ሰሞኑንን ትጥቅ አንስተው በየአቅጣጫው ሲታኮሱ ከነበሩት መካከል የሚታወቁትን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸው ታጣቂዎች “ወደ ሰላም መንገድ መጥተናል” ሲሉ ተድምጧል። በቪዲዮ እንደታየው ወደ ካምፕ እየገቡ ያሉት ታጣቂዎች ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ይህንኑ ተከትሎ የሚሰጡ አሉታዊና አዎንታዊ አስተያየቶች እየተደመጡ ነው። ለማጣጣል የሚምክሩም አሉ። ኢትዮቲቬው እንደሰማችው በቅርቡ ምንአልባትም በቀናት ልዩነት የሚታውቁ የጥጥቅ ትግል መሪዎች ከነኃይላቸው ይገባሉ።
መጀመሪያ ጃል ሰኚ ማን ነው?
ጃል ሰኚ ምዕራብ ሸዋ የጊንጪ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ነበር። በድርጅት የኦሮሞ ፌደራል ኮንግረንስ አባል የነበረና የፕሮፌሰር መራራ የትግል ልጅ ነው። በ1997 ምርጫ ወቅት ዕድሜው 19 ስለነበር በምዝገባ ናራዘሚያ የመጨረሻ ቀን ዕድሜው ከመታወኢያው ላይ ተፍቆ 21 ከተደረገ በሁዋላ ዕጩ ተወዳዳሪ የሆነ የወቅቱ ጎረምሳ ነበር።
በተወዳደርበት የክክል ምርጫ አሸንፎ የጨፌ ኦሮሚያ ምክር ቤት አባል ሆነ። ብዙም ሳይቆይ ክትትሉና ማሳደዱ ሲበዛበት፣ በሰላማዊ መነገድ መታገል ስላልቻለ፣ በባህሪውም ዕልኸኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ “ዱር ቤቴ” ካለው ኦነግ ጋር ተቀላቀለና ወታደራዊ ስልጠና ወሰደ። የሚያውቁት እንደነገሩን ሰልጥኖ ትግል ውስጥ ከገባ በሁዋላ ድርጅታዊ ስራውን እየሰራ ሳለ በጥቆማ ተይዞ ታሰረ።
በ2010 ለውጥ ሲመጣ እንደ በርካቶች ምህረት ተደርጎለት ከዝዋይ ማረሚያ ቤት ወጣ። በምህረት ከተለቀቀ በሁዋላ ኦፌኮን ትቶ ከኦነግ ጋር ቀጠለ። አፍታም ሳይቆይ የመካከለኛው ኦሮሚያ የጦር መሪ ሆኖ ተሾመ። አሁንም የሚያውቁት እንደሚያስረዱት ከሆነ ጃል ሰኚ ተራ ዝርፊያን፣ ህዝብን ማስጨነቅና እያገቱ ገንዘብ የሚደራደሩትን ይቀጣ ነበር። አምቦ ዙሪያ በኦነግ ስም ታጣቂ ነን እያሉ ህዝብ ሲያማርሩ በነበሩ ላይ ህዝብ ፊት እርምጃ እንዲወሰድ ያደረገው የሱ አመራር እንደሆነ ይመስክራሉ።

ጃል ሰኚ እያደር ከጃል መሮ ጋር መግባባት አቅቶት በገሃድ መለየቱን ራሱ እስካስታወቀ ድረስ መንግስት “ሸኔ” ንየሚልው እነሱ ደግሞ የኦሮሞ ነጻ አውጪ ጦር የሚሉት ታጣቂ ክንፍ ስር አመራር የሚቀበልና የሚፈጽም ሹመኛ ነበር። በዚህም ኃላፊነቱ በውጭ ያሉ ሚዲያዎች፣ የድርጅቱ ልሳኖችና ደጋፊዎች ዘንዳ በሰላም ለመታገል መግባቱ ይፋ እስከሆነበት ቀን ድረስ “ጀግና” እየተባለ የሚወደስ እንደነበር ይታወሳል።
ጃል ሰኚ ወደ ሰላማዊ አግብባብ መመለሱን ተከትሎ በኦሮሚያ የፖለቲካው ጡዘት መረገቡን በርካቶች እያስታወቁ ነው። ኢትዮሪቬው እንደሰማችው የነ ጃል ሰኚን እግር ተከትለው ታዋቂ የኦነግ ሰራዊት አመራሮች ወደ ሰላማዊ ትግል መንገድ ሊመጡ ጫፍ ደርሰዋል። መረጃውን ያካፈሉት እንዳሉት ለጊዜው ስማቸውን የማይጠቅሷቸው ታዋቂ የኦነግ ሰራዊት አመራሮች ሃያላቸወን ይዘው የገባሉ።
በኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን በአማራ ክልልም ሰሞኑንን እየገቡ ካሉት ቁጥራቸው ሰፊ የሆነ የፋኖ ታጣቂዎች በተጨማሪ የሚገቡ እንዳሉ ዝግጅት ክፍላችን ሰምቷል። እነዚህ ታጣቂዎች ከወዲሁ ጅጃይላቸውን ከሚያዟቸው መሪዎች ለይተው ንግግር ላይ እንደሆኑ ነው የተሰማው። እነዚህ ጎጃምን ጨምሮ በሶስት አቅጣጫ ወደ ሰላም ለመግባት እየተነጋገሩ ያሉት የፋኖ ታጣቂዎች ወደ ሰላማዊ ትግሉ ሲገቡ፣ ጎጃምን ሙሉ በሙሉ ነጻ ለማድረግና በፋኖ ህኃይሎች የተያዙትን አካባቢዎች የማጽዳት ዘመቻ ለአጭር ቀናት እንደሚደረግ ተሰምቷል።
ሰሞኑንን በአማራ ክልል ከሰሜን ወሎ፣ ከደቡብ ወሎ ፣ ከሰሜን ሸዋ ፣ ከዋግኸምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር፤ ከደሴ፤ ኮምቦልቻና ወልድያ ከተሞች እንዲሁም ከኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር የተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ የነበሩት የታጠቁ አካላት ወደ ሰላማዊ መንገድ መመለሳቸውን ጠቅሰው ሲናገሩና ወደ ተሃድሶ ጣቢያ ሲገቡ በፊልም የተደገፈ መረጃ መሰራጨቱ ይታወሳል።
በተመሳሳይ ጭልጋ ሰራባ ካምፕ ለተሃድሶ ስልጠና ትጥቃቸውን እያስረከቡ አቀባበል ሲደረግላቸው የታዩት የአፋኖ ታጣቂዎች ቁጥር ከዚህ ቀደም ከታየው ሁሉ በርክታ ነው።
በኦሮሚያና በአማራ ክልል ሰፊ ቁጥር ያላቸው ታጣቂዎች እጅ መስጠታቸውን ተከትሎ “አንድም ሰው ቢሆን መሳሪያ ያነገበ ወደ ሰላም መንገድ መምጣቱ ሊደነቅና ሊበረታታ ይገባል፤ ይህ እንዲሆን ያደረጉም ምስጋና ያስፈልጋቸዋል። ሌሎችም በተመሳሳይ እንዲመጡ ግፊትና ጫና ያስፈልጋል” በማለት የሚያበረታቱ እንዳሉ ሁሉ፣ የሚታየውና የሚሰማው ሁሉ ተራ ፕሮፓጋንዳ መሆኑን በመግለጽ እያጣታሉ ያሉም አሉ።
ሁለቱም ወገኖች የያዙት አቋም እንዳለ ሆኖ በቀጣይ ከአማራና ኦሮሚያ ጫካ በርካቶች ከመሪዎቻቸው ጋር ወደ ሰላማዊ መነገድ እንደሚመለሱ ዜናውን ያጋሩን አረጋግጠዋል።

ይህን ተከትሎ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲያፈርሱ ታጠቀው በተለያዩ የአማራና ኦሮሚያ የተሰማሩትን ሲያስለጥን፣ ሲያስታጥቅና በውክልና ገንዘብ ሲሰጥ የነበረው ሻዕቢያ ” ወራጅ አለ” ሊል እንደሚችል ማስፈራሪያ መላኩ ተሰምቷል።
መረጃው ያላቸው የዜናው ባለቤቶች ለአዲስ አበባ ተባባሪያችን እንዳሉት ከሆነ፣ ሻዕቢያ ወደዚህ ውሳኔ ያመራው የሸኔ ኃይል እየፈረሰ መሆኑና አማራ ውስጥ ያለው እንቅስቃሴ በሚፈለገው መጠን ሊሄድ ባለመቻሉ ነወ።
ሻዕቢያ ከአማራ ኃይሎች ጋር የያዘው ዕቅድ ባለፉት ስድስት ወራት የሚጠናቀቅ እንደሆነ ታሳቢ ተደርጎ ነበር። በውክልና የሚያገኘውን ከፍተኛ በጀትና ትጥቅ አስገብቶላቸው እንደታሰበው ባለመፈጸማቸው፣ ይልቁኑም እጃቸውን ለመንግስት የሚሰጡ መብዛታቸው አላስደሰተውም። በዚህም ሳቢያ “በአዲሱ ጥምረት” የትጥቅ ትግሉ በአጭር ጊዜ የበለይነቱን ክልያዘ ድጋፉን እንደሚከለክል አስጠንቅቋል።

