Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ሰነድ አልባ ስደተኞች ላይ የታውጀው የትራምፕ አዋጅና የኢትዮጵያዊያን ስጋት እንዴት ይታያል?
News

ሰነድ አልባ ስደተኞች ላይ የታውጀው የትራምፕ አዋጅና የኢትዮጵያዊያን ስጋት እንዴት ይታያል?

Ethioreview newsEthioreview news—January 28, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በአሜሪካ ባለፈው ሳምንት በተጀመረው አሰሳ ሰነድ አልባ ስደተኞች የሆኑ ስደተኞች በሙሉ በቁጥጥር ስር እንደሚውሉ ማዘዛቸውን የስደተኞች ጉዳይ ኃላፊው ቶም ሆማን ተናግረዋል።

ሰነድ አልባ ስደተኞች የሚባሉት የትኞቹ ናቸው? በሚል የጠየቅናቸው በአሜሪካ የሕግ ባለሙያ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ፕሮፌሰር ሔኖክ ጋቢሳ የጥገኝነት ጉዳያቸው በየትኛውም የአሜሪካ መንግሥት ተቋም የማይታወቁትን መሆኑን ይናገራሉ።

“በመደበኛ ፍርድ ቤትም ይሁን የስደተኞችን ጉዳይ በሚመለከተው ፍርድ ቤት እየታየ ያለ ጉዳይ የሌላቸው ስደተኞች ሰነድ አልባ ስደተኞች በሚለው ውስጥ የሚካተቱ ናቸው።”

ዩኤስ ሲቲዝንሺፕ ኤንድ ኢሚግሬሽን ሰርቪስ (ሲአይኤስ) የሚባለው በአሜሪካ ለጥገኝነት ጥያቄ የሚያቀርቡ ሰዎችን ጉዳይ በመመልከት ፈቃድ የሚሰጠው እና የሚከለክለው ተቋም ጉዳያቸውን ያልያዘ ሰዎችም ሰነድ አልባ በሚለው ውስጥ ይገኙበታል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ስለዚህም ፕሮፌሰር ሄኖክ “ከአሜሪካ መንግሥት ኤጀንሲዎች ጋር የሚያገናኛቸው ጉዳይ የሌላቸው ስደተኞች አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ናቸው” ይላሉ።

በፍርድ ቤት ከአሜሪካ እንዲወጡ ትዕዛዝ የተላለፈባቸው እና “እዚህም እዚያም እየተደበቁ የሚኖሩ” አልያም በፍርድ ቤት ቀጠሮ ያልሰጣቸው እንዲሁም ወደ ፍርድ ቤት ጉዳያቸውን የመውሰድ ዕድል የሌላቸው ሰዎችም ይህ የማባረሩ እርምጃ ይመለከታቸዋል።

በፍርድ ቤት ጉዳያቸው እንዲታይ ቀጠሮ በማስያዝ ወይም የቀጠሮ ቀን በመጠባበቅ ላይ ያሉት ግን አስጊ ሁኔታ ውስጥ እንዳልሆኑ በአሜሪካ የሕግ ባለሙያ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ፕሮፌሰር ሔኖክ ያስረዳሉ።

የስደተኞችን ጉዳይ በፍርድ ቤት የሚከታተሉት ባለሙያው አሰሳ እና ጅምላ እስር እየተከናወነ መሆኑ ያስደነገጣቸው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች “ሁሉም ሰው በፖሊስ ተይዞ ወደ አገር ቤት የሚወረወር መስሏቸው ፈርተው ነበር” ይላሉ።

ሆኖም ግን ይሄ እንደማይሆን ባለሙያው ያስረዳሉ። “ማንንም ሰው መንገድ ላይ አቁሞ መጠየቅ አይቻልም። ይሄ በቆዳ ቀለም ሰዎችን ዒላማ ማድረግ (racial profiling) ነው። ወንጀልም ነው” ሲሉ ያስረዳሉ።

አሰሳውን እና እስሩን እያካሄዱ ያሉት አካላት በአሁኑ ጊዜ እርምጃ እየወሰዱ ያሉት ሰነድ አልባ ስደተኞች ይገኙባቸዋል ተብለው ቀደም ሲል በተለዩ የሥራ ቦታዎች እና ማንነታቸው ተለይቶ በሚፈለጉት ላይ መሆኑን ሪፖርቶች ያመለክታሉ።

የትራምፕ ውሳኔዎች የስደተኞችን ሒደት ያጓትታል?

