ወደ ስልጣን ከመጣ ከአጭር ጊዜ በሁዋላ የተቀነባበረ የጥላቻ ዘመቻ እየወረደበት፣ ከየአቅጣጫው ጦርነት የሚከፈትበት፣ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በማበር ጥቃት የሚሰነዘርበት፣ ሆን ተብሎ ህዝብን በማጎሳቆል፣ በመግደል፣ በማፈን፣ በማፈናቀል ወዘተ ምሬት ውስጥ በመክተት እንዳይረጋጋ ሁሉም ዓየነት ሴራ የተሸረበበት መንግስት ተግባሩ ከሚባለው የተለየ እንደሆነ በርካቶች እየተረዱ መሆናቸው እያደር እየተሰማ ነው።
የምንግስትን ጥላቻና የአገርን ጉዳይ ቀላቅለው ለጠላት ያደሩ በግልጽ ከግብጽ፣ ከሻዕቢያ፣ ከፈራረሰችውና ኢትዮጵያ ከምትጠብቃት ሶማሊያ ጎን ቆመው አገራቸውን ለማፍረስ ሌት ተቀን በሚደክሙበት ወቅት፣ ሁሉንም እንደ አመጣጡ በመመለስ ከነጥፋቱም ቢሆን መንግስት በርካታ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ማከናወኑን መካድ አይቻልም።
ሰሞኑንን ኢትዮጵያ የጸረ ረሃብ ትግል ማስተባበሪያ ፣ የዓለም የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤን ስብሰባ ከማስተናገዷ በተጨማሪ፣ ለወትሮው ሲያሟርቱባት የነበሩት የዓለም የገንዘብ ተቋማት የተቀማጭ የውጭ ምንዛሬ መጠን 1.3 ቢልዮን ዶላር መድረሱን ይፋ መስክረዋል። ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ስምንት መቶ ሚሊዮን የሚሆን ዶላር ማበደሯና የብድሩ ስትራቴጂካዊ አካሄድን ከቀጠናው ፖለቲካ አንጻር ድንቅ አካሄድ መሆኑ ተሰምቷል። ይህ ብቻ አይደለም ኢትዮጵያ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሚያደርጋትን ኤ350-1000 ተረክባለች።
እነዚህ የሳምንቱ ታላላቅ ክስተቶች ከዜና ያለፈ ትርጉም ያላቸው ቢሆንም ጥላቻና ተቃውሞ ላይ የተመሰረቱ ጭፍን ሚዲያዎችና ፖለቲከኞች ቢያንስ ለታሪክ ሲሉ ዜናውን በቀናነቱ አላሳዩም። ይልቁኑም ” ምን ያደርጋል” ነው ያሉት።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን ኤ350-1000 “Ethiopia land of origins” የሚል ስያሜ የተሰጠውን የመንገደኞች አውሮፕላን ዛሬ ከኤር ባስ የአውሮፕላን ኩባንያ ተረክቧል ። የአውሮፕላኑ ዘመናዊነትና ኢትዮጵያ የአውሮፕላኑ ብቸኛ ባለቤት የአፍሪካ አገር ከመሆኗ ባሻገር የአውሮፕላኑ ስያሜ ኢትዮጵያ የፍጥረት መጀመሪያ መሆኗን የሚያበስር መሆኑ አገራቸውን ለሚወዱ ልዩ ስሜት ፈጥሯል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ሰሞኑን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ ሲሰጡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አንድ መቶ ሃይ አራት አውሮፕላኖችን ለመግዛት ውል ማድረጉን ወይም ተዕዛዝ መስተቱን አስታውቀው ነበር። በዚህ ለሕዝብ ክፍት በሆነው ንግግራቸው ኢትዮጵያን በልኳ ከፍ የማድረግ ጉዳይ ለአፍታም ወደሁዋላ እንደማይባል የተረሱ ቤተመንግስቶችን በማደስና ታሪክን እንደታሪክነቱ ማጉላት የመንግስታቸው ቀዳሚ ተግባር እንደሆነ በተግባር የሚታዩ ጅማሮዎችን በመዘርዘር አብራርተው ነበር።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመት እስከ አንድ መቶ ሰላሳ ሚሊዮን መንገደኞችን ማስተናገድ የሚችል ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት እንቅስቃሴ መጀመሩም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብስረዋል። ይህን ተከትሎ ቀናት ሳይቆጠሩ ኤ350-1000 ኤር ባስ ኢትዮጵያ መግባቱ ይፋ ሆኗል። “ኢትዮጵያን የሚያሳንሱ፣ ኢትዮጵያን ለማፈራረስ የተነሱ፣ ኢትዮጵያን የሚጠሉና ጸሯ ናቸው ወዘተ.” በሚል ዘመቻ የማይላያቸው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይና መንግስታቸው በዚህ ጉዳይ እንኳን ከተቃዋሚዎች በግልጽ ምስጋና አላገኘም።
በሳምንቱ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ስምንት ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን በአራት አመት እፎይታ ጊዜ በአስር ዓመታት ተከፍሎ የሚጠናቀቀው ከ738 ሚሊየን ዶላር በላይ ማበደሯ፣ ይህ ብድር ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ብድር በመስጠት እንድትጠራ የሚያደርግ ብቻ ሳይሆን ከብድሩ ጀርባ ያለውን ፖለቲካዊና ስላታዊ ጠቀሚታ በማንሳት አካሄዱን በአገር ጥቅም አስልተው ምላሽ የሰጡ ፖለቲከኞችም ሆኑ ሚዲያዎች የሉም። ይህን አካሄድ አገራቸው የሚወዱ “ድንቁርናና በጭፍን ምክንያት አልባ ጥላቻ የመነዳት ውጤት” ሲሉት ተደምጠዋል። የብድር አመላለሱም በካሽ እና በድፍድፍ ነዳጅ እንደሚሆን ተመልክቷል።
