነግ ጀርባ መስጠቱን አስታወቀ

March 6, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2