Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  አካልን ነፃ ስለ ማዉጣት (Habeas Corpus)
lawNews

አካልን ነፃ ስለ ማዉጣት (Habeas Corpus)

Ethioreview newsEthioreview news—September 23, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አካልን ነፃ ማዉጣት ከህግ አግባብ ዉጭ የታሰረ ሰዉ ከዚህ እስር እንዲፈታ ለፍርድ ቤት የሚቀርብ የፍትሐብሔር ጉዳይ ነዉ፡፡ ነገሩ የሚታየዉ በፍትሐብሔር መዝገብ ቢሆንም በወንጀል ሰበብ የታሰረዉ ሰዉ ይጠቀምበታል፡፡

መግቢያ

የሰዉ ልጆች ሰዉ በመሆናቸዉና በተፈጥሮ ያገኟቸዉ ሰብአዊ መብቶችና ነፃነቶች የተከበሩ ናቸዉ፡፡ ከእነዚህ መብቶች አንዱ ህጋዊ ያልሆነ እስርን የመቃወም መብት (አካልን ነፃ ማዉጣት) አንዱ ነዉ፡፡ የሰዎች የነፃነት መብት የሚገደበዉ ሕጋዊ በሆነ ሥርዓት ብቻ ነዉ፡፡ ይህን ለመጠበቅ ሲባል የአያያዝ ሥርዓትም ሆነ እስር ላይ የሚቆይበት ሁኔታ በሕግ በግልጽ እንዲደነገግ ይደረጋል፡፡ የአያያዝ ሕጋዊነትን ለማረጋገጥ እንዲቻል የያዘዉ ፖሊስ በ48 ስዓት ዉስጥ ወደ ፍርድ ቤት እንዲቀርብ መደረጉ የነፃነት መብትን ማረጋገጫ አንዱ መንገድ ነዉ፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ አካልን ነፃ ስለ ማዉጣት እና ተያያዥ ጉዳዮችን እንመለከታለን፡፡

አካልን ነፃ ማዉጣት(Habeas Corpus) ምንነት

More stories

ዐቃቤ ህግ በእነ ጃዋር መሀመድ ላይ «ለምስክሮቼ ደህንነት ሲባል ከመጋረጃ በስተጀርባ በዝግ ችሎት ምስክሮቼን ላሰማ» ጥያቄ ውድቅ ሆነ

April 6, 2021

በወላይታ ዞን በሙስናና የተጠረጠሩ የሥራ ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

July 27, 2024

“የበረራ ህግ ጥሰው ለማስገደድ የሞከሩ በሽብር ወንጀል ይከሰሳሉ”

August 25, 2024

አሰሪዋን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የተጠረጠረችው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለች

November 1, 2022

አካልን ነፃ ማዉጣት /Habeas Corpus/ ቃሉ የላቲን ቃል ሲሆን ትርጉሙም “that you have the body” ማለት ሲሆን ወደ አማረኛ ሲተረጎም አካል (ሰዉ) ይዘሃል የሚል ይሆናል፡፡ ሀብየስ ኮርፐስ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ተገድዶ እንዳይዘዋወር የተከለከለ ወይም የታሰረ ሰዉ ከዚህ ክልከላ ወይም እስራት እንዲለቀቅ የሚጠየቅበት ሥነ-ሥርዓት ነዉ፡፡ ከእስር እንዲፈታ የሚጠይቅ ሰዉ የታሰረዉ የወንጀል ድርጊት ፈጽመሀል በሚል ቢሆንም ሀብየስ ኮርፐስ የፍትሐብሔር ጉዳይ ነዉ፡፡ አካልን ነፃ ማዉጣት /Habeas Corpus/ ፅንሰ ሀሳብ በመጀመሪያ ተገልፆ የነበረዉ እ.ኤ.አ 1215 ለእንግሊዛዉያን ነዋሪዎች ልዩ ልዩ ነፃነቶችና መብቶችን ይዞ ብቅ ካለዉ ትልቅ ሰነድ /Magna Charta/ ማግና ካርታ ነዉ፡፡ መርሁም የንጉሶች ሳይሆን የህግ የበላይነት እንዲኖር ማድረግ ነዉ፡፡ ማንም ሰዉ ከሕግ ዉጪ በማንም ሊያዝ፣ ሊታሰር፣ ሊታገት እና እንቅስቃሴዉም ሊገደብ አይገባዉም የሚሉ ዓለም አቀፋዊ መርሆችን አቅፎ የያዘ ነዉ፡፡ ነፃነት ሊገደብ የሚችለው በህግ ሥርዓት (Due Process of law) ጠያቂና ተጠያቂነት በሰፈነበት መልኩ ሊሆን ይገባል በማለት የማግና ካርታ የዉስጥ ይዘት ያስረዳል፡፡

የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳን (International Convention on Civil and Political Rights) ሀገራችን ያፀደቀችው የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳን በአንቀጽ 9(1) ማንኛዉም ሰዉ የግል ነፃነቱና ደህንነቱ እንዲረጋገጥለት መብት እንዳለው አመልክቷል፡፡ ማንኛዉም ሰዉ በህግ ከተደነገገዉ ምክንያትና ሥርዓት ዉጭ የግል ነፃነቱ አይነፈግም፡፡ በስምምነቱ አንቀጽ 9(4) መሰረትም ማንኛዉም በመታሰሩ ወይም በመያዙ ምክንያት ነፃነቱን የተነፈገ ሰዉ የእስራቱን ሕጋዊነት ወዲያዉኑ መርምሮ ያለአግባብ መታሰሩን ካረጋገጠ በነፃ እንዲለቀቅ እንዲያዝለት ፍርድ ቤት የመቅረብ መብት አለዉ፡፡

የአካል ነፃነት አቤቱታ አቀራረብ እና አወሳሰን ሥነ-ሥርዓት

አካልን ነፃ ማዉጣት ከህግ አግባብ ዉጭ የታሰረ ሰዉ ከዚህ እስር እንዲፈታ ለፍርድ ቤት የሚቀርብ የፍትሐብሔር ጉዳይ ነዉ፡፡ ነገሩ የሚታየዉ በፍትሐብሔር መዝገብ ቢሆንም በወንጀል ሰበብ የታሰረዉ ሰዉ ይጠቀምበታል፡፡ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 177 መሰረት በወንጀል ሕግ ወይም በዚህ ሕግ የተነገረዉን መሰረት በማድረግ ፍርድ ቤት ሳይወስንበት ወይም ሳይፈርድበት ማናቸዉም ሌላ ትዕዛዝ ሳይሰጥ በማናቸዉም ሌላ ስልጣን ወይም በሌላ ሁኔታ ወይም በሌላ ሰዉ የተገደደ፣ እንዳይዘዋወር የተከለከለ፣ የተያዘ ወይም የታሰረዉ ሲኖር ይህ አድራጎት እንዲወገድለትና እራሱ ፍርድ ቤት ቀርቦ እንዲያስረዳ ሊያመለክት ይችላል፡፡ የመያዙ ወይም የመታሰሩ ትዕዛዝ የተሰጠዉ በሕግ ባለስልጣን ቢሆንም መያዙ ወይም መታሰሩ የተፈፀመበት ሁኔታ ሕግን ተቃራኒ በሆነ መንገድ ከሆነ አቤቱታ ማቅረብ ተገቢ ነዉ፡፡ በተገዳጅ የሚቀርበዉ ማመልከቻ በመሀላ-ቃል የተደገፈ ሆኖ የተያዘዉን ወይም የተገደደዉን ሰዉ ስም፣ የአስገዳጁን ሰዉ ስም፣ ተገዶ የተያዘበትን ስፍራ፣ ይህንኑ የሚያረጋግጡ ሰዎች እንዳሉ የምስክሮችን ስምና አድራሻ ዘርዝሮ የሚገለጽ ሊሆን ይገባል፡፡ የተያዘዉ ሰዉ ራሱ መቅረብና የመሀላ-ቃሉን መስጠት የማይችል ከሆነ ሌላ ሰዉ ሊያቀርብለት የሚችል ሲሆን በዚህ ሁኔታ አቤቱታውን የሚያቀርበው ሰው በሚሰጠዉ መሀላ ላይ ዋናዉ ባለጉዳይ ለመቅረብ ወይም ማመልከቻ ለመፃፍ ያልቻለ መሆኑን ጨምሮ ሊገለፅ ይገባል፡፡

በፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ ቁጥር 15(2)(ቀ) መሰረት የሚቀርበዉን አቤቱታ የመቀበል ስልጣን ሙሉ በሙሉ የከፍተኛዉ ፍርድ ቤት ሥልጣን ነዉ፡፡ በዚህ መሠረት ከፍተኛዉ ፍርድ ቤት ማመልከቻ ሲቀርብለት አስገዳጁ ወይም አሳሪዉ ተገዳጁን ወይም ታሳሪዉን ሰዉ ይዞ እንዲቀርብና ይህንንም ሰዉ የማይለቅበትን ምክንያት እንዲያስረዳ በመጥሪያዉ ላይ የመቅረቢያዉን ቀነ ቀጠሮ ወስኖ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ እንዲሁም ለፍርድ ቤቱ በቀረበዉ ማመልከቻ ላይ ነገሩን በምስክርነት ለማስረዳት ይችላሉ ተብለዉ የተጠቀሱት ምስክሮች እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሊሰጥ ይችላል (የፍ/ /ሥ/ሥ/ህ/ቁ 178)፡፡

በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 179 መሰረት ጉዳዩ በሚሰማበት ቀን በቀረበዉ ማመልከቻ ላይ የተገለፀዉን አቤቱታ እዉነተኛነት ፍርድ ቤቱ ይመረምራል፡፡ ስለማስረጃዉም ተገቢ መስሎ የታየዉን ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ አመልካቹ የተያዘዉ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ መሆኑን ፍርድ ቤቱ ከተረዳዉ ወዲያዉኑ እንዲለቀቅ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ የዚህ ዓይነት ትዕዛዝ ከፍርድ ቤት ከተሰጠ በኋላ ማናቸዉም ሌላ ትዕዛዝ እንዲኖር ሳያስፈልግ የፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ብቻ በቂ ሆኖ መፈፀም አለበት፡፡ በሌላ በኩል ማመልከቻዉ ላይ የተገለፀዉ የአቤቱታ ቃል በማናቸዉም ሁኔታ ለፍርድ ቤቱ የሚያጠራጥር መስሎ የታየዉ እንደሆነ አቤት ባዩ ዋስ ጠርቶ እንዲለቀቅ ሊያዝ ይችላል፡፡ ይህ ዋስትና የገንዘብ ማስያዝ ወይም የሰዉ ዋስ ሊሆን ይችላል፡፡ በዋስትናዉም የሚገባዉ ግዴታ እንዲለቀቅ ያደረገዉ ፍርድ ቤት በፈለገዉ ጊዜ እንዲቀርብ ወይም ማንኛዉንም ፍርድ ቤቱ የሚሰጠዉን ትዕዛዝ አክብሮ እንዲፈፅም የሚያስገድድ ይሆናል ፡፡

ማጠቃለያ

አካልን ነፃ ማውጣት (Habeas Corpus) የሰዎች ሰብአዊ ነፃነት በህገወጥ መንገድ እንዳይጣስ ለመከላከል አስፈላጊ የሆነ ሥርዓት ሲሆን በሀገራችንም የህግ ጥበቃ ያለው መሆኑን በመረዳት ህብረተሰቡ ከህግ ውጪ የሆነ መያዝ ወይም መታሰር ሲያጋጥመው ይህን ህጋዊ መፍትሄ በመጠቀም መብቱን በማስከበር እና ህገወጥነትን በመካላከል የበኩሉን ሊወጣ ይገባል፡፡

ፍትህ ሚኒስቴር ትምህርት ክፍል

law
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በግለሰቦች ላይ ጥናት በማድረግ የዘረፋ ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ዋሉ
“በሶማሊያ የውጭ ሃይላት የጦር መሣሪያ አቅርቦት ሀገሪቷ በአሸባሪዎች እጅ ላይ እንድትወድቅ በር ይከፍታል”
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2