Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የኦሮሚያ ክልልና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በይፋ ዕርቅ አወረዱ ፤ የስምምነቱ ፊርማ ለኦሮሚያም ሆነ ለኢትዮጵያ ሰላም “ቁልፍ ጉዳይ” ተብሏል
News

የኦሮሚያ ክልልና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በይፋ ዕርቅ አወረዱ ፤ የስምምነቱ ፊርማ ለኦሮሚያም ሆነ ለኢትዮጵያ ሰላም “ቁልፍ ጉዳይ” ተብሏል

Ethioreview newsEthioreview news—December 1, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ከፍተኛ አመራር የነበሩት ጃል ሰኚ ነጋሳ ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ የሰላም ስምምነት ተፈራረሙ። ጃል ሰኚ ነጋሳ መንግሥት ያቀረበላቸውን የሰላም ጥሪ በመቀበል ነው ከአቶ ሽመልስ አብዲሳ ጋር የሰላም ስምምነቱን የፈረሙት፡፡

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት፣ የሰላም ጥሪውን ተቀብለው ለስምምነት የመጡትን አመስግነዋል።

“ከጦረኞች በላይ ጦርነትን የሚያባብሱት ስለጦርነት የማያውቁ ናቸው” ያሉት ፊልድ ማርሻሉ፣ “እኔ ካለኝ ልምድ አንፃር ጦርነት ጎጂ በመሆኑ የሰላምን መንገድ መርጣችሁ በመምጣታችሁ ልትመሰገኑ ይገባል” ብለዋል። ይህ አይነቱ ተግባር በሌሎች አካባቢዎችም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በመገለጽ ጥሪ አሰምተዋል።

አቶ ሽመልስ በበኩላቸው የኦሮሞ ሕዝብ በባህሉ መሰረት “ሰላም ይውረድ ብሎ ያቀረበውን ጥሪ ተቀብላችሁ በመምጣታችሁ በክልሉ መንግሥት ስም አመሠግናለሁ” ብለዋል። መከላከያ ሠራዊቱ ለሰላም ስምምነቱ ላበረከተው አስተዋፅኦም አቶ ሽመልስ አመሥግነዋል፡፡

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

የፖለቲካ ልዩነት ያለና ተፈጥሯዊ መሆኑን ያወሱት ጃል ሰኚ ነጋሳ፣ “እኛም ያለንን የፖለቲካ ልዩነት በጠመንጃ ከመፍታት በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት ወስነን ነው ስምምነቱን የመረጥነው” ብለዋል። ስምምነቱ ለኦሮሞ ሕዝብ ትልቅ እፎይታን እንደሚሰጥም በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡

በኦሮሚያ ክልል መንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል የተፈረመው የሰላም ስምምነት በኦሮሞ ሕዝብ የፖለቲካ ትግል ታሪክ ውስጥ ታላቁ ምዕራፍ መሆኑን አቶ ሽመስል በግል ማህበራዊ ገጻቸው አመልክተዋል።

አቶ ሽመልስ፣ የለውጡ መንግሥት የሰላም እጦት እና ለሕዝብ ስቃይ ምንጭ የሆነውን የፖለቲካ ልዩነት በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት በማይናወጥ ቁርጠኝነት ሲንቀሳቀስ እንደነበር አስታውሰዋል።

የኦሮሞ ልሂቃን፣ አባገዳዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ሀደ ሲንቄዎች እና የኦሮሚያ ሰላም ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ወገኖች ሁሉ፣ በተለይም ደግሞ ሰፊው የኦሮሞ ሕዝብ ልዩነቶች በሰላማዊ መንገድ መፍትሔ እንዲያገኙ በተደጋጋሚ ሲጠይቁ እንደነበርም ጠቅሰዋል።

ይህንኑ መሠረት በማድረግ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊትም የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ለሰላማዊ ውይይት ላለው ቁርጠኝነት እውቅና በመስጠት እና የባለድርሻ አካላትን የሰላም ጥሪንም በመቀበል ሕዝቡ የገባበት ስቃይ እንዲያበቃ ተቋርጦ የነበረውን የሰላም ውይይት ዳግም በመጀመር በዛሬው ዕለት ታሪካዊ ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል።

አቶ አደም ፋራህ

ባለፉት አመታት በሀገራችን የትኛውም የፖለቲካ ልዩነት በንግግር እንጂ በአፈሙዝ እንደማይፈታ በተደጋጋሚ ታይቷል – አቶ አደም ፋራህ

ኦቢኤን ሣይበር ሚዲያ ህዳር 22፣2017- ባለፉት አመታት በሀገራችን የትኛውም የፖለቲካ ልዩነት በንግግር እንጂ በአፈሙዝ እንደማይፈታ በተደጋጋሚ ታይቷል ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ።

አቶ አደም በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ክንፍ ከፍተኛ አመራር ጃል ሰኚ ነጋሳ መካከል በዛሬው እለት የተፈረመው የሰላም ስምምነት እጅግ ሊበረታታ የሚገባውና እንደ ሀገር ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ለምናደርገው ጥረት ከፍተኛ አስተዋኦ የሚያበረክት ነው ብለዋል።

እንደ ብልፅግና ፓርቲ ሰላም ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ተገንዝበን እራሳችንን ለንግግር፣ ለድርድር እና ለትብብር ክፍት አድርገናል ሲሉም በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።

ህብረተሰባችን በተደጋጋሚ የሚያቀርባቸው የህግ የበላይነት መከበር ጥያቄዎች በምሉዕነት እንዲመለሱ ለማድረግም የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ ጥረቶችን ይበልጥ አጠናክሮ መሄድ እንደሚገባ እናምናለን ብለዋል።

ባለፉት አመታት በሀገራችን የትኛውም የፖለቲካ ልዩነት በንግግር እንጂ በአፈሙዝ ኃይል በዘላቂነት ሊፈታ እንደማይችል በተደጋጋሚ ታይቷል ሲሉም ገልጸዋል።

በመሆኑም በየትኛውም የሀገራችን ክፍል የሚገኙ ታጣቂዎች አሁንም ቢሆን የተሻለው አማራጭ ሰላማዊ መንገድ መሆኑን ተገንዝበው በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ ምርጫቸው እስካደረጉ ድረስ እንደ ብልፅግና ፓርቲ የሚጠበቅብንን ድርሻ ለመወጣት ሁሌም ዝግጁ መሆናችንንም ጭምር በዚህ አጋጣሚ ለመግለፅ እወዳለሁ ብለዋል።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Chad ends a defense cooperation agreement with France, its former colonial ruler
“አህያም ካናፋ በኛ ቤት ዘፈን ነው” የኢሳያስ ስላቅ “ኤርትራ በፍፁም ኢትዮጵያ ያለመረጋጋት ውስጥ ገብታ የማየት ፍላጎት የላትም”
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2