ከዚህም ሌላ የዓለም ዓቀፉ የገንዘብ ድርጅት የኢትዮጵያ የምንዛሬ ክምችት ከተገመተው ልቆ መገኘቱን ይፋ ያደረገው በዚሁ ሳምንት ነው። “IMF raises Ethiopia’s international reserves target after first review” ገንዘብ ተቋሙ ጠቅሶ ኤፒ እንደዘገበው ከሆነ The net international reserves stood at $1.3 billion in mid-August, more than double the target of $630 million, the Fund said. የአገሪቱ የምንዛሬ ክምችት በአኦግስት አጋማሽ ይሆናል ተብሎ ከታቀደው 630 ሚሊዮን ዶላር በእጥፍ ልቆ 1.3 ቢሊዮን መድረሱን አድንቆ ይፋ አድርጓል። ይህ ዜና በምንዛሬ እጥረት ስጋት ሳምንትና ቀናትን ሲቆጥሩ ለነበሩ ሁሉ መላክም ብስራት ቢሆንም ያነሳው የለም።
የኢትዮጵያ ዕዳ የአገሪቱን አጠቅላይ ሃብት ውጦ መበደር የማይቻልበት ደረጃ ደርሶ ከነበረበት ታሪያ ወርዶ ወደ ሁለት ዕቅድ መውረዱ ዜና የማይሆንባት ኢትዮጵያ አሁንም ” “Ethiopia land of origins” በሚል ስያሜ መንግስት አየር መንገድን ይበልጥ ኃያል ለማድረግ ያስገባውን አውሮፕላን ጉዳይ ዜናቸው ያላደረጉ ” ይህ ኢትዮጵያን ሊያጠፋ የተነሳ መንግስት ” እያሉ ይወቅሳሉ።
ይህም የኢትዮጵያ አየር መንገድን በአፍሪካ ትልቁ የአውሮፕላን ባለቤት ብቻ ሳይሆን ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ያለው ተቋምም የሚያደርገውን የኤ350-1000 የመንገደኞች አውሮፕላንን ዋና ስራ አስፈሳሚው አቶ መስፍን ጣሰውና የቦርድ ሰብሳቢው ሌተናል ጄነራል ይልማና መርዳሳ ከልዑካን ቡድናቸው ጋር በመሆን ከፓሪስ እየተምዘገዘጉ ሽንጣሙን አውሮፕላን አዲስ አበባ ሲያስገቡ፣ እኒሁ ጥላቻ ያሳወራቸው ሚዲያዎችና ፖለቲከኞች አሁንም በተቃውሞ ነው ዜናውን ያጀቡት።

በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ የአየር መንገዱ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ፣ በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲ ለሚክ የኤር ባስ ኩባንያ ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጄነራል ይልማና መርዳሳ ፣ ኢትዮጵያ አጠቃላይ ሀገራዊ ሪፎርም ላይ መሆኗን አንስተዋል ።
በአፍሪካ የመሪነት ሚናውን ድርሻ እየተወጣ ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአህጉሪቷ ኢኮኖሚ ትስስርን በመፍጠር የማይተካ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል።
አየር መንገዱ ዛሬ ከኤር ባስ ኩባንያ የተረከበውና በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኤ 350_1000 አውሮፕላንም ለአየር መንገዱ ቀጣይ እድገት ትልቅ ስኬት መኾኑን ገልጸዋል ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፣ የኤ350-1000 አውሮፕላን ወደ ገበያው መግባት አየር መንገዱ የተያያዘውን ፈጣን እድገት በላቀ ደረጃ ለማሳለጥ ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን አንስተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ አዳዲስ አውሮፕላኖችን በማስገባት ፈር ቀዳጅ መኾኑን በማንሳት፣ ኤ 350-1000 አውሮፕላንም በአየር መንገዱ ታሪክ ትልቅ ስኬት መሆኑን አክለዋል።
የኤር ባስ ኩባንያ ዓለም አቀፍ ዋና ስራ አስፈጻሚ ውተር ቫን ዌርሰች በበኩላቸው ይህ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኤ350_1000 አውሮፕላን ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ራዕይ 2035 ስኬት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ገልጸዋል ። ኢዜአ እንደዘገበው በቀጣይ ጊዜያትም ኩባንያው ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በትብብር ለመሥራት ትልቅ ፍላጎት አለው ብለዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤ350-900 አውሮፕላኖችን ተረክቦ መሥራት ከጀመረ ሰባት ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም 20 ኤ350-900 አውሮፕላኖች በሥራ ላይ ይገኛሉ።
በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኤ350-1000 የመንገደኞች አውሮፕላን ከፈረንሣይ ቱሉስ ተነስቶ ኢትዮጵያ በመግባቱ በርካቶች ደስታቸውን ገልጸዋል። ምስሉን በመቀባበል በማህበራዊ ገጻቸው አሰራጭተዋል።