ትራምፕ የስደተኞችን ጉዳይ የሚከታተሉ የፍርድ ቤት ሠራተኞችን ማባረራቸውና በኃላፊነት የሾሟቸው ባለሥልጣኖችም በስደተኞች ጉዳይ እንደእሳቸው ዓይነት ተቋም ያላቸው መሆኑ ብዙዎችን ያሰጋ ነው።

ይህ ውሳኔ ጥገኝነት የመጠየቅ ሒደትን ሊያጓትት ይችላል? በሚል የተጠየቁት የሕግ ባለሙያ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ፕሮፌሰር ሔኖክ እንደሚሉት፣ የስደተኞች ጉዳይን የሚከታተሉ ዳኞች እና ባለሙያዎች መባረራቸው የስደተኞች ፍርድ ቤት ላይ የሚወሰኑ ውሳኔዎችን ማስወገጃ መንገድ ነው። “ሒደቱ ይጓተታል። የስደተኞች ጉዳይ ፍርድ ቤት በጣም የሚጓተትም ይሆናል” ሲሉ ያስረዳሉ።

የስደተኞችን ጉዳይ የሚከታተሉ ፍርድ ቤቶች ሠራተኞች መባረር የፍርድ ቤቶች በሚመለከቷቸው ጉዳዮች የመጨናነቅ ሁኔታ እንዲፈጠር እና የፍርድ ቤት ቀጠሮዎች እስከ ዓመት እና ከዚያ በላይ እንዲዘገዩ እንደሚያደርግ ያክላሉ።

ሆኖም ግን ይህ ሁኔታ ስደተኞች ጉዳያቸውን በፍርድ ቤት የማቅረብ መብታቸውን በፍትሕ የመዳኘት መብታቸውን መንጠቅ እንደማይቻል ያስረዳሉ።

ስደተኞች ወደሌሎች ግዛቶች ‘መሸሽ’ ይችላሉ?

አሰሳና የጅምላ እስር ከተካሄደባቸው ግዛቶች አንዱ በሆነው ቺካጎ ከንቲባ የሆኑት ብራንደን ጆንሰን ሰዎች የታሰሩት በስደተኞች ጉዳይ ተቋም እንጂ በቺካጎ ፖሊስ እንዳልሆነ ገልጸው፣ ሰዎች መብታቸውን እንዲያውቁም አስታውሰዋል።

ወታደራዊ አገልግሎት የሰጡ ሰዎችን ጨምሮ ሰነድ አልባ ነዋሪዎች እና ዜጎች በአሰሳው መያዛቸውን የገለጹት የኔዋርክ ከንቲባ ራስ ባራካ በበኩላቸው “ሰዎች በሕገ ወጥ መንገድ ሲሸበሩ ኔዋርክ ዝም ብላ አታይም” ብለዋል።

አንዳንድ የአሜሪካ ግዛቶች ስደተኞች የፌደራል መንግሥትን አሰሳ እና የጅምላ እስርን በመሸሽ እነሱ ጋር ከለላ እንደሚያገኙ አስታውቀዋል።

የሕግ ባለሙያ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ፕሮፌሰር ሔኖክ እንደሚሉት፣ የፌደራል መንግሥት “የተወሰነ ሥልጣን ነው ያለው። ከአንድ ግዛት ግለሰቦችን የመውሰድ መብት የለውም”።

የግዛቶች ሉዓላዊነት የተጠበቀ እንደሆነ በመጥቀስ፣ የፌደራል መንግሥትን ድጎማ አንፈልግም ብለው ከለላ የሚሰጡ ግዛቶች (sanctuary states) በአሜሪካ ይገኛሉ።

“አንድ ስደተኛ ከአንድ ግዛት ወደ ሌላው ሲሄድ የግዛት መታወቂያ ብቻ ሳይሆን የፌደራል መታወቂያ መያዝ ያስልጋል የሚል ሕግ ወጥቷል። ስለዚህ ከአንድ ግዛት ወደ ሌላው ሲሄዱ ችግር ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ። ሆኖም ግን ከለላ በሚሰጡ ግዛቶች መኖር ይችላሉ” ሲሉ አብራርተዋል።

በእነዚህ ግዛቶች መኖር ቢቻልም የስደተኞችን ጉዳይ የሚመለከተው የፌደራል መንግሥት ስለሆነ ግዛቶች “በስደተኞች ጥያቄ ጉዳይ መፍትሔ መስጠት” እንደማይችሉ ባለሙያው ያስረዳሉ።

እነዚህ ግዛቶች ሠራተኛ በመፈለግ፣ በሰብአዊነት ተቆርቁረው አልያም ከፌደራል መንግሥት ጋር ባላቸው የፖለቲካ ልዩነት ለስደተኞች ከለላ ሊሰጡ ይችላሉ።

የትራምፕ አሜሪካ ለስደተኞች ምን ትመስላለች?

የትራምፕ ዳግም ወደ ሥልጣን መመለስን ተከትሎ በአሜሪካ ውስጥ ያሉ ያልተመዘገቡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞች በአሁኑ ጊዜ ጭንቅ ውስጥ ገብተዋል።

ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት ስደተኞችን በወንጀለኝነት እና በሕብረተሰቡ ውስጥ ፍርሃትን በሚፈጥር ሁኔታ በመፈረጅ የሚያደርጓቸው ንግግሮች፤ ለዘመናት የዘለቀውን የአሜሪካንን ጥገኝነት ጤኣቂዎች ተቀባይነት ዝና የሚቀይር ነው።

ይህ በቀጣይ አራት የትራምፕ የሥልጣን ዘመን የሚቀጥከው ስደተኞችን የማሻደድ እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይመስላል።

ፕሮፌሰር ሄኖክም “በጣም እርግጠኛነት የጎደለው እና አስፈሪ ይሆናል” ሲሉ ቀጣዩን የትራምፕ አራት የሥልጣን ዓመታትን ይገልጻሉ።

ሆኖም ግን ተስፋ እንደማይቆርጡ እና የሚለወጡ ነገሮች እንሚኖሩ “በአገሩ [አሜሪካ] እተማመናለሁ” ሲሉም ሊኖር የሚችለውን ተስፋ ይጠቅሳሉ።

“ፕሬዝዳንት ትራምፕ ዛሬ አይደለም የመጡት። ከሥልጣን ሲወርዱ የአገሪቱ ዴሞክራሲ ቀጥሏል። አሜሪካ የ250 ዓመት ልምድ ያካበተች ነች። ዛሬ ላይ ተነስቶ የሚቀየር የለም” ይላሉ።

ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ቀናት አርብ 538፣ ቅዳሜ 593 እና እሑድ 286 ሰዎች በጅምላ ተይዘዋል።

በጆ ባይደን የአራት ዓመታት አስተዳደር ዘመን ከአሜሪካ ተባረው ወደ አገራቸው የተመለሱ 1.5 ሚሊዮን ስደተኞች ናቸው።

ዘገባው ከቢቢሲ የተወሰደ ነው

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ዳግም ከተመዘገቡ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መስፈርቱን ያሟላ የለም
የትግራይ የስልጣን ጥመኞች የሚቆምሩበት ሕዝብ “ማሾ” እንደ ማሳያ – የትህነግ ሃፍረት
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